ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ thise is teppi tecnical vocational & educational training colege

''ተጨማሪ ሙያ ለዜጎች'' የቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከፍላጎታቸዉ በመነሳት በአጫጭር ስልጠና ዜጎችን እያበቃ ወደ ገበያው እንዲቀላቀሉ ማስቻል አንዱ ትኩረት ነው ።      ኮሌጁም ይሄንን ተግ...
08/03/2025

''ተጨማሪ ሙያ ለዜጎች''
የቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከፍላጎታቸዉ በመነሳት በአጫጭር ስልጠና ዜጎችን እያበቃ ወደ ገበያው እንዲቀላቀሉ ማስቻል አንዱ ትኩረት ነው ።
ኮሌጁም ይሄንን ተግባር ሲከውን የቆየ ቢሆንም ለሁሉም ተደራሽ ከመሆን አንፃር እና የተጨማሪ ሙያ ፍለሠጎት እያደገ በመምጣቱ ''ተጨማሪ ሙያ ለዜጎች በመረጡት ስዓት በመረጡት ሙያ'' በሚል መሪ ቃል ከ 1 ወር እስከ 3 ወር በሚደርስ ጊዜ በቀን የ3 ሰዓት በ3 ፈረቃ ለማንኛውም ዜጋ ስልጠና ለማድረስ ዝግጅቱን ጨርሷል በመሆኑም ከዚህ ቀደም ሙያ ቢኖሮትም ባይኖሮትም ወደ ኮሌጃችን በመምጣት የተጨማሪ ሙያ ባለቤት እዲሆኑ ተጋብዘዋል።

የምዝገባ ጊዜ ከመጋቢት 1 ጀምሮ በቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

በተጨማሪም በልምድ ያዳበሩትን ማንኛውንም ሙያ በምዘና በማረጋገጥ እውቅና የምንሰጥ መሆኑንም እንናረጋግጣለን።

07/03/2025
የካቲት 27/2017በ EASE ፕሮጀክት ድጋፍ ፕሮፖዛል አፃፃፍ ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ለ ቴፒ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ  አሰልጣኞች በሚዛን ካሺኒ ሆቴል እየተሰጠ ይገኛልስልጠናዉም ለተከታታይ 4...
06/03/2025

የካቲት 27/2017
በ EASE ፕሮጀክት ድጋፍ ፕሮፖዛል አፃፃፍ
ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ለ ቴፒ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች በሚዛን ካሺኒ ሆቴል እየተሰጠ ይገኛል

ስልጠናዉም ለተከታታይ 4 ቀን እንደሚቆይ እና በ አሰልጣኞች ላይ ያለዉን የ ፕሮፖዛል አፃፃፍ የክህሎት ክፍተት እንደሚሞላ የ ኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ተገኝ አየለ ተናግረዋል ።

አክለውም በቀጣይ በተለያዩ ሶፍት ስኪል በEASE ፕሮጀክት ድጋፍ ስልጠናዎችን በመስጠት ብቁ አሰልጣኞችን ለማፍራት እንደሚሰራ ገልፀዋል ።

የካቲት 26 2017public entrepreneurship ስልጠና በቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ ቴፒ ፖሊቴክኒክ ማኔጅመንት እንዲሁም ለ ክላስተር ኮሌጆች ዲኖች በEASE ፕሮጀክት እና በ EDI ...
05/03/2025

የካቲት 26 2017
public entrepreneurship ስልጠና በቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ ቴፒ ፖሊቴክኒክ ማኔጅመንት እንዲሁም ለ ክላስተር ኮሌጆች ዲኖች በEASE ፕሮጀክት እና በ EDI ትብብር እየተሰጠ ይገኛል ።

የካቲት 26 2017በ ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ EBMS ኢንተርፕነረሺፕ ስልጠና በወርልድ በንክ የሚደገፈዉ EASE ፕሮጀክት እና  በ EDI ለ ሁለት ዙር ለ ኮሌጁ እንዲሁም ከ ክላስተር ኮሌ...
05/03/2025

የካቲት 26 2017
በ ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ EBMS ኢንተርፕነረሺፕ ስልጠና በወርልድ በንክ የሚደገፈዉ EASE ፕሮጀክት እና በ EDI ለ ሁለት ዙር ለ ኮሌጁ እንዲሁም ከ ክላስተር ኮሌጆች ለመጡ አሰልጣኞች ሲሰጥ የነበረዉ የ አሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቁዋል ።

ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዲስ ሠልጣኝ ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዲስ ሠልጣኝ ተማሪ ምዝገባ መጀመሩን የኮሌጁ ምክትል ዲንና የሰልጣኞችና አሰልጣኞች አመራር ልማት ...
24/10/2024

ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዲስ ሠልጣኝ ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ

ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአዲስ ሠልጣኝ ተማሪ ምዝገባ መጀመሩን የኮሌጁ ምክትል ዲንና የሰልጣኞችና አሰልጣኞች አመራር ልማት ዳይሬክተር አቶ ተገኝ አየለ ገልፀዋል።

ምዝገባው ከጥቅምት 12/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት መካሄድ መጀመሩን አስታውቀዋል።

ማንኛውም 12ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀ ተመዝግቦ መሠልጠን የሚችል መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተገኝ አየለ በአጫጭር ስልጠናዎች ማንኛውም ዜጋ ተመዝግቦ ልሰለጥን ይችላል ብለዋል።

ለውጪ ሀገር የስራ ስምሪት መሄድ ለሚፈልጉ ዜጎች ኮሌጁ ስልጠና በመስጠትና ምዘና በማካሄድ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ ገልፀው በዚህም ዘርፍ መሠልጠን ለሚፈልጉ አካላት ዝግጅቱን አጠናቆ እየጠበቀ እንደሚገኝም አንስተዋል።

ኮሌጁ እንስሳት እርባታ፣እፅዋት ሳይንስ፣ኮምፒውተር ሳይንስ፣ልብስ ስፌትና ዲዛይን፣አውቶ መካኒክን ጨምሮ በአጠቃላይ በ12 ሙያዎች መደበኛና አጫጭር ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀዋል አቶ ተገኝ።

በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት መሆን የሚፈልግ ማንኛውም ዜጋ በተጠቀሰው የምዝገባ ቀናት በኮሌጁ ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት ተመዝግቦ መሰልጠን እንደሚችል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ዋጋ የከፈሉበት ተሳክቶ ማየት ደስታው የላቀ ነው!! ውድ የኮሌጃችን ማህበረሰቦች የቴፒ ከተማ እንድሁም የሸካ ዞን ህዝቦች እንዃን ደስ አላች ኮሌጃችን ያለውን የማደግ ተስፋ እውን የምያደርግ ...
28/06/2024

ዋጋ የከፈሉበት ተሳክቶ ማየት ደስታው የላቀ ነው!!
ውድ የኮሌጃችን ማህበረሰቦች የቴፒ ከተማ እንድሁም የሸካ ዞን ህዝቦች እንዃን ደስ አላች
ኮሌጃችን ያለውን የማደግ ተስፋ እውን የምያደርግ የአለም ባንክ ድጋፍ የምያረጋግጥ የማስጀመሪያ ደብዳቤ በዛሬው ዕለት ከስራና ክህሎት ሚኒስተር ተቀብለናል። በድጋፋ የአምስት ሚሊዮን ዶላር ወይም ETB 285 ሚሊዮን ብር የምገኝ ሲሆን በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ኮሌጁ በውጤታማነት ካጠናቀቀ እአአ በ2030 EASETRIP ውስጥ በመካተት እአአ በ2035 center of excellence በመሆን ለከተማችን ተጨማሪ ዩኒቨርሲቲ ወይም አለም አቀፍ Technical institute በመሆን በትንሹ የ East Africa ተማሪዎችን የምቀበል ይሆናል። በተጨማሪነት ፕሮጀክቱ የዞኑን tvet ኮሌጆች፣ ሴቶችን፣ ወጣቶችን እና አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ የምያደርግ ይሆናል።
Melkamu Ayele

ለቴፒ ቴክኒክና ሙያ  ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች እና መምህራን በሥራ ፈጠራ ላይ የሚያተኩር ስልጠና ሰጥቷል።ወጣቱ ትውልድ ስራ ጠባቂ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ መሆን እንዳለበት ተገለፀ ።የስራና ክህሎት...
26/04/2024

ለቴፒ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች እና መምህራን በሥራ ፈጠራ ላይ የሚያተኩር ስልጠና ሰጥቷል።

ወጣቱ ትውልድ ስራ ጠባቂ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ መሆን እንዳለበት ተገለፀ ።የስራና ክህሎት ሚንስቴር ከኢንተርፕርነር ሺፕ ዲቨሎፕመንት ኢንስቲትዩት ( EDI) ጋር በመተባበር ለቴፒ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች እና መምህራን በሥራ ፈጠራ ላይ የሚያተኩር ስልጠና ሰጥቷል።

በተቋሙ አሰልጣኝና የቢዝነስ አማካሪ የሆኑት አቶ ስንታየሁ ሽብሩ ተቋሙ ከ9 አመት በላይ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ለወጣቶች፣ለሴቶችና በተለያዩ ስራ ላይ ለተሰማሩ አካላት በስራ ፈጠራና ተያያዥ ዘርፎች ስልጠናዎችን በመስጠት ሠልጣኞች ከራሳቸው አልፎ ለሀገር እንዲበቁ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

እስከ አሁን ከ140 ሺህ በላይ ወጣቶችን ማሰልጠን መቻላቸውንም ተናግረዋል ።

አሁን ደግሞ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ውስጥ በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ስልጠናዎችን በመስጠት ተመራቂ ተማሪዎች ስራ ጠባቂ ከመሆን ወጥተው ስራ እንዲፈጥሩ እየሰሩ እንደሆነም ጠቁመዋል ።

የስልጠናው ዋና አላማ ወጣቱ ትውልድ ከስራ ጠባቂነት በመውጣት ስራ በመፍጠር ከራሱ አልፎ ለሀገር እንዲተርፍ ለማስቻል ነው ብለዋል::

ከሰልጣኞች መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት እየተሰጠ ያለው ስልጠና በተማሩት የስራ ዘርፍ ማንግሥትን ሳይጠብቁ ስራ ፈጣሪ በመሆን ከእራሳቸው አልፎ ለሀገር እንዲበቁ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ሚያዝያ 10/2016 ዓምበኢፌዴሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ልዑክ  በሸካ ዞን ቴፒ   የሚገኘውን የቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ስራዎች ተዘዋውረው ተመልክቷል።የቴፒ ...
19/04/2024

ሚያዝያ 10/2016 ዓም

በኢፌዴሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ልዑክ በሸካ ዞን ቴፒ የሚገኘውን የቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ስራዎች ተዘዋውረው ተመልክቷል።

የቴፒ ፖሊ ቴክንክና የሙያ ኮለጅ ኃላፊ የሆኑት አቶ መልካሙ አየለ በጉብኝት ወቅት እንደገለጹት የቴፒ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጁ በ2013 ዓም ወደ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተቀየረ በኋላ አግሪካልቸር፣የአግሮ ፕሮሰስንግ ዘርፎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ተግባራቶችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በሌላም በኩል ኮሌጁ በተለያዩ 10 በላይ የሙያ ዘርፎች የማስተማር ስራዎችን እየሰራ መቆየቱን በማንሳት ከትምህርት አገልግሎት ጋር ተያይዞም የመምህራን እጥረቶች መኖራቸውን አመላክቷል ።

በኢፌዲሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ እንደገለጹት የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ተቋማት በሪፎርምና አዳዲስ እሳቤዎች አኳያ መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታዎችንና ምቹ አጋጣሚዎችን በመጠቀም ለውጤታማነቱ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

አክለውም ኮሌጆች ከሚሰጡት ጠቀሜታና ከሚፈጥረው የስራ እድል አኳያ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የማምረት ምርትና ምርታማነቶችን በማጉላት እንዲሁም የእርስ በእርስ ግንኙነት አቅሞችን ማሳደግ ይኖርበታል ብለዋል።

ተቋምን በማዘመን ክህሎት መር ስልጠና ከመስጠት ጋር ያለው ጉዳይ ትኩረት የሚሻ በመሆኑ በቀጣይነት የባለድርሻ ተቋማትን ቅንጅት በማጠናከር ውጤታማ ተግባር ለማከናወን ዕቅድ መያዙን ተገልጸዋል።

የዞኑንና የክልሉን ጸጋዎች የሚመጥኑ ቴክኖሎጂዎች ከኢንተርፕራይዞች እኩል በማምረት ወደ ገበያ ማቅረብ እንዲችል ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሊሰራ ይገባል ተብሏል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር እያደረገ ያለው ጉብኝት ለየት የሚያደርገው ችግሮችን ለይቶ ይዞ መሄድ ብቻ ሳይሆን እዚሁ የመፍታት ልምድ ያለውና በጉብኝቱ የሚታዩ ችግሮች የክህሎት ስልጠና እየተሰጠ የሚሄድበት መሆኑ ነው ብለዋል።

ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በዘርፉ በርካታ ስራዎች ካሉት ምቹ አጋጣሚዎች ጋር በማስተባበር መስራትና ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ ከማድረግ አኳያ እስከታች ወርዶ ተቀናጅቶ ከመስራት አኳያ ያሉ ውስንነቶችን በጉብኝቱ መለየትና የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ እንድሰራም ተጠይቀዋል።

የቴፒ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአለም ባንክ ከሚደገፉ ኮሌጆች አንዱ መሆኑን አስመልክቶ ለኮሌጁ ማህበረሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ ።
22/12/2023

የቴፒ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአለም ባንክ ከሚደገፉ ኮሌጆች አንዱ መሆኑን አስመልክቶ ለኮሌጁ ማህበረሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ ።

ለስልጠና ፈላጊዎች
02/12/2023

ለስልጠና ፈላጊዎች

Address

Tepi

Telephone

+251475560541

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to ቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ:

Shortcuts

Share

Category