መምህር ኢንጂነር ታሪኩ አበራ

መምህር ኢንጂነር ታሪኩ አበራ

Share

ይህ ገጽ ሕዝብን የሚያንጽ መንፈሳዊ ትምህርት፣ምክርና መረጃ

03/06/2026

«የሰውን ደም የሚያፈስ ሁሉ ደሙ ይፈስሳል፤ ሰውን በእግዚአብሔር መልክ ፈጥሮታልና» ኦሪት ዘፍጥረት 9፥ 6

30/05/2026

† በአትላንታ ቅድሥት ሥላሴ ቤተክርስቲያን †

በዓለ ጰራቅሊጦስ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ የወረደበት ታላቅ ዕለት ነው።ይህ ዕለት ለቤተክርስቲያን የልደት ቀን ነው፤በአትላንታ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በልዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ይታሰባል፤ስለሆነም ሁላችሁ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በዕለቱ ከነቤተሰባችሁ ወደ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን መጥታችሁ የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በታላቅ አክብሮት ተጋብዛችኋል።

በዕለቱ በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ከሌሊቱ 4 AM ጀምሮ ሥርዓተ ማኅሌት፣ቅዳሴ፣የወንጌል አገልግሎትና ዝማሬ ስለሚኖር ከነቤተሰባችሁ መጥታችሁ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋና ረድሄት ትካፈሉ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

ለሌሎችም ሼር አድርጉት

29/05/2026
28/05/2026

በረከታቸው ይደርብንና ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሀገረ እንግሊዝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ነበሩ።

27/05/2026

★ መንግሥት ሐሰተኛ ነቢያትና አጭበርባሪ ፓስተሮች ★

"የምታስደንቅና የምታስደነግጥ ነገር በምድር ላይ ሆናለች፤ነቢያት በሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፤ካህናትም በእነዚህ እጅ ይገዛሉ፤ህዝቤም እንደዚህ አይነት ነገር ይወዳሉ፤በፍጻሜውስ ምን ታደርጋላችሁ?" ኤር 5፡30-31

"እነሆ ከምላሳቸው ትንቢት አውጥተው፡-እርሱ ይላል በሚሉ ነቢያት ነኝ ይላል እግዚአብሔር፡፡እነሆ ሐሰትን በሚያልሙ፣በሚናገሩም፣በሐሰታቸውና በድፍረታቸውና ህዝቤን በሚያስቱ በነቢያት ላይ ነኝ ይላል እግዚአብሔር፡፡እኔም አልላክኋቸውም አላዘዝኋቸውምም ለእነዚህም ህዝብ በማናቸውም አይረቡአቸውም ይላል እግዚአብሔር፡፡" ኤር 23፡30-32

የጸጋ ስጦታዎች ቤተክርስቲያንን ለማነጽ ሆኖ ሣለ በጸጋ ስጦታ ስም የሚገለጡ የተለያዩ የሐሰት አሠራሮች ደግሞ ሕዝብን በእጅጉ ይፈታተናሉ፣ያዳክማሉ አብዛኛውን ጊዜ በቤተእምነቶች የሚታዩ የስህተት አሠራሮችና መልዕክቶች የሚመጡት ነቢያት ነን በሚሉ የሐሰት ትንቢት በሚናገሩና ህዝቡ በከንቱ ተስፋ እንዲታመን በሚያደርጉ ሰዎች ነው፡፡እነዚህ ሰዎች የሐሰት ነቢያት ይባላሉ፡፡

እውነተኛ ትንቢትና ነቢያት እንዳሉ ሁሉ ሐሰተኞችም በብዛት እንደተነሱ ቃሉ በግልጥ ይናገራልና አገልግሎታቸውን በእግዚአብሔር ቃል መፈተሸና ለቃሉ ቅድሚያ መስጠት ይገባናል፡፡

ሐሰተኛ ነቢያት በሁለት ይከፈላሉ፡-
1ኛ) የዋጃቸውን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የሚክዱ (2ኛ ጰጥ 2፡1-3) ከእግዚአብሔር ያልሆኑና በመናፍስታዊ ኃይል ተሞልተው በክርስቶስ ተቃዋሚ መንፈስ የሚናገሩ ናቸው፡፡

2ኛ) በጌታ የሚያምኑ ሆነው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውነተኛ ጥሪና ጸጋው እያላቸው በእግዚአብሔር ህዝብ መካከል የሚገኙ ግን ከእግዚአብሔር ያልሆነ ትንቢት የሚናገሩ ናቸው፡፡

እነኝህ ሰዎች ራሳቸውን ነቢያት ተብለው በነቢይነታቸው እየታወቁ ሳለ ግን ከእግዚአብሔር ቃል ያፈነገጡ፣ለገንዘብ፣ለክብርና ለዝና ሲሉ ከእግዚአብሔር ሳይሆን ከገዛ ልባቸው እና በሰይጣን ተታለው የሐሰት ትንቢትን የምናገሩ ናቸው፡፡መጽሐፍም ስናገር በፍሬያቸው ታውቃላችሁ እንደምለን ሁሉ በፍሬያቸው ለይተን ልናውቃቸው ይገባል፡፡እስቲ የሐሰተኛ ነቢያትን የአገልግሎት ባህሪ በቃሉ እንመዝን

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሐሰተኛ ነቢያት ምን ይላል ?፡-
• በምድረ በዳ እንደሚኖሩ ቀበሮዎች የፈረሰው እንዲጠገን የማይሹ ይልቁን ከፍርስራሹ መጠቀም የሚፈልጉ ናቸው፡፡ (ሕዝ 13፡4)

• ከእግዚአብሔር ሳይላኩ ትንቢት የሚናገሩ (ኤር 29፡31)

• ህዝቡን ይደልላሉ እንጂ አያንጹም ለጥቅማቸውም አይሆኑም (ኤር 23፡32)
• ስለጭብጥ ገብስና ስለቁራሽ እንጀራ ትንቢት የሚናገሩ ናቸው፡፡(ሕዝ 13፡9) ሐሰተኛ ነቢያት ለእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ ናቸው፡፡
• "...ያመነዝራሉ በመዋሸትም ይኖራሉ፣ማንም ከክፋቱ እንዳይመለስ የክፉዎችን እጅ ያበረታሉ...፡፡" (ኤር 23፡14)
• "...ከእግዚአብሔር አፍ የወጣ ሳይሆን፣ከገዛ ልባቸው የወጣውን ራዕይ ይናገራሉ፡፡" (ኤር 23፡16)
• "እኔን ለሚንቁኝ እግዚአብሔር ሰላም ይሆንላችኋል ብሏል ይላሉ፤የልባቸውን እልከኝነት ለሚከተሉ ሁሉ ክፉ ነገር አይነካችሁም ይላቸዋል፡፡" (ኤር 23፡17)
• "ሰላም ሳይኖር 'ሰላም አለ' እያሉ ህዝቡን ያስታሉ፤ህዝብ ካብ ሲሰራ እነርሱ በኖራ ይለስናሉ፡፡" (ህዝ 13፡10)
• የእግዚአብሔርን ፍላጎት ሳይሆን የራሳቸውን ፍላጎቶች ለማሟላት ይናገራሉ፡፡ኤር 14፡14፣ኤር 23፡21-22 ፣ህዝ 13፡1-3
• ህዝቡን ስለ ኃጢአታቸው ከመገሰጽ ይልቅ እግዚአብሔር በህዝቡ እንደተደሰተ ይገልጻሉ፡፡ እውነታው ግን ህዝቡ በኃጢአቱ ምክንያት ለፍርድ እየተዘጋጀ መሆኑ፡፡ኤር 23፡11-17፣ህዝ 13፡8-16 ህዝ 13፡22
• ሐሰተኛ ነቢያት በውጪያዊ ሁኔታዎች ከእውነተኛ ነቢያት ጋር ተመሣሣይነት አላቸው፡፡ በውስጣቸው ግን ነጣቂ ተኩላዎች ናቸው፡፡(ማቴ 7፡15)
• ነቢያቶች በገንዘብ ያምዋርታሉ (ምክ 3፡11)
• ከእግዚአብሔር ሳይሆን ከገዛ ራሳቸው ትንቢት ይናገራሉ፣አንዳች ነገር ሳያዩ የራሳቸውን መንፈስ የሚከተሉ ሞኞች ናቸው፡፡(ህዝ 13፡1-3)
• የተናገሩት የሐሰት ትንቢት እንዲፈጸም በብዙ ቃልና በተደጋጋሚ የምናገሩ እንዲሁም ህዝቡ እንደተከተላችሁ በከንቱ ተስፋ የሚያስደርጉ ናቸው፡፡በሕዝቅኤል ዘመን ያሉ የሀሰት ነቢያት ሐሰት መናገር ብቻ ሳይሆን ቃሉ ይፈጸም ዘንድ ተስፋ አድርገዋል፡፡ (ሕዝ 13፡6)
• ሐሰተኛ ነቢያትና ሐሰተኛ ሰዎች እርግጠኛ ራዕይ ይኑራቸው አይኑራቸው አይታወቅም፤እነርሱ ግን ከእግዚአብሔር ራዕይ እንደተቀበሉ ይናገራሉ፤ይሁን እንጂ የመልዕክታቸው ይዘት ስመረመር አድማጮቻቸው ልሰሙአቸው የምፈልጉት ብቻ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ኢሳ 30፡10 ኤር 23፡9-17 2ኛ ጢሞ 4፡3
• ሐሰተኛ ነቢያት ሐሰት የሚናገሩት ለራሳቸው ጥቅም ለማግኘትና በአለቆቻቸው ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ነው፡፡ (ነህ 6፡11-13)
• ሐሰተኛ ነቢያት በክፉ መንፈስ ተመርተው ትንቢት የሚናገሩ ናቸው፡፡ 1ኛ ነገ 22፡19-25
በአጠቃላይ አገልግሎታቸውና ህይወታቸው ሲታይ ያመነዝራሉ፣ይዋሻሉ፣ሐጥአተኛው ከሐጥአቱ በንስሐ እንዲመለስ የንስሐ መልዕክት አያመጡም፣ከራሳቸው ልብ ትንቢት ይናገራሉ፣እግዚአብሔርን ለምንቁ ሰላም ይሆንላችኋል፣ትባረካላችሁ፣ይሳካላችኋል ይላሉ እንጂ ከክፉ መንገዳቸው እንድመለሱ አያስጠነቅቁም፣ቃሉን በግልጥ አያስተምሩም፣ገንዘብ ይወዳሉ፣ቅድስናና ጽድቅ ላይ አያተኩሩም ምጽአቱንም አይሰብኩም፡፡በአጠቃላይ አገልግሎታቸው ሲታይ ክርስቶስ ኢየሱስ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ያከናወነውን የደህንነት ሥራ ማሳየትና የእግዚአብሔር መንግሥት ላይ ያተኮረ ሳይሆን ዲያብሎስ ኢየሱስን ሲፈትነው የዓለምን መንግሥታት ሥልንና ክብር በቅጽበት አሳይቶ ለእኔ ብትሰግድልኝ ይህ ሁሉ ላንተ ይሆናል ብሎ እንደፈተነው ሐሰተኛ ነቢያት አገልግሎታቸው ያተኮረው ህዝቡን ደስ ለማሰኘት እንዲችሉ በዚህ ምድር ሀብት፣ሥልጣን፣ዝናና ገንዘብ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

ስለዚህ በዚህ በመጨረሻ ዘመን ላይ በመሆናችን በሀሰተኛ ነቢያት እንዳንታለልና እንዳንበዘበዝ ጌታ ማስተዋሉን ይስጠን ወደ ቃሉ እውነት እንመለስ፡፡
"እነሆ ከምላሳቸው ትንቢት አውጥተው፡-እርሱ ይላል በሚሉ ነቢያት ነኝ ይላል እግዚአብሔር፡፡እነሆ ሐሰትን በሚያልሙ፣በሚናገሩም፣በሐሰታቸውና በድፍረታቸውና ህዝቤን በሚያስቱ በነቢያት ላይ ነኝ ይላል እግዚአብሔር፡፡እኔም አልላክኋቸውም አላዘዝኋቸውምም ለእነዚህም ህዝብ በማናቸውም አይረቡአቸውም ይላል እግዚአብሔር፡፡" ኤር 23፡30-32

Photos from መምህር ኢንጂነር ታሪኩ አበራ's post 26/05/2026

† ወንጌል ለሙስሊም ወገኖቼ †

ክፍል 2

"ቁርአን ክርስቶስን አምነው የሚከተሉት አማኞች ታላቅ በረከት እንዳላቸው በግልጽ ይመሰክራል።"

መ/ር ታሪኩ አበራ

وَأَمَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ فَيُوَفِّيهِمْ أُجُورَهُمْ ۗ وَاللَّهُ لَا يُحِبُّ الظَّالِمِينَ
«እነዚያ /የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳን/ ያመኑትማ መልካም ሥራዎችንም የሠሩት ምንዳዎቻቸውን ይሞላላቸዋል፡፡ አላህም በዳዮችን አይወድም፡፡»አል ኢምራን 3፥57

በአገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ሙስሊም ወገኖቼ ሁላችሁ በያላችሁበት ሰላምና ጤና ከነቤተሰቦቻችሁ ይብዛላችሁ ።

እናንት ኢትዮጵያውያን ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! አባቶቻችሁና አባቶቻችን በፍቅር እትብት ተሳስረው በደም ሐረግ ተሰናስለው ፣የዘርና የሃይማኖት አጥር ሳይገድባቸው ፍቅርን ዘርተው ፍቅርን ያሳጨዱን ከእምነትና ከተስፋ ይልቅ በፈጣሪ ፊት ታላቅ ዋጋ የሚያሰጠውን የፍቅር ሕይወት ከቃል በዘለለ በተግባር ያሳዩን የሰላም አርበኞች ናቸውና ለቀደሙት የእምነት አባቶቻችሁና አባቶቻችን ከልብ የሆነ ምሥጋናና ክብር ይግባቸዋል።

ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! በሌላው ዓለም ካለው የሙስሊም ማህበረስብ ይልቅ የእናንተ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ልባችሁ እጅግ ቅንና ርኅሩኅ የሆነ፣ከክርስቲያን ወንድሞቻችሁ ጋር በማኅበራዊ ሕይወት አብራችሁ ደፋ ቀና የምትሉ ፣ለክርስቲያን እህታችሁ በችግሯ ሰዓት ከማንም ቀድማችሁ የምትደርሱ፣የተቸገረ ምስኪን ክርስቲያን ደጃችሁ ቢቆም ዘካ ከመስጠት የማትነፍጉ ደግና ቀናዎች ናችሁና የኢትዮጵያ አምላክ ከክፉ ይጠብቃችሁ። በሕመማችሁና በችግራችሁ ሰዓት ቅዱሱን ጠበል ፍለጋ ከክርስቲያኑ ጋር ቤተክርስቲያን ገብታችሁ በፍቅር የምትጠመቁ፣ስእለታችሁ ሲደርስ ለቁልቢ ገብርኤል ድባብ ዣንጥላና የእጃችሁን አንባር አውልቃችሁ የምትሰጡ እግዚአብሔርን አክባሪ ጨዋ ማህበረሰብ ናችሁ ።

ደሴናከሚሴ፣ ኮምቦልቻና ወልድያ ቤተክርስቲያን ሲታነጽ ድንጋይ ተሸክማችሁ ፣ውሃ ቀድታችሁ የምታመላልሱ ልበ ርኅሩሆች ናችሁና በእውነት የኢትዮጵያ አምላክ ዘራችሁን ይባርክ ።በእኛ እና በእናንተ መካከል ያለውን የፍቅር ግንብ ለመደርመስና ሰላማችንን ለማደፍረስ በእምነት ስም ከባዕዳን የወረሱትን ጽንፈኝነትና አክራሪነትን ይዘው በጂኒ መንፈስ የሚሯሯጡትን ሁሉ የመርየም ልጅ አል መሲ ዒሳ ልባቸውን ይመልሰው አሜን።

ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! ዛሬ ለእናንተ ታላቁን የምስራች ቃል አድርስላችሁ ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ልቤን ከወትሮው ይልቅ እጅግ አስጨንቆታል ።ይህ ዛሬ የምትሰሙት የምሥራች ነፍሳችሁ የምትጽናናበት፣ መንፈሳቹ የሚያርፍበት፣ መዳናችሁ የሚረጋገጥበት የጽድቅ ቃል ነው።

ሁላችሁ እንደምታውቁት የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳ በድንግልና ተጸንሶ በድንግልና የተወለደ ሞትና መቃብርን ድል አድርጎ በክብር ተነስቶ በእልልታ ያረገ ድንቅ አባት ነው። ክርስቶስን የሚያምኑትና የሚከተሉት ሁሉ ታላቅ በረከትና ሰማያዊ ዋጋ እንደሚያገኙም ቁራአንና መጽሐፍ ቅዱስ በጋራ በግልጽ ይመሰክራሉ። ቁርአኑ እንዲህ ይላል
وَأَمَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ فَيُوَفِّيهِمْ أُجُورَهُمْ ۗ وَاللَّهُ لَا يُحِبُّ الظَّالِمِينَ
«እነዚያ /የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳን/ ያመኑትማ መልካም ሥራዎችንም የሠሩት ምንዳዎቻቸውን/በረከታቸው/ ይሞላላቸዋል፡፡ አላህም በዳዮችን አይወድም፡፡»አል ኢምራን 3፥57

«እነዚያንም የተከተሉህን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ከነዚያ ከካዱት በላይ አድራጊ ነኝ፡፡»አል ኢምራን 3፥55
እንግዴህ ልብ በሉ ኢየሱስ ክርስቶስን የሚያምኑትና የሚከተሉት ሁሉ ምንዳዎቻቸው የሚሞላ እስከ ትንሣኤ ዘጉባኤ ዕለት ማለትም የሰው ልጆች ሁሉ ለፍርድ እስከሚቆምባት እስከ መጨረሻይቱ ሰዓት ድረስ ክርስቶስን የተከተሉ ሁሉ ከካዱት በላይ የክብር ባለቤቶች እንደሚሆኑ ቁርአኑ በግልጽ መስክሯል።

እውነት ነው ክርስቶስን የሚያምንና እርሱን በእምነት የሚከተል ሁሉ በነፍሱ ዋስትና አለው ከጨለማም ወደሚደነቅ ብርሃን በክብር ይሻገራል ።ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ሲል አስተምሯል ። «ልባችሁ አይታወክ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም ደግሞ እመኑ »ዮሐ 14፥1 «እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የህይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ።»ዮሐ 8፥12።

የተወደዳችሁ ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳ ወደ ዚህች ምድር ያለ አንዳች ዓላማ አልተገለጠም በእግዚአብሔር የዘለዓለም እቅድ ውስጥ ለሰው ልጆች የተዘጋጀውን የዘለዓለም ሕይወትና የጽድቅ ትሩፋት በጸጋ ሊያጎናጽፈን ነው።ክርስቶስ ወደ ዚህች ምድር መጥቶ ኢንጅልን/ወንጌልን/ ከመስበኩ በፊት ዓለም በተውራት/በኦሪት/ና በሙሴ ሕግጋት እግዚአብሔርን ደስ በማሰኘት ጽድቅን ለማግኘት ሞክረው ነበር ፤ሆኖም ግን አልተቻላቸውም ሁሉም ከመርገም በታች ነበሩና ጽድቃቸው ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ተቆጥሮባቸው የሰው ልጅ ሁሉ ሲሞት እድል ፈንታውና ጽዋ ተርታው ወደ ሲኦል መውረድ ነበር ።ሆኖም ግን በሰው ልጆች ሐዘንና ስቃይ የማይደሰተው ርኅሩኅና አዛኝ የሆነው ጌታ ዓለምን የፈጠረበትን ቃሉን ወደ ድንግል ማርያም ማሕጸን ልኮ ሰው ሆኖ እንዲወለድ አደረገው እርሱም ዒሳ/ኢየሱስ/ ተብሎ ተጠራ ።

የኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመምጣትም ትልቁ ዓላማ በስራቸው መጽደቅ ላልቻሉ የአዳም ልጆች ሁሉ እርሱ የጽድቅ መንገድ ይሆናቸው ዘንድ ነው ።በቁርአኑ አንተን የተከተሉህን ከካዱት በላይ አድራጊነኝ የተባለለትም ለዚህ ነው ።ይህ ከድንግል ማርያም በፍጹም ተዋሕዶ ሰው ሆኖ የተወለደው ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሎ ይጠራል ለምን ቢባል በምድር እናት እንጂ አባት ሳይኖረው በመንፈስ ቅዱስ ድንቅ ግብር በተአምር ተወልዷልና እናቱ ድንግል ማርያም አባቱ እግዚአብሔር ተብሎ ይጠራል ፤ አንድም በልብ ታስቦ በአንደበት የሚገለጥ ቃል ልብ የወለደው የልብ ልጅ ይባላል ።ሙስሊም ወገኖቼ ብዙ ጊዜ ፈጣሪ አይወልድም አይወለድምም ስትሉ እንሰማለን ፤ነገር ግን በደንብ እንድትረዱት የምፈልገው ነጥብ ቢኖር እግዚአብሔር ልጅ አለው ሲባል በሰው የአወላለድ ሥርዓት የሚገለጥ ሳይሆን ከልብ እንደ ሚወለደው ቃል የሚመሰል ነው ።እግዚአብሔር አንድ ነው አብ በልብ ይመሰላል፣ ወልድ በቃል ይመሰላል፣ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በእስትንፋስ ይመሰላል ሦስት አማልክት ግን አንልም አንድ አምላክ ብለን እናምናለን እንጂ ። ወልድ ከአብ ተወለደም ስንል ቃል ከልብ ተወለደ የማለት ያህል ነው።ለዚህ ነው እግዚአብሔር« ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር» ያለው ሰው ሦስት ነገር አለው ነገርግን አንድ ሰው ይባላል። እያንዳንዳችን ፣ልብ ፣ቃል፣ እስትንፋስ አለን ግን ሦስት ሰዎች አንባልም አንድ ሰው ነን እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው ። አብ ፣ ወልድ ፣መንፈስ ቅዱስ ተብሎ ቢጠራም አንድ አምላክ አንድ ጌታ ነው ።( ስለ ምሥጢረ ሥላሴ ወደፊት በስፋት እንማማራለን።)

ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! ዋናው ቁም ነገሩ በሥጋ የተገለጠውን ፣በመንፈስ የጸደቀውን፣ለመላእክት የታየውን፣ በአሕዛብ የተሰበከውን፣በዓለም የታመነውንና በክብር ያረገውን ኢየሱስ ክርስቶስን በፍቅር አምናችሁ በፍቅር ትከትሉት ዘንድ ነው ይህም ለጥቅማችሁ ነው ምንዳዎቻችሁ ሁሉ ይሞላሉ፤ በነፍሳችሁም ክብርን ታገኛላችሁ መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላል «እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም»ሮሜ 8፥1 ክብር ለስሙ ይሁን ።

ኢየሱስ ክርስቶስ የነፍስ እረፍት ነው ማንም ወደ እርሱ የመጣ እንቆቅልሹ ተፈቶ፣እንባው ከፊቱ ላይ ታብሶ ፣ጨለማው ተገፎ ፣ቀንበር ተሰብሮለት በክብር ይመለሳል።ኢየሱስ ክርስቶስ የማምለጫ ዓለት ነው እርሱን ተከተሉት ከጠላት ፍላጻ በስሙ ትድናላችሁ ፣ኢየሱስ ክርስቶስ የሕይወት ውሃ ነው እርሱን ተከተሉት የጠወልገች ነፍሳችሁ በቃሉ ትለመልማለች፣ኢየሱስ ክርስቶስ መልካም እረኛ ነው እርሱን ተከተሉት በለመለመ መስክ ያሰማራችኋል ፣ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ነው እርሱን ተከተሉት ወደ ዘለዓለም ርስት ወደ አባቱ ዙፋን ያደርሳችኋል።ኢየሱስ ክርስቶስ የነፍሳችሁ ቤዛ ነው እርሱን እመኑት ጽድቅን ያለዋጋ እንዲያው በጸጋ በእምነት ትቀበላላችሁ በልጅነት ስልጣንም የመንግስቱ ወራሾች ትሆናላችሁ።

ቅዱስ መጸሐፍ እንዲህ ይላል «በልጁ የሚያምን የዘለዓለም ሕይወት አለው።»ዮሐ 3፥36
ወገኖቼ አንዳች አትጠራጠሩ ቃሉ የታመነ ነው ፤አምናችሁ ተከተሉት ተብላችኋል በእምነት ተከተሉት እርሱ በሰማያት የነፍሳችሁ ምስክር ነው ።«በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን በነፍሱ ምስክር አለው ።» ተብሎ ተጽፏል 1ዮሐ 5፥10

የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሆይ ! በኢየሱስ ክርስቶስ የማያምኑና እርሱን የማይከተሉ በምድርም ሆነ በሰማይ ብርቱ ቅጣት እንደ ሚጠብቃቸው ቁርአኑ እንዲህ ሲል በብርቱ ያስጠነቅቃል።

فَأَمَّا الَّذِينَ كَفَرُوا فَأُعَذِّبُهُمْ عَذَابًا شَدِيدًا فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَمَا لَهُم مِّن نَّاصِرِينَ
«እነዚያማ የካዱትን ሰዎች በቅርቢቱ ዓለምና በመጨረሻይቱ ዓለም ብርቱን ቅጣት እቀጣቸዋለሁ፡፡ ለእነርሱም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡»አል ኢምራን 3፥56

ልብ ያለው ልብ ይበል! በክርስቶስ ኢየሱስ የሚገኘውን ጽድቅና የዘለዓለም ሕይወት ካወቁና ከተረዱ በኋላ እንደ ተራ ነገር በማቃለል የተፈጸመልንን የቤዛነት ሥራ ማክፋፋትና መናናቅ ብርቱ ቅጣትን በነፍስም በሥጋ ያስከትላል፤ምክንያቱም የተከፈለልን ዋጋ ከአእምሮ በላይ ነው። ጌታ ልዑለ ባሕርይውን ዝቅ አድርጎ የባሪያን መልክ ይዞ በሥጋ የተገለጠው እኛን ለማክበር ነው።ምራቅ የተተፋበት ፣በአይሁድ እጅ የተንገላታው ፣ ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ እርጥብ መስቀል ተሸክሞ 65 ጊዜ እየወደቀ እየተነሳ ለመሰቀል የሄደው፣ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪታይ ድረስ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ የተገረፈው፣የእሾህ አክሊል አናቱ ላይ ደፍቶ ፊቱ በደም ጅረት የተጋረደው አንዳችም በደልና ኃጢአት ተግኝቶበት ሳይሆን እኛ የአዳም ልጆች ስለ ኃጢአታችን ልንቀበል የሚገባውን ቅጣት እርሱ በኛ ፈንታ ተቀብሎ የእርሱን ጽድቅ ለእኛ ሊያወርሰን ነው። አንድ ጊዜ የዓለሙን ሁሉ በደል ተሸክሞ በመስቀል ላይ የታየልንና ስለ እኛ እርግማን እርሱ እንደ ተረገመ ሰው መስሎ በመስቀል ላይ የዋለው ላመኑበትና ለተከተሉት ሁሉ ሕያው የሆነ የማስታረቂያ ልመና ለማቅረብ ነው።« አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅርበላቸው» በማለት ከብርቱ ጩኽትና እንባ ጋር ጸሎትና ምልጃን ፡አቀረበ ተሰማለትም ።ዓለምን ከአብ ጋር ለዘለዓለም አስታረቀ አሁን ግን ክርስቶስ በሰማያት በክብር ዙፋኑ አለ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁትም በአብ ፊት ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል ማለትም ቀድሞ የዓለሙን ሁሉ ኃጢአት ተሸክሞ ነበር የታየልን አሁን ግን የማንንም ኃጢአት ሳይሸከም ያለ ኃጢአት ይታይልናል በመስቀል ላይ የፈጸመው የቤዛነት ሥራም እይታሰበ ዛሬም በእምነት ወደ እርሱ የሚቀርቡትን ሁሉ ሲያድን ይኖራል።ዕብ 9፥28 ክብር ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን።

የተከበራችሁ ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላል «በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመን አሁን ተፈርዶበታል።»ዮሐ 3፥18 ወገኖቼ ሆይ የመዳን ቀን ዛሬ ነው ይህንን የመዳን ጥሪ በአንድም በሌላም መንገድ እግዚአብሔር ወደ ልባችሁ ያመጣላችሁ ወገኖች ዛሬውኑኑ ወስኑ ወደ ክርስቶስ ተጠጉ በእርሱ እምኑ፣ስሙን ጠርታችሁ ተማጸኑ፣ወደ ልባችሁ እልፍኝም እርሱ እንዲገባ በእምነት በልብ ቋንቋ እርሱን ጠይቁት ዛሬ በቤታችሁ ታላቅ ደስታ ይሆናል በነፍሳችሁም የዘለዓለም ድኅነትን ታገኛላችሁ ።ይህንን የመዳን የምስራች የማይቀበሉ ግን ቁርአኑ እንዳለው ብርቱ ቅጣት ይጠብቃቸዋል መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላል።«በልጁ የማያምን የእግዚአብሔር ቁጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም» ዮሐ 3፥36

ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ ቀጥሎ ያለውን ጸሎት በእምነት ሆናችሁ ጸልዩት በሕይወታችሁ ድንቅ ነገርን እግዚአብሔር ይሰራል።

« ሰማይና ምድርን ባህርና ውቅያኖስን በቃልህ የፈጠርህ የዓለም ፈጣሪ እግዚአብሔር ሆይ አንተን አምናለሁ ለአንተም እገዛለሁ፤
የሰው ልጆችን ይስተምርና ያድን ዘንድ ወደ ድንግል ማርያም ማህጸን ልከህ ሰው ሁኖ እንዲወለድ ባደረግከው በቃልህ በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ፤
እርሱንም እከተላለሁ እርሱ የጽድቅ መንገድ ነው፣እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ ቤዛ ነው፣በእርሱ ወደ አንተ ወደ እግዚአብሔር እቀርባለሁ፤
በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የልጅነት ስልጣንና የወራሽነትን ክብር በጸጋ ሰጥተኽኛልና ስምህ ለዘለዓለም ከፍ ከፍ ይበል፣
እግዚአብሔር ሆይ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ብለህ ቀንበሬን ከላዬ ላይ ስበር፣እንቆቅልሼን ፍታ፣ጨለማዬን ግፈፍ፣ታሪኬን ለውጥ፣
ከቤቴ ጣራ በታች ግባ ማዳንህንም በእኔና በቤተሰቦቼ ላይ አሳይ ክንድህን ዘርጋ በሰማያዊ በረከትም ባርከኝ ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን።»

ወድ አንባብያን ሆይ በኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነትና ፈጣሪነት ዙሪያ ከሙስሊም ወገኖቻችን የሚነሱ በርካታ ጥያቄዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ ለሚነሱት ለእያንዳናዳቸው ጥያቄዎች በሙሉ ሰፊ ማብራሪያ መልስ የሰጠሁበት ኢየሱስ ማን ነው? በሚል ርእስ ያዘጋጀሁት መጽሐፍ ስላለ ከመንፈሳዊ መጻሕፍት መደብር እየጠየቃችሁ መጠቀምና ለሚጠይቋች ሁሉ መልስ ለመስጠት ዝግጁዎች ትሆኑ ዘንድ መልእክቴን ማስተላለፍ እፈልጋለሁ።

ሙስሊም ወገኖቼም መጻሐፉን ብታነቡት ለበርካታ ጥያቄዎቻችሁ በቂ መልስ ታገኙበታላችሁ።

እባካችሁ ይህንን መልእክት ለሙስሊም ወገኖቻችን ሁሉ ሼር በማድረግ የክርስቶስ ወገን ታደርጓቸው ዘንድ በፍቅር እጠይቃለሁ።
ለበረከት ሁኑ።

ይቀጥላል


እባክዎን ፔጁን like ያድርጉ

«በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ »ሉቃ 24፥45 25/05/2026

በአትላንታ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የተሰጠ የወንጌል አገልግሎት።

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቅደሱ ጸንተን እርሱን እያመለክን ኖረን የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ እንድንላበስ ሁላችንን ይርዳን።

ትምህርቱን ዩቲዩብ ውስጥ ገብታችሁ አድምጡ ለሌሎችም ሼር አድርጉ።

https://www.youtube.com/live/ADx5TMFg1FE?si=uUf742KmGH9GyUst



«በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ »ሉቃ 24፥45 In this channel you can get all Ethiopian Orthodox Tewahido Church ...

23/05/2026

የዲቁና ትምህርት መማር የምትፈልጉ ታዳጊዎችና ወጣቶች ዘወትር ቅዳሜ ከ11AM -1PM በአትላንታ ደብረ ብርሃን ቅድሥት ሥላሴ ቤተክርስቲያን እየመጣችሁ መማር ትችላላችሁ።ትምህርቱ በነጻ ነው።

ውዳሴ ማርያም፣ቅዳሴ፣የሰንበት መዝሙራት፣ወረቦችንና ከበሮ አመታት በሚገባ ትማራላችሁ።

ወላጆችም ልጆቻችሁን እየላካችሁ ለቤተክርስቲያን ና ለሃገር የሚጠቅሙ የተባረኩ ልጆችን ታፈሩ ዘንድ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።



22/05/2026

† ወንጌል ለሙ*ስ*ሊ*ሞች †

ክፍል 1

"ቁርአን ክርስቶስን አምነው የሚከተሉት አማኞች ሁሉ ታላቅ በረከት እንዳላቸው በግልጽ ይመሰክራል።"
መ/ር ታሪኩ አበራ
ﻭَﺃَﻣَّﺎ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﻭَﻋَﻤِﻠُﻮﺍ ﺍﻟﺼَّﺎﻟِﺤَﺎﺕِ ﻓَﻴُﻮَﻓِّﻴﻬِﻢْ ﺃُﺟُﻮﺭَﻫُﻢْ ﻭَﺍﻟﻠَّﻪُ ﻟَﺎ ﻳُﺤِﺐُّ ﺍﻟﻈَّﺎﻟِﻤِﻴﻦَ
«እነዚያ /የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳን/ ያመኑትማ መልካም ሥራዎችንም የሠሩት ምንዳዎቻቸውን ይሞላላቸዋል፡፡ አላህም በዳዮችን አይወድም፡፡»አል ኢምራን 3፥57

«እነዚያማ የካዱትን ሰዎች በቅርቢቱ በመጨረሻይቱ ዓለም ብርቱን ቅጣት እቀጣቸዋለሁ፡፡ ለእነርሱም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡»አል ኢምራን 3፥56
በአገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ሙስሊም ወገኖቼ ሁላችሁ በያላችሁበት ሰላምና ጤና ከነቤተሰቦቻችሁ ይብዛላችሁ ።
እናንት ኢትዮጵያውያን ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! አባቶቻችሁና አባቶቻችን በፍቅር ህትብት ተሳስረው በደም ሐረግ ተሰናስለው ፣የዘርና የሃይማኖት አጥር ሳይገድባቸው ፍቅርን ዘርተው ፍቅርን ያሳጨዱን ከእምነትና ከተስፋ ይልቅ በፈጣሪ ፊት ታላቅ ዋጋ የሚያሰጠውን የፍቅር ሕይወት ከቃል በዘለለ በተግባር ያሳዩን የሰላም አርበኞች ናቸውና ለቀደሙት የእምነት አባቶቻችሁና አባቶቻችን ከልብ የሆነ ምሥጋናና ክብር ይግባቸዋል።

ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! በሌላው ዓለም ካለው የሙስሊም ማህበረስብ ይልቅ የእናንተ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ልባችሁ እጅግ ቅንና ርኅሩኅ የሆነ፣ከክርስቲያን ወንድሞቻችሁ ጋር በማኅበራዊ ሕይወት አብራችሁ ደፋ ቀና የምትሉ ፣ለክርስቲያን እህታችሁ በችግሯ ሰዓት ከማንም ቀድማችሁ የምትደርሱ፣የተቸገረ ምስኪን ክርስቲያን ደጃችሁ ቢቆም ዘካ ከመስጠት የማትነፍጉ ደግና ቀናዎች ናችሁና የኢትዮጵያ አምላክ ከክፉ ይጠብቃችሁ። በሕመማችሁና በችግራችሁ ሰዓት ቅዱሱን ጠበል ፍለጋ ከክርስቲያኑ ጋር ቤተክርስቲያን ገብታችሁ በፍቅር የምትጠመቁ፣ስእለታችሁ ሲደርስ ለቁልቢ ገብርኤል ድባብ ዣንጥላና የእጃችሁን አምባር አውልቃችሁ የምትሰጡ እግዚአብሔርን አክባሪ ጨዋ ማህበረሰብ ናችሁ ።

ደሴና ከሚሴ፣ ኮምቦልቻና ወልድያ ቤተክርስቲያን ሲታነጽ ድንጋይ ተሸክማችሁ አቀብላችኋል ፣ውሃ ቀድታችሁ አመላልሳችኋል። ልበ ርኅሩሆች ናችሁና በእውነት የኢትዮጵያ አምላክ ዘራችሁን ይባርክ ።በእኛ እና በእናንተ መካከል ያለውን የፍቅር ግንብ ለመደርመስና ሰላማችንን ለማደፍረስ በእምነት ስም ከባዕዳን የወረሱትን ጽንፈኝነትና አክራሪነትን ይዘው በጂኒ መንፈስ የሚሯሯጡትን ሁሉ የመርየም ልጅ አል መሲ ዒሳ ልባቸውን ይመልሰው አሜን።

ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! ዛሬ ለእናንተ ታላቁን የምስራች ቃል አድርስላችሁ ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ልቤን ከወትሮው ይልቅ እጅግ አስጨንቆታል ።ይህ ዛሬ የምትሰሙት የምሥራች ነፍሳችሁ የምትጽናናበት፣ መንፈሳቹ የሚያርፍበት፣ መዳናችሁ የሚረጋገጥበት የጽድቅ ቃል ነው።

ሁላችሁ እንደምታውቁት የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳ በድንግልና ተጸንሶ በድንግልና የተወለደ ሞትና መቃብርን ድል አድርጎ በክብር ተነስቶ በእልልታ ያረገ ድንቅ አባት ነው። ክርስቶስን የሚያምኑትና የሚከተሉት ሁሉ ታላቅ በረከትና ሰማያዊ ዋጋ እንደሚያገኙም ቁራአንና መጽሐፍ ቅዱስ በጋራ በግልጽ ይመሰክራሉ። ቁርአኑ እንዲህ ይላል
ﻭَﺃَﻣَّﺎ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﻭَﻋَﻤِﻠُﻮﺍ ﺍﻟﺼَّﺎﻟِﺤَﺎﺕِ ﻓَﻴُﻮَﻓِّﻴﻬِﻢْ ﺃُﺟُﻮﺭَﻫُﻢْ ﻭَﺍﻟﻠَّﻪُ ﻟَﺎ ﻳُﺤِﺐُّ ﺍﻟﻈَّﺎﻟِﻤِﻴﻦَ
«እነዚያ /የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳን/ ያመኑትማ መልካም ሥራዎችንም የሠሩት ምንዳዎቻቸውን/
በረከታቸው/ ይሞላላቸዋል፡፡ አላህም በዳዮችን አይወድም፡፡»አል ኢምራን 3፥57
«እነዚያንም የተከተሉህን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ከነዚያ ከካዱት በላይ አድራጊ ነኝ፡፡»አል ኢምራን 3፥55
እንግዴህ ልብ በሉ ኢየሱስ ክርስቶስን የሚያምኑትና የሚከተሉት ሁሉ ምንዳዎቻቸው የሚሞላ በትንሣኤ ዘጉባኤ ዕለት ማለትም የሰው ልጆች ሁሉ ለፍርድ በሚቆምባት በመጨረሻይቱ ሰዓት ክርስቶስን የተከተሉ ሁሉ ከካዱት በላይ የክብር ባለቤቶች እንደሚሆኑ ቁርአኑ በግልጽ መስክሯል።

እውነት ነው ክርስቶስን የሚያምንና እርሱን በእምነት የሚከተል ሁሉ በነፍሱ ዋስትና አለው ከጨለማም ወደሚደነቅ ብርሃን በክብር ይሻገራል። ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ሲል አስተምሯል ። «ልባችሁ አይታወክ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም ደግሞ እመኑ »ዮሐ 14፥1 «እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የህይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ።»ዮሐ 8፥12።

የተወደዳችሁ ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳ ወደ ዚህች ምድር ያለ አንዳች ዓላማ አልተገለጠም በእግዚአብሔር የዘለዓለም ዕቅድ ውስጥ ለሰው ልጆች የተዘጋጀውን የዘለዓለም ሕይወትና የጽድቅ ትሩፋት በጸጋ ሊያጎናጽፈን ነው።ክርስቶስ ወደ ዚህች ምድር መጥቶ ኢንጅልን/ወንጌልን/ ከመስበኩ በፊት ዓለም በተውራት/በኦሪት/ና በሙሴ ሕግጋት እግዚአብሔርን ደስ በማሰኘት ጽድቅን ለማግኘት ሞክረው ነበር ፤ሆኖም ግን አልተቻላቸውም ሁሉም ከመርገም በታች ነበሩና ጽድቃቸው ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ተቆጥሮባቸው የሰው ልጅ ሁሉ ሲሞት እድል ፈንታውና ጽዋ ተርታው ወደ ሲኦል መውረድ ነበር ።ሆኖም ግን በሰው ልጆች ሐዘንና ስቃይ የማይደሰተው ርኅሩኅና አዛኝ የሆነው ጌታ ዓለምን የፈጠረበትን ቃሉን ወደ ድንግል ማርያም ማሕጸን ልኮ ሰው ሆኖ እንዲወለድ አደረገው እርሱም ዒሳ/ኢየሱስ/ ተብሎ ተጠራ ።

የኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም የመምጣትም ትልቁ ዓላማ በሥራቸው መጽደቅ ላልቻሉ የአዳም ልጆች ሁሉ እርሱ የጽድቅ መንገድ ይሆናቸው ዘንድ ነው ።በቁርአኑ አንተን የተከተሉህን ከካዱት በላይ አድራጊነኝ የተባለለትም ለዚህ ነው ።ይህ ከድንግል ማርያም በፍጹም ተዋሕዶ ሰው ሆኖ የተወለደው ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሎ ይጠራል ለምን ቢባል በምድር እናት እንጂ አባት ሳይኖረው በመንፈስ ቅዱስ ድንቅ ግብር በተአምር ተወልዷልና እናቱ ድንግል ማርያም አባቱ እግዚአብሔር ተብሎ ይጠራል ፤ አንድም በልብ ታስቦ በአንደበት የሚገለጥ ቃል ልብ የወለደው የልብ ልጅ ይባላል ።አብ ልብ ነው፣ወልድ ቃል ነው፣መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ነው።እግዚአብሔር አንድ ነው።

ሙስሊም ወገኖቼ ብዙ ጊዜ ፈጣሪ አይወልድም አይወለድምም ስትሉ እንሰማለን ፤ነገር ግን በደንብ እንድትረዱት የምፈልገው ነጥብ ቢኖር እግዚአብሔር ልጅ አለው ሲባል በሰው የአወላለድ ሥርዓት የሚገለጥ ሳይሆን ከልብ እንደ ሚወለደው ቃል የሚመሰል ነው ።እግዚአብሔር አንድ ነው አብ በልብ ይመሰላል፣ ወልድ በቃል ይመሰላል፣ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ በእስትንፋስ ይመሰላል ሦስት አማልክት ግን አንልም አንድ አምላክ ብለን እናምናለን እንጂ ። ወልድ ከአብ ተወለደም ስንል ቃል ከልብ ተወለደ የማለት ያህል ነው።ለዚህ ነው እግዚአብሔር« ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር» ያለው ሰው ሦስት ነገር አለው ነገርግን አንድ ሰው ይባላል እንጂ ሦስት ሰው አይባልም። እያንዳንዳችን ፣ልብ ፣ቃል፣ እስትንፋስ አለን ግን ሦስት ሰዎች አንባልም አንድ ሰው ነን እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው ። አብ ፣ ወልድ ፣መንፈስ ቅዱስ ተብሎ ቢጠራም አንድ አምላክ አንድ ጌታ ነው ።( ስለ ምሥጢረ ሥላሴ ወደፊት በስፋት እንማማራለን።)

ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! ዋናው ቁም ነገሩ በሥጋ የተገለጠውን ፣በመንፈስ የጸደቀውን፣ለመላእክት የታየውን፣ በአሕዛብ የተሰበከውን፣በዓለም የታመነውንና በክብር ያረገውን ኢየሱስ ክርስቶስን በፍቅር አምናችሁ በፍቅር ትከትሉት ዘንድ ነው ይህም ለጥቅማችሁ ነው ምንዳዎቻችሁ ሁሉ ይሞላሉ፤ በነፍሳችሁም ክብርን ታገኛላችሁ መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላል «እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም»ሮሜ 8፥1 ክብር ለስሙ ይሁን ።

ኢየሱስ ክርስቶስ የነፍስ እረፍት ነው ማንም ወደ እርሱ የመጣ እንቆቅልሹ ተፈቶ፣እንባው ከፊቱ ላይ ታብሶ ፣ጨለማው ተገፎ ፣ቀንበር ተሰብሮለት በክብር ይመለሳል።ኢየሱስ ክርስቶስ የማምለጫ ዓለት ነው እርሱን ተከተሉት ከጠላት ፍላጻ በስሙ ትድናላችሁ ፣ኢየሱስ ክርስቶስ የሕይወት ውሃ ነው እርሱን ተከተሉት የጠወልገች ነፍሳችሁ በቃሉ ትለመልማለች፣ኢየሱስ ክርስቶስ መልካም እረኛ ነው እርሱን ተከተሉት በለመለመ መስክ ያሰማራችኋል ፣ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ነው እርሱን ተከተሉት ወደ ዘለዓለም ርስት ወደ አባቱ ዙፋን ያደርሳችኋል።ኢየሱስ ክርስቶስ የነፍሳችሁ ቤዛ ነው እርሱን እመኑት ጽድቅን ያለዋጋ እንዲያው በጸጋ በእምነት ትቀበላላችሁ በልጅነት ስልጣንም የመንግስቱ ወራሾች ትሆናላችሁ።

ቅዱስ መጸሐፍ እንዲህ ይላል «በልጁ የሚያምን የዘለዓለም ሕይወት አለው።»ዮሐ 3፥36
ወገኖቼ አንዳች አትጠራጠሩ ቃሉ የታመነ ነው ፤አምናችሁ ተከተሉት ተብላችኋል በእምነት ተከተሉት እርሱ በሰማያት የነፍሳችሁ ምስክር ነው ።«በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን በነፍሱ ምስክር አለው ።» ተብሎ ተጽፏል 1ዮሐ 5፥10
የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሆይ ! በኢየሱስ ክርስቶስ የማያምኑና እርሱን የማይከተሉ በምድርም ሆነ በሰማይ ብርቱ ቅጣት እንደ ሚጠብቃቸው ቁርአኑ እንዲህ ሲል በብርቱ ያስጠነቅቃል።
ﻓَﺄَﻣَّﺎ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻛَﻔَﺮُﻭﺍ ﻓَﺄُﻋَﺬِّﺑُﻬُﻢْ ﻋَﺬَﺍﺑًﺎ ﺷَﺪِﻳﺪًﺍ ﻓِﻲ ዓለምና ﺍﻟﺪُّﻧْﻴَﺎ ﻭَﺍﻟْﺂﺧِﺮَﺓِ ﻭَﻣَﺎ ﻟَﻬُﻢ ﻣِّﻦ ﻧَّﺎﺻِﺮِﻳﻦَ
«እነዚያማ የካዱትን ሰዎች በቅርቢቱ በመጨረሻይቱ ዓለም ብርቱን ቅጣት እቀጣቸዋለሁ፡፡ ለእነርሱም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡»አል ኢምራን 3፥56
ልብ ያለው ልብ ይበል! በክርስቶስ ኢየሱስ የሚገኘውን ጽድቅና የዘለዓለም ሕይወት ካወቁና ከተረዱ በኋላ እንደ ተራ ነገር በማቃለል የተፈጸመልንን የቤዛነት ሥራ ማክፋፋትና መናናቅ ብርቱ ቅጣትን በነፍስም በሥጋ ያስከትላል፤ምክንያቱም የተከፈለልን ዋጋ ከአእምሮ በላይ ነው። ጌታ ልዑለ ባሕርይውን ዝቅ አድርጎ የባሪያን መልክ ይዞ በሥጋ የተገለጠው እኛን ለማክበር ነው።ምራቅ የተተፋበት ፣በአይሁድ እጅ የተንገላታው ፣ ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ እርጥብ መስቀል ተሸክሞ 65 ጊዜ እየወደቀ እየተነሳ ለመሰቀል የሄደው፣ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪታይ ድረስ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ የተገረፈው፣የእሾህ አክሊል አናቱ ላይ ደፍቶ ፊቱ በደም ጅረት የተጋረደው አንዳችም በደልና ኃጢአት ተግኝቶበት ሳይሆን እኛ የአዳም ልጆች ስለ ኃጢአታችን ልንቀበል የሚገባውን ቅጣት እርሱ በኛ ፈንታ ተቀብሎ የእርሱን ጽድቅ ለእኛ ሊያወርሰን ነው። አንድ ጊዜ የዓለሙን ሁሉ በደል ተሸክሞ በመስቀል ላይ የታየልንና ስለ እኛ እርግማን እርሱ እንደ ተረገመ ሰው መስሎ በመስቀል ላይ የዋለው ላመኑበትና ለተከተሉት ሁሉ ሕያው የሆነ የማስታረቂያ ልመና ለማቅረብ ነው።« አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅርበላቸው» በማለት ከብርቱ ጩኽትና እንባ ጋር ጸሎትና ምልጃን ፡አቀረበ ተሰማለትም ።ዓለምን ከአብ ጋር ለዘለዓለም አስታረቀ አሁን ግን ክርስቶስ በሰማያት በክብር ዙፋኑ አለ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁትም በአብ ፊት ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል ማለትም ቀድሞ የዓለሙን ሁሉ ኃጢአት ተሸክሞ ነበር የታየልን አሁን ግን የማንንም ኃጢአት ሳይሸከም ያለ ኃጢአት ይታይልናል በመስቀል ላይ የፈጸመው የቤዛነት ሥራም እይታሰበ ዛሬም በእምነት ወደ እርሱ የሚቀርቡትን ሁሉ ሲያድን ይኖራል።ዕብ 9፥28 ክብር ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን።

የተከበራችሁ ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ! መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላል «በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመን አሁን ተፈርዶበታል።»ዮሐ 3፥18 ወገኖቼ ሆይ የመዳን ቀን ዛሬ ነው ይህንን የመዳን ጥሪ በአንድም በሌላም መንገድ እግዚአብሔር ወደ ልባችሁ ያመጣላችሁ ወገኖች ዛሬውኑኑ ወስኑ ወደ ክርስቶስ ተጠጉ በእርሱ እምኑ፣ስሙን ጠርታችሁ ተማጸኑ፣ወደ ልባችሁ እልፍኝም እርሱ እንዲገባ በእምነት በልብ ቋንቋ እርሱን ጠይቁት ዛሬ በቤታችሁ ታላቅ ደስታ ይሆናል በነፍሳችሁም የዘለዓለም ድኅነትን ታገኛላችሁ ።ይህንን የመዳን የምስራች የማይቀበሉ ግን ቁርአኑ እንዳለው ብርቱ ቅጣት ይጠብቃቸዋል መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ይላል።«በልጁ የማያምን የእግዚአብሔር ቁጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም» ዮሐ 3፥36
ሙስሊም ወገኖቼ ሆይ ቀጥሎ ያለውን ጸሎት በእምነት ሆናችሁ ጸልዩት በሕይወታችሁ ድንቅ ነገርን እግዚአብሔር ይሰራል።

« ሰማይና ምድርን ባህርና ውቅያኖስን በቃልህ የፈጠርህ የዓለም ፈጣሪ እግዚአብሔር ሆይ አንተን አምናለሁ ለአንተም እገዛለሁ፤
የሰው ልጆችን ያስተምርና ያድን ዘንድ ወደ ድንግል ማርያም ማህጸን ልከህ ሰው ሁኖ እንዲወለድ ባደረግከው በቃልህ በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ፤
እርሱንም እከተላለሁ እርሱ የጽድቅ መንገድ ነው፣እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ ቤዛ ነው፣በእርሱ ወደ አንተ ወደ እግዚአብሔር እቀርባለሁ፤
በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የልጅነት ስልጣንና የወራሽነትን ክብር በጸጋ ሰጥተኽኛልና ስምህ ለዘለዓለም ከፍ ከፍ ይበል፣
እግዚአብሔር ሆይ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ብለህ ቀንበሬን ከላዬ ላይ ስበር፣እንቆቅልሼን ፍታ፣ጨለማዬን ግፈፍ፣ታሪኬን ለውጥ፣
ከቤቴ ጣራ በታች ግባ ማዳንህንም በእኔና በቤተሰቦቼ ላይ አሳይ ክንድህን ዘርጋ በሰማያዊ በረከትም ባርከኝ ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን።»

ወድ አንባብያን ሆይ በኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነትና ፈጣሪነት ዙሪያ ከሙስሊም ወገኖቻችን የሚነሱ በርካታ ጥያቄዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ ለሚነሱት ለእያንዳናዳቸው ጥያቄዎች በሙሉ ሰፊ ማብራሪያ መልስ የሰጠሁበት ኢየሱስ ማን ነው? በሚል ርእስ ያዘጋጀሁት መጽሐፍ ስላለ ከመንፈሳዊ መጻሕፍት መደብር እየጠየቃችሁ መጠቀምና ለሚጠይቋች ሁሉ መልስ ለመስጠት ዝግጁዎች ትሆኑ ዘንድ መልእክቴን ማስተላለፍ እፈልጋለሁ።

ሙስሊም ወገኖቼም መጻሐፉን ብታነቡት ለበርካታ ጥያቄዎቻችሁ በቂ መልስ ታገኙበታላችሁ።
እባካችሁ ይህንን መልእክት ለሙስሊም ወገኖቻችን ሁሉ ሼር በማድረግ የክርስቶስ ወገን ታደርጓቸው ዘንድ በፍቅር እጠይቃለሁ።

ለበረከት ሁኑ።
ይቀጥላል

መ/ር ታሪኩ አበራ

Want your school to be the top-listed School/college in London?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address


Barking Road
London
E164HB