08/02/2023
በ2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች:: የማህበራዊ ሣይንስ ተማሪዎች ናቸው::
We are a network of people across the globe working together to raise money and build a high school in Chachkuna, Ethiopia.
Because of redistricting, Chachkuna Woreda’s Administration was transferred from Gondar Zuria to Lay Armachiho. Based on this reason, the Chachkuna schools are now administrated by Lay Armachiho educational administration and students are allowed to study only in the Tikel Dengay High School which is more than 35 kilometers away from Chachkuna. Because of school redistricting and policies, stude
08/02/2023
በ2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች:: የማህበራዊ ሣይንስ ተማሪዎች ናቸው::
07/10/2023
የ2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ከመገባደዱ በፊት ተማሪዎች በወላጆቻቸው ፊት ሰርትፍኪት ሲቀበሉ: የግንባታ ግብአት የሆነው አሸዋና ግንባታው እየተካኺደ ምሆኑን የሚያሳዩ ፎቶዎች ናቸው::
እየተገነባ ላለው ተጨማሪ አንድ ብሎክ 4 መማሪያ ክፍሎች ተማሪዎች ድንጋይ ሲያቀርቡ
የጫጭቁና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በዓመቱ ማብቂያ አባላጫ ነጥብ ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ዕውቅና ሲሰጥ::
03/20/2023
በጫጭቁና አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እየተገነባ ያለውን ተጨማሪ አንድ ብሎክ 4 መማሪያ ክፍሎች የሚያሳዩ ፎቶዎች ናቸው። ግንባታው እስከ ግንቦት ባለው ጊዜ ተጠናቆ ክፍሎቹ መስከረም ወር 2016 ዓ/ም ለመማር ማስተመር ዝግጁ ይሆናሉ። ት/ቤቱ ገና ከውጥኑ ጀምሮ እንዲሠራ በሃሳብ በሞራልና በማተሪያል ለረዳችሁን ሁሉ ክልብ እናመሰግናለን።
በ2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ት/ቤቱ 437 ተማሪዎች፤ 50 መምህራን የአስተዳደርና የጥበቃ ሠራተኞች እያስተናገደ ይገኛል።
ት/ቤቱ በ2014 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ጊዜ 64 ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና አስቀምጦ 30ዎቹ ለዩኒቭርስቲ ሲያልፉ ቀሪዎቹ 34 ደግሞ ሞያና ቲክኒክ ማሰልጠኛ ገብተው እየተማሩ ይገኛሉ። እንዲሁም ለ2015 የትምህርት ዘመን 69 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ።
11/15/2022
የጫጭቁና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት 64 ተማሪዎች በ2014 የብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወሰደዋል፦
------------------------------------------------------------------
የጫጭቁና አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታው እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በ2007 ዓ.ም ጀምሮ የመማር ማስተማር ተግባሩን በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም አስጀምሯል። በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 437 ተማሪዎች፤ 26 መምህራን፤ 8 የአስተዳደርና 2 የጥበቃ ሠራተኞች እያስተናገደ ይገኛል።42 የማህበራዊ ሳይንስና 22 የተፈጥሮ ሣይንስ ተማሪዎች በ2014 ዓ.ም የብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስደዋል።እነዚህ የብሔራዊ መልቀቂ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸው ሰምሮ እራሳቸውን ቤተሰቦቻቸውንና አገራቸውን የሚያገለግሉ ብቁ ዜጎች እንዲሆኑ ከወዲሁ እንመኛለን።
04/14/2022
በጫጭቁና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቅጥር ግቤ ላይ እየተገነባ ያለው የንጹህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ለተማሪዎች፣ ለመምህራን፣ ለአከባቤው ህብረተሰብና ለከብቶቻቸውም ጭምር ነው።
04/10/2022
እነዚህ ፎቶዎች የሚያሳዩት በጫጭቁና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቅጥር ግቤ ላይ እየተገነባ ያለው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ነው። ኃላፊነቱን ወስዶ ይህንን ፕሮጀክት እያስገነባ ያለው ወገን የሕፃናትና እናቶች መርጃ ማህበር የሲያትል ቅርንጫፍ ነው። በዚህ አጋጣሚ ወገንን እናመሰግናለን።
04/09/2022
በጫጭቁና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቅጥር ግቤ ላይ እየተገነባ ያለው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ነው። ኃላፊነቱን ወስዶ ይህንን ፕሮጀክት እያስገነባ ያለው ወገን የሕፃናትና እናቶች መርጃ ማህበር የሲያትል ቅርንጫፍ ነው። በዚህ አጋጣሚ ወገንን እናመሰግናለን።
04/09/2022
በጫጭቁና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ላይ እየተገነቡ ያሉት ተጨማሪ መማራ ክፍሎች በቪድዮ ይህን ይመስላል:: ግንባታው ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ተጠናቆ መስከረም 2014 ዓ,ም አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ነበር የተጀመረው:: ሆኖም ግን አንድ አመት ዘግይቶም ቢሆን መስከረም 2015 ዓ.ም አገልግሎት እንዲሠጥ የግንባታውሥራ እየተካኺደ ነው:: የሞራል የሃሳብና የገንዘብ አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው::