World Bright College

World Bright College As a College uniquely situated in

World Bright College, Hossana Campus envisions to be a leading private and become a centre of excellence in education and research in Ethiopia and Horn of Africa.

ዉድ የወርልድ ብራይት ኮሌጅ ተማሪዎች እና የቻናልችን ቤተሰቦች የኢትዮጵያ በሔራዊ ቡድን ለ33ኛ የአፊርካ ዋንጫ በማለፉ ደስታችን ወደር የለዉም። ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ እኛም ደስ ብሎ...
31/03/2021

ዉድ የወርልድ ብራይት ኮሌጅ ተማሪዎች እና የቻናልችን ቤተሰቦች የኢትዮጵያ በሔራዊ ቡድን ለ33ኛ የአፊርካ ዋንጫ በማለፉ ደስታችን ወደር የለዉም። ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ እኛም ደስ ብሎናል።
በዚህም ጨዎታ የተመለከትነዉ ፊጹም ኢትዮጵያውነትን ስሆን፤ እኛ ኢትዮጵያን አንድ ሆነን በቛንቛ፣በብሔር እና በሀይማኖት ሳንለያይ ለአንድ አላማ ሲንቆም የሚኖረው ዉጤት የላቀ መሆኑን ለማረጋገጥ ችለናል። ስለዚህ ወንድሞቻችን ከኮትዲቫር ጋር ባደረጉት ጨዋታ እንዳየነዉ ሁላችንም በተሠማራንበት የሥራ መስክ ሁሉ እግዚአብሔርን በማስቀደም ለሕዝባችንና ለሀገራችን ስኬት ያለመታኬት በትጋት እና በጥራት ከሰራን የሀገራችን ከፊታዋ እና ትንሳዔ በአፊርካ ቀንድ እና በመላ ዓላም የምታይበት ጊዜ ቅርብ ነው።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ ይጠብቀንም ።
ለኢትዮጵያ የከፊታ ጊዜ ነው።

28/03/2021
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ(Notice: for Open Job Vacancy)ወርልድ ብራይት ኮሌጅ በሆሳና እና በስሩ ላሉት ካምፓሶች ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የስራ መደቦች ላይ ሠራተኞችን...
27/03/2021

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
(Notice: for Open Job Vacancy)
ወርልድ ብራይት ኮሌጅ በሆሳና እና በስሩ ላሉት ካምፓሶች ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የስራ መደቦች ላይ ሠራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
World Bright College need to hire the Applicants on the following vacant job position for Hossana Main campus and Branches that are working under main Campus Based on the Criteria provided Below)

'' የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቛማት ድርሻ እና አስታዉጽዖ ለሀገራዊ ብልጽግና '' በሚል መሪ ቃል ለግል ከፊተኛ ትምህርት ተቛማት አመራሮች በፖሊሲና እስትራቴጂ ላይ ሥልጠና መዉሰዳችን ይታወቃ...
24/03/2021

'' የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቛማት ድርሻ እና አስታዉጽዖ ለሀገራዊ ብልጽግና '' በሚል መሪ ቃል ለግል ከፊተኛ ትምህርት ተቛማት አመራሮች በፖሊሲና እስትራቴጂ ላይ ሥልጠና መዉሰዳችን ይታወቃል።
የሳይንስና ከፊተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ '' ፖሊሲና ስትራቴጂው ለሀገራችን ብልጽግና ጉዞ ከፍተኛ አስታዋጽዖ ስላለው የግሉም ዘርፊ ለዚህ ተግባር ትልቅ ኃላፊነት እንዳለዉ ገልጸዋል" በመሆኑም ተቛማችንም ይህንን ተልዕኮ በመቀበል በጥራትና በቁርጠኝነት የልማት ፖሊሲ፣የፖሊስዉን ማስተግበሪያ ፕሮግራሞችን እና የቀጣይ 10 ዓመታት የልማት ዕቅድ እና ቁልፍ የዉጤት አመልካች/ KPI/ ትግበራዎችን በማሣለጥ በራሱ የሚተማመንና በገበያ ተወዳዳር ሊሆን የምችል የሰው ኃይል ለማፍራት ተቛማዊ የዉስጥ አቅም በመገንባት ኮሌጃችንን በዉስጥ እና በዉጭ በአካዳሚክ እና አስተዳደር ዘርፋ በሙያቸዉ የሚተማመኑ ጠንካራ አደረጃጀት በመፍጠር፤ በጠንካራ ፖሊሲና ስትራቴጂ የበለፀገና በዕቅድና ትግበራ እንዲሁም በመልካም ስነ- ምግባር የተመሠገነ ተፈላጊና ተመራጭ ኮሌጅ ለማድረግ ይበልጥ ለሥራ ያነሳሳና ያዘጋጄ ስልጠና ሆኖ አግኝተነዋል።
በዚህም ሥልጠና ወቅት ከእኛ እና ከአቻ ተቛማት ባቀረብነው ጥያቄና አስተያየት ነጥቦች ላይ ሠፊ ዉይይት ካደረግን በኃላ በክቡር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ እና በክቡር ዶክተር አንዱአለም አድማሴ ማጠቃለያ ሀሳብ ሰጥተዉ ሥልጠናዉን ለማጠናቀቅ ችለናል።
ይህንን ከፍ ያለ ሥልጠና ላዘጋጁልን የሳይንስና ከፊተኛ ትምህርት ሚኒሰተርን በኮሌጃችን ስም ላቅ ያለ ምስጋና እናቀርባለን።
መጋቢት 14/2013 ዓም
መግኖሊያ ሆቴል
አድስ አበባ ኢትዮጵያ

11/03/2021

ዉድ የኮሌጃችን ተማሪዎች እና የቻናላችን ቤተሰቦች እንደሚታወቀዉ ኮሌጃችን የመማር ማስተማር ስራን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከነርሴር እስከ ስምንተኛ እንድሁም ከዲፕሎማ እስከ ማስተርስ ዲረስ ጥራት ያለውን ትምህርት በከፊተኛ ባለሙያዎች (በኤክስፔርቶች፣በረ/ፕ/ሮች፣በተጠባባቂ ፕ/ሮች፣ በዶ/ሮች እና በፕሮፌሰሮች) በማስተማር ላይ እንገኛለን። በዚህ ወቅት ለበርካታ በለሙያዎች ጊዜያዊ እና ቛሚ የስራ ዕድል መፊጠር ተችለዋል። ከዚህም በተጨማሪ ከትምህርት ጎን ለጎን በኮሌጃችን የተለያዩ የማህበረሰብ አቀፊ ስራዎች በመስራት ላይ የሚንገኝ ስሆን፤ ከነዚህም በጥቅቱ # ከ27 በላይ ለሆኑ ተማሪዎች ነፃ የት/ት ዕድል መስጠት፣ በፊቅርና ሪህራሄ ቡድን ለታቀፉ ለ30 ልጆች ሙሉ የት/ት ቤት ቁሳቁስ በየዓመቱ መስጠት፣ ከመንግስት እና ከሕዝብ የሚቀርበውን ጥር በመቀበል በመንግስት ፕሮጄክቶች፣በማዕድ ማጋራት እና ወቅቱን ያገናዘቤ ችግር ፈች ጥናቶችን ማድረግ የኮሌጃችን ኃላፊነት፣ ሀገራዊና የዜግነት ግዴታችን በመሆኑ በከፊተኛ መነሳሳት በመከወን ላይ እንገኛለን። በዚህም ሚክንያት # በዋቸሞ ዩኒቨርሲት እና በሠላሚ ሚኒሲተር አዘጋጂነት ከመላ ኢትዮጵያ ወደ ዋቸሞ ዩኒቨርሲት መጥተው ስልጣና ስወስዱ ለነበሩ ከ1,400 በላይ ለሆኑ ሠልጣኞች ባደረግነው የማህበረሰብ አገልግሎት የሠላም አምባሳደር ከሆነው የዋቸሞ ዩኒቨርሲት የዋንጫ፣ የሜዳልያና የሠርትፊኬት ሽልማት ልናገኝ ችለናል። ይህም ሺልማት የአጠቃላይ የኮሌጃችን ማህበረሰብ እና የቻናላችን ቤተሰቦች በመሆኑ ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አልን።
የካትት23/2013 ዓ/ም
ዋቸሞ ዩኒቨርሲት
ሆሳዕና ኢትዮጵያ

03/03/2021

World Bright College, envisions to be a leading private and become a centre of excellence in education and research in Ethiopia and Horn of Africa.
As a World Bright College is uniquely situated in the Country, committed to teaching learning and community service and consultancy that bring an important difference in the lives of our customers around Hossana, and the nation at large . and # join our channel

17/02/2021

ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ባሉበት

ጉዳዩ፦ ለስራ የዋስትና ገንዘብ ማስያዝን ይመለከታል
ማንኛውም የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ፈቃድ አግኝቶ ወደ ማስተማር ከመግባቱ አስቀድሞ ለስራው ዋስትና በገንዘብ ብር 500,000.00(አምስት መቶ ሺህ ብር) በባንከ የዝግ አካውንት ማስያሰዝ ወይም ተመጣጣኝ የባንክ ዋስትና ማቅረብ እንዳለበት በአዋጅ ቁጥር 1152/2011 አንቀጽ 79 ንዑስ ቁጥር 5 ላይ ተደንግጓል፡፡ በመሆኑም ከየካቲት 09/2013 ዓ.ም. ጀምሮ ማንኛውም ነባር ወይም አሁን ጥያቄ አቅርባችሁ ውጤት በመጠባበቅ ያላችሁ የአዲስ ወይም የእድሳት ፈቃድ ጠያቂዎች እንዲሁም ወደፊት ጥያቄ ማቅረብ የፈለጋቸሁ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአዋጅ ቁጥር 1152/2011 አንቀጽ 79 ንዑስ ቁጥር 5 የተጠቀሰውን ብር 500,000.00(አምስት መቶ ሺህ ብር) በባንከ የዝግ አካውንት ማስያሰዝ ወይም ተመጣጣኝ የባንክ ዋስትና በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንድታቀርቡ እያሳሰብን ይህ ባልሆነበት የተቋማትን የዕውቅና ፈቃድ/እድሳት የማናስተናግድ ከመሆናችን በተጨማሪ ቀጣይ አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ታውቆ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡
ከሠላምታ ጋር
ግልባጭ፡
ለክቡር ሚኒስትር ጽ/ቤት
ለክቡራን ሚኒስትር ዴኤታዎች
ሳከትሚ
ለዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት
ለም/ዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት
ከትአጥኤ

11/02/2021

የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፊጠን በአዕምሮ የበለፀገ የተማረ የሰው ኃይል ያስፈልጋል። ስለሆነም የመንግስትና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቛማት አስተዳደራዊና ማዋቂራው ለውጥ በማድረግ በተግባር የሚታይ ለውጡን የሚያስቀጥል ጠንካራ ኢስትራቴጂ በመንደፊ በትምህርት፣በጥናትና ምርምር በመልካም ስነ ምግባር ሀገርን ከምገነቡ ተቛማት አንዱ በመሆን በየትኛውም መመዘኛ ተወዳዳሪ እና አምራች ዜጋ ለመፊጠር በየተቛማችን ከፍተኛ ሥራ ይጠብቀናል።
በዉይይት መድረኩ የትምህርት ተቛማት የምሰጠውን የትምህርት አግባብነት፣ጥራት፣ ፋትሀዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ መመሪያና ደንቦችን መተግበር እና የከፊተኛ ት/ት አግባብነትንና ጥራትን ማረጋገጥ እንዳለብን የሚያስችል ሀገራዊ ጥር ቀርቦ በምክክር መድረኩ ልንወያይ ችለናል። በዚህም ይህን ፕሮግራም ላዘጋጀው የሳይንስና ከፊተኛ ትምህርት ሚኒስተርን በኮሌጃችን በወርልድ ብራይት ስም ምስጋናችንን እናቀርባለን።
ጥር 25/2013ዓ/ም
ሂልተን ሆቴል አድስ አበባ

Address

Hoedspruit

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when World Bright College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category