እንኳን ለኢትዮጵያ የዘመን መለወጫ
🌼🌻እንቁጣጣሽ🌼🌻🌼
🌻🌼በሰላም አደረሰን! 🌻🌼
🌼🌻አዲሱ🌻🌼
🌻🌼የ2017 ዓ/ም🌼🌻
በአገራችን ያለ ስጋት ከቦታ ቦታ የምንቀሳቀስበት🌻 🌼🌻ፀጥታ ነግሶ በልባችን የሰላም አየር የምንተነፍስበት
🌻🌼 የምንፈልገውን ዕቅድ የምናሳካበት🌻 🌻🌼🌻🌼የምንመኘውን የምናገኝበት🌻🌼
🌻🌼የሰላም🌻🌼
🌼🌻የጤና🌼🌻
🌻🌼የፍቅር🌻🌼
🌼🌻የደስታ🌼🌻
🌻🌼የመተሳስብ🌻🌼
🌼🌻መቻቻል🌻🌼
🌻🌼የአንድነት🌻🌼
🌼🌻ዘመን 🌼🌻
🌻🌼ይሁንልን🌻🌼
🌼🌻መልካም አዲስ ዓመት!!🌻🌼
ከለገሰ
መስከረም ፩/2017 ዓ/ም
Educational issues
ባንጃ ወረዳ በአሁኑ ሰዓት በ2009 ዓ.ም 50 የመጀመሪያ ደረጃ ?
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሰኞ ይፋ ይደረጋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ሰኞ ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ/ም እንደሚገለጽ አሳውቋል።
ለተማሪዎቹ መልካም ውጤት ይሁንላችሁ!!
02/09/2024
12/06/2024
ትውልድ ጥራት ያለውን ትምህርት እንዲማር ሁሉም የዜግነት ኃላፊነትን መወጣት ያስፈልጋል። የፈተና ሥርዓቱም ተገቢነት ባለው ሁኔታ ተማሪዎች በራሳቸው እውቀት፣ ክህሎት እና አመለካከት ሃቅም ብቻ የሚመዝን መሆን አለበት። የ2016 ዓ.ም የባንጃ ወረዳ የመካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መልቀቂያ 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አፈታተን ሂደት በከፊል (የቅዳማጃ መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት )❤❤❤
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሠሌዳ ይፋ ሆነ!!
የትምህርት ሚኒስቴር የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሠሌዳ ይፋ አደረገ።
በዚህ መሠረት
*በመጀመሪያ ዙር የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ከመስከረም 26 እስከ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገቡ ሲሆን÷ መስከረም 29 ቀን 2015 ዓ.ም ኦሬንቴሽን ይሰጣል፡፡
ከመሰከረም 30 እሰከ ጥቅምት 2 ቀን 2015 ፈተና ይሰጣል፤ ጥቅምት 3 እና 4 ቀን 2015 ዓ.ም ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ።
*በሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ።
በዚህም ጥቅምት 5 እና 6 ቀን 2015 ዓ.ም ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም ኦሬንቴሽን ለተፈታኞች ይሰጣል።
ከጥቅምት 8 እሰከ 11 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ፈተና የሚሰጥ ሲሆን፥ ከጥቅምት 12 እና 13 ቀን 2015 ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው እንደሚመለሱ ተገልጿል።
መረጃው ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘ ነው፡:
01/10/2022
የአገራችን የትምህርት ሥርዓት በአዲስ ሥርዓት-ትምህርት መሠረት አዲስ መፅሐፍ ተዘጋጅቶ በአዲስ የተነሳሽነት ስሜት፣ የተሻለ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነት፣ እና ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ አዲሱ የትምህርት ዘመኑን መስከረም 9/2015 ዓ/ም እንደሚጀመር ይጠበቃል።
በዚህም መሠረት የባንጃ ወረዳ የትምህርት አጀማመር ቀኑን በወረዳው ባሉት ሁሉም ት/ቤቶች በደመቀ ሁኔታ ተጀምሯል። በአጀማማሩ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች፣ የትምህርት አመራሮች እና ባለሙያዎች፣ የወረዳው አመራሮች በተገኙበት በወረዳ ደረጃ ከሳ አጠ/፩ኛ/ደ/ት/ቤት በድምቀት ተከብሯል።
ባለፈው የትምህርት ዘመን የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ሽልማት በመስጠት ተጀምሮ መምህራን እና ተማሪዎች በክፍል ውስጥ በመማር ማስተማር /day one class one/ ሂደት ፊት ለፊት በናፍቆት ተገናኝተው ውለዋል።
መልካም የትምህርት ዘመን ይሁን!!
===========================
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Website
Address
London