24/04/2026
የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርቲፊኬት(12ኛ) ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
Government education office page to give latest information to students and families
24/04/2026
የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርቲፊኬት(12ኛ) ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የድጋሚ ተፈታኞች (private ) ምዝገባ ስለጀመረ 03 /07/18 እስከ 10/07/2018 ዓ.ም ብቻ የሚቆይ ስለሆነ በራሳችሁ
Use register.eaes.et for G12 private student registration እንድትመዘገቡ ድጋፍ ከስፈለገ በዝህ ቁጥር 0910079101ደውላችሁ እንድታገኙ ይሁን !!
19/02/2026
02/12/2025
ወላይታ ዞን በገሱባ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ አጠቃላይ የቁ-1 እና ቁ-2 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ሱፐርቫይዘሮች፣ ር/መ/ራን፣ መ/ራን እና ትምህርት ባለሙያዎች ጋር ወቅታዊ የትምህርት ተግባራት ውጤታማነት ዙሪያ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
ገሱባ ኅዳር 23/2018 ዓ.ም ወላይታ ዞን በገሱባ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ አጠቃላይ የቁ-1 እና ቁ-2 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ሱፐርቫይዘሮች፣ ር/መ/ራን፣ መ/ራን እና ትምህርት ባለሙያዎች ጋር ወቅታዊ የትምህርት ተግባራት ውጤታማነት ዙሪያ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
✍️ፈጣን መረጅዎች ለማግኘነት የፌስቡክ ገጽያችን በመወዳጀት ይከታተሉ Like share አይዘነጉ!
21/11/2025
የሀዘን መግለጫ
የገሱባ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አጋፋው ጂኦግራፊ መ/ር ምንተስኖት አረጋ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን፡ለሥራ ባልደረቦቻቸው ፣ለተማሪዎቻቸው እና ለቤተሰብ ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን፡፡
20/11/2025
በገሱባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ትምህርት ዘመን የእስካሁን አፈጻጸምና ቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ከተማዊ መድረክ እየተካሄደ ነው
ገሱባ ከተማ ፤ህዳር 11/2018 በወላይታ ዞን የገሱባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ትምህርት ዘመን የእስካሁን አፈጻጸምና ቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ያተኮረ ከተማዊ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የገሱባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 ትምህርት ዘመን የእስካሁን አፈጻጸም ሪፖርት ካቀረበ በኃላ ቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በመድረኩ የከተማ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወ/ሪት ፀጋነሽ እስጢፋኖስ፤ የገሱባ ከተማ አስተዳደር የከንቲባ ተወካይ ዋና አፌ-ጉባኤ አቶ ዘካርያስ ዋቤቶ ጨምሮ የከተማ አጠቃላይ አመራር እና የትምህርት ባለሙያዎች እንድሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ናቸው።
18/11/2025
በዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መረጃ መያዝና አገልግሎት መስጠት ብልሹ አሰራርን የሚከላከልና የአገልግሎት አስጣጥ ችግሮችን የሚፈታ መሆኑ ተገለፀ ።
ዲጂታለይዜሽን አስራርን በመጠቀም ከዚህ በፊት በትምህርት ዘርፍ የነበረውን የመረጃ አሰባሰብ እና አደረጃጀት ችግር የሚፈታ ታማኝነት እና ወቅቱን የጠበቀ የመረጃ ሊዉዉጥ ሥርዓት መንግስት እንዳመቻቸ የገሱባ ከተማ አስተዳደር ትም/ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈቃዱ ጊቦን ገለጹ።
በመሆኑም ዛሬ ህዳር 09/2018 ዓ/ም በገሱባ ከተማ አስ/ር ሥር ላሉ ለሁሉም መንግስት እና ግል ትምህርት ቤቶች ር/መ/ራን፣ሱ/ሮች እና ለትም/ት ባለሙያዎች የዲጂታላይዘሽን ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
30/10/2025
የገሱባ ከተማ አስ/ር ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት 2018 ዓ/ም የ1ኛ ሩብ ዓመት የትም/ት ሥራ አፈጻጸምን ግምገማ አካሄዷል።
ገሱባ፣ጥቅምት 20/2018 ዓ/ም የገሱባ ከተማ አስ/ር ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት የ1ኛ ሩብ ዓመት የትም/ት ሥራ አፈጻጸምን ግምገማ አካሄዷል።
በመድረኩም ላይ የትምህርት ባለሙያዎች ፣ሱ/ሮች እና ር/መ/ራን የተገኙት ሲሆን በ1ኛ ሩብ ዓመት ትምህርት ቤቶች መስክ ምልከታ ጊዜ የተገኙ ጠንካራና መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮችን ትኩረት በማድረግ በጥልቀት ለመገምገም ተችሏል።
በዋናነት የትምህርት አመራር እና መ/ራን ከምንም ጊዜ በላይ ለመማር ማስተማር ስራ ትኩረት በማድረግ ሀገር አቀፍ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በጊዜ የለኝም መንፈስ መስራት እንዳለበት መግባባትን መፍጠር ተችሏል።
በመጨረሻም በሩብ ዓመት አፈጻጸም የተሻለ ተግባር ያላቸውን በማበረታታት እና እንደ ድክመት የተመዘገቡትን በማረም ግምገማውን ማጠናቀቅ ተችሏል።
07/10/2025
ማስታወቂያ
የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብን ስለማሳዎቅ
ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የ Remedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን እናሳውቃለን።
1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን።
2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ።
30/09/2025
09/08/2025
እንኳን ለ2018 በጀት ዓመት ትምህርት ዘመን በሠላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን‼
በገሱባ ከተማ አስ/ር የ2018 የትምህርት ዘመን ከቅድመ-አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ያለው የተማሪ ምዝገባ/ ከነሐሴ 5/ 2017 ጀምሮ እስከ ነሐሴ 23/2017 ዓ/ም ድረስ የሚካሄድ ስለሆነ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጅ ከወዲሁ በቂ ዝግጅት በማድረግ ተማሪዎች እንዲትመዘገቡ እናሳውቃለን ።
የተማሪዎች ምዝገባ በሁሉም መንግስትና ግል ትምህርት ቤቶች የሚጀምር ስለሆነ የትምህርት ባላድርሻዎች፣ ወላጆች እንዲሁም ህብረተሰቡ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ምዘገባ በማድረግ ከነዚህ ቀናት ቀድሞም ሆነ ዘገይተዉ የሚመጣ ተማሪም ሆነ የሚያመጣ ወላጅ እንደማናስተናግድ አጥብቀን እናሳውቃለን ።
አንድም ህጻን ከትምህርት ገበታ ዉጪ አይሆንም!!
ነሐሴ 3/2017 ዓ.ም
የገሱባ ከተማ አስ/ር ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት