03/06/2026
ዛሬ ቀን 26/9/2018 ዓ.ም በቃራዎ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በማለቅ ላይ ያለውን ህንፃ ግንባታ የማጠናቀቂያ ሥራዎች ቁመና ግምገማ ተደርጓል።
ኢንጅነር ዳዊት ደስታ የዳውሮ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መመሪያ ኃላፊ ፣ የዛባ ጋዞ ወረዳ አሰተዳደር የተቋሙ ቦርድ ሰብሳቢና ልዑካናቸው በተገኙበት የኮሌጁን አሁናዊ የህንፃ ግንባታ ምልከታና ግምገማ አድርጓል።
የመምሪያው ኃላፊ ኢንጂነር ዳዊት አክለውም ተቋራጩ አሁን እያሳየ ያለውን ፍጥነት አጠናክሮ በመቀጠል ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ማጠናቀቅ እንዳለበት አሳስበዋል።
ኢንጅነር ዘላለም ተስፋዬ የዞኑ ግንባታ ሳይት ተቆጣጣሪ መሀንዲስ ፣ ኢንጅነር መብራቱ መምህሬ የዳውሮ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መመሪያ የግንባታ ቁጥጥር ሱፐርቪዥን ሥራ ሂደት አስተባባሪ በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ሀሳባቸውን አንስተዋል።
ልዑካኖቹ በጉብኝታቸው ወቅት እስካሁን የተከናወኑት ሥራዎች እጅግ በጣም የተሻሉና በተፈለገው ጥራት እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
#ዘገባው ቃራዎ ኮ/ኢ/ኮሌጅ 🌺🌺