አስደሳች ዜና ለት/ት ፈላጊዎች በሙሉ
በ2018 ዓ/ም የት/ት ዘመን በኮሌጃችን በመጀመሪያ ዲግሪ በሚከተሉት ፕሮግራሞች በማታና በሳምንት መጨረሻ ከፍለው ለመማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ምዝገባ የተጀመረ መሆኑን እየገለጽን ለበለጠ መረጃ የዪኒቨርሲቲውን ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት፣ የተከታታይ ት/ት ዳይሬክቶሬት ወይም ት/ት ክፍሉን በቀጥታ ማናገር የሚቻል መሆኑን በደስታ እንገልጻለን።
1. ኢኮኖሚክስ
2. ማኔጅመንት
3. አካውንቲንግና ፋይናንስ
4. ማርኬቲንግ ማኔጅመንት
5. የሕዝብ አስተዳደር
6. ቱሪዝምና ሆቴል ማኔጅመንት
በተጨማሪም በሁለተኛ ዲግሪ NGAT ያለፉ ተማሪዎችን በሚከተሉት ፕሮግራሞች ተቀብለን ለማስተማር ሙሉ ዝግጅታችንን የጨረስን መሆኑንም በደስታ እንገልጻለን።
1. MBA (Masters of Business Administration)
2. MSC in Economics with various Specializations
3. MSC in Accounting and Finance
4. MA in Project Management
5. MA in Marketing Management
6. MA in Development Management
College of Business and Economics Wolaita Sodo University
The purpose of this page is to share educational information for UG and PG students.
ውዶች
እንኳን ለ2018 ዓ/ም የት/ት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያልን ኮሌጃችን የመማር ማስተማር፣የምርምርና የማህበረሰብ ጉድኝት ሥራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ ለማከናወን ሰፊ ዝግጅት አድርጎ ወደ ሥራ የገባ መሆኑን መግልጽ እንወዳለን።
09/05/2025
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ
የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በመደበኛ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ-ግብር ከዚህ በታች ባሉት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።
1. MA in Development Management
2. Masters of Business Administration
3. MSc in Accounting and Finance
4. MA in Marketing Management
5. MA in Project Management
6. MSc in Economics (with specialization)
o Economic Policy Analysis
o International Economics
o Development Economics
ማሳሰቢያ፦ ለ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ሴሚስቴር የትምህርት ዘመን ምዝገባ NGAT ላለፉት እስከ 26/07/2017 ዓ.ም ተብሎ የነበረ ቢሆንም ፍላጎት ያላችሁ ወደ ት/ት ክፍሎች ወይም ሬጅስትራር በመቅረብ ማመልከት የሚትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
02/02/2025
08/01/2025
#ማስታወቂያ
28/12/2024
የቀድሞ የኮሌጃችን ዲን መ/ር ዘገዬ ጳውሎስ ለAC አባላት ያስተላለፉት የምስጋና መልዕክት🙏
-----------------------------------
"የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን (AC) አባላት ዛሬ ቅዳሜ በቀን 19/04/2017 ዓ.ም ወደ ሌላ ተቋም ሥምሪት ወስጄ መመደበን መነሻ በማድረግ በተደረገልኝ የሽኝት ፕሮግራም በጣም ተደስችያለሁ።
ከኮሌጃችን AC አባላት ጋር ባለፉት ስድስት አመታት የኮሚሽኑ አባልና ጻሐፊ በመሆን እና ከህዳር 27,2015 ዓ.ም ጀምሮ የኮሌጅ ዲን በመሆን ኮሚሽኑን በሰብሳቢነት በመራሁበት ጊዜያት ከእናንተ ውድ የኮሌጅ አመራሮች እና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር በርካታ ሥራዎችን በመማር ማስተማር ፣በምርምር ፣በማህበረሰብ አገልግሎት፣በመምህራን ልማት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር አንጻር የመምራትና የመወሰን ዕድል አግኝቼ በመሥራቴ ትልቅ ኩራት እና ደስታ ይሰማኛል።
በቆየሁባቸው የኃላፊነት ዘመናት ከእናንተ የረጂም ጊዜ የስራና የህይወት ልምድ ካላችሁ ጓደኞቼ ጋር በመስራቴ አሁን ለተመደብኩበት ተቋም ሆኔ ለቀጣይ ሕይወቴ ስንቅ ልሆን የሚችል ዘመን ተሻጋሪ እውቀትና ልምድ ከማገኘቴም በተጨማሪ በኃላፊነት ዘመኔ ለመራሁት ኮሌጅ ስኬተማነት የአንበሳውን ድርሻ የሚትወስዱት እናንተ የAC አባላት ናችሁ:
በዚህም መሠረት ዛሬ በቀን 19/04/2017 ዓ.ም በሽኝት ፕሮግራም ላይ የተገኛችሁ ውድ የAC አባላት እና ቅርብ ጓደኞቼ ላደረጋችሁልኝ ከፍ ያለ ሽኝት እና ላሳለፍናቸው ስኬታማ ጓዞዎችን ከልብ እያመሰገንኩኝ መልካም የሥራ ጊዜ እንድሆንላችሁ እመኛለሁ።"
ውድ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ መምህራን እና አስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ🙏
-----------------------------------
ባለፉት ረጅም አመታት በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች በተለይም በኮሌጅ ምክትል ዲንነት ሁለት ዙር እና ከህዳር 27,2015 ዓ.ም ጀምሮ የኮሌጅ ዲን በመሆን ከእናንተ ከወጣት ምሁራን ጋር የመሥራት፣የማስተማር እና የማገልገል ዕድል አግኝቼ በመሥራቴ ትልቅ ኩራት እና ደስታ ይሰማኛል።
በዚህም መሠረት በቆየሁባቸው የኃላፊነት ዘመናት እምቅ እውቀታችሁን እና ክህሎታችሁን ለተቋም ራዕይ ስኬት ስታዋጡ የነበራችሁ ከወጣት ምሁራን እስከ የረጂም ጊዜ የስራና የህይወት ልምድ ካላቸው የኮሌጅ እና የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ጋር በመስራቴ ዘመን ተሻጋሪ እውቀትና ልምድ ከማገኘቴም በተጨማሪ በኃላፊነት ዘመኔ ለመራሁት ኮሌጅ ውጤታማነት ደግሞ የአንበሳውን ድርሻ የሚትይዙት እናንተ የሥራ እና የሙያ ባልደረቦቼ ናችሁ፡
በመሆኑም ከታህሳስ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከእናንተ ጋር በነበርኩበት ዘመን የቀሰምኩትን እውቀትና ልምድ ተጠቅሜ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንዱስትሪ ልማት ጉዳዮች አማካሪ በመሆን ህዝባችን፣ ክልላችንን እና ሀገርን የማገልገል ዕድል የተሰጠኝ ስለሆነ አብረን በነበርንበት ዘመን ላደረጋችሁልኝ ድጋፍ ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ።
ዘገዬ ጳውሎስ ቦርኮ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Telephone
Website
Address
Gandaba
S**o