15/01/2023
መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ገጽ ያለው ትልቅ መጽሐፍ እንደሆነ ታውቃለህ። ሆኖም ይህ ተስፋ እንዲያስቆርጥህ አትፍቀድ! ከዚህ ይልቅ መጽሐፍ ቅዱስን ከድግስ ቡፌ ጋር ልታመሳስለው ትችላለህ። የቀረበውን ነገር ሁሉ ልትበላ አትችልም። ሆኖም የምትፈልገውን ምግብ መርጠህ እስክትጠግብ ድረስ መብላት ትችላለህ።
ከመጽሐፍ ቅዱስ ንባብህ የተሟላ ጥቅም ማግኘት ከፈለግክ ሙሉ ትኩረትህን በምታነበው ነገር ላይ ማሳረፍ ይኖርብሃል። #ከታች የቀረቡት ሐሳቦች እንዲህ እንድታደርግ ይረዱሃል #
።።።። #ከመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ጋር በተያያዘም ሁኔታው ተመሳሳይ ነው። በችኮላ ከማንበብ ይልቅ ጊዜ ወስደህ አእምሮህና ልብህ በትምህርቱ ላይ እንዲያተኩር አድርግ። የመዝሙር 119 ጸሐፊም ያደረገው ይህንኑ ነው። ስለ አምላክ ሕግ ሲናገር “ቀኑን ሙሉ አሰላስለዋለሁ” ብሏል።—መዝሙር 119:97
እርግጥ ይህ ሲባል ቃል በቃል ቀኑን ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን እያነበብክና እያሰላሰልክ መዋል አለብህ ማለት አይደለም። ታዲያ ነጥቡ ምንድን ነው? መዝሙራዊው ስለ አምላክ ቃል ለማሰብ ጊዜ መድቧል። እንዲህ ማድረጉ ደግሞ ጥሩ ውሳኔ ለማድረግ ረድቶታል።—መዝሙር 119:98-100
“እናቴ በአንድ ወቅት እንዲህ ብላኝ ነበር፦ ‘በሳምንት ውስጥ ሰባት ቀናት አሉ፤ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ለራስሽ ብዙ ነገር ታደርጊያለሽ። ታዲያ ለይሖዋ የተወሰነ ጊዜ ብትሰጪው ምክንያታዊ አይመስልሽም?’”—ሜላኒ
ጊዜ ወስደህ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ መመሪያዎች ማሰብህ ጥሩ ውሳኔ ለማድረግ ይረዳሃል፤ ለምሳሌ ጓደኛ ስትመርጥ ወይም መጥፎ ነገር እንድታደርግ ስትፈተን የተሻለ ውሳኔ ማድረግ ትችላለህ።