10/12/2025
𝐆𝐢𝐟𝐚𝐚𝐭𝐚𝐚 𝐅𝐞𝐬𝐭𝐢𝐯𝐚𝐥 𝐈𝐧𝐬𝐜𝐫𝐢𝐛𝐞𝐝 𝐨𝐧 𝐔𝐍𝐄𝐒𝐂𝐎’𝐬 𝐈𝐧𝐭𝐚𝐧𝐠𝐢𝐛𝐥𝐞 𝐂𝐮𝐥𝐭𝐮𝐫𝐚𝐥 𝐇𝐞𝐫𝐢𝐭𝐚𝐠𝐞 𝐋𝐢𝐬𝐭
Gifaataa, the New Year festival of the Wolaita people, has been inscribed on the Representative List of the Intangible Cultural Heritage of Humanity during the 20th Session of the Intergovernmental Committee for the Safeguarding of the Intangible Cultural Heritage, currently taking place in New Delhi, India.
During the session, Minister of Tourism, Selamawit Kassa, delivered a statement highlighting the importance of preserving and promoting this valued heritage.
Passed down through generations, Gifaataa marks the transition from the old year to the new and holds deep cultural significance for the Wolaita community.
25/09/2025
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የዎላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር
10/07/2025
በወላይታ ሶዶ ከተማ የደረጃ "ሐ" የግብር አሰባሰብ እና የ2018 የንግድ ፍቃድ እድሳት በሌሎችም የንቅናቄ ተግባራት ዙሪያ ዕለታዊ ዕቅድ አፈጻጸም ተገመገመ
ወላይታ ሶዶ ሐምሌ 3/2017 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ የደረጃ "ሐ" የግብር አሰባሰብ እና የ2018 የንግድ ፍቃድ እድሳት በሌሎችም የንቅናቄ ተግባራት ዙሪያ ዕለታዊ ዕቅድ አፈጻጸም አስተባባሪዎች፣ የቀበሌ ደጋፊ አመራሮች በተገኙበት ተገምግሟል።
በአፈፃፀም ግምገማው በከተማው የ"ሐ" ግብር አሰባሰብ እና የተለያዩ የገቢ አሰባሰብ የተከናወኑ ስራዎች፣ ከውስጠ ፓርቲ አኳያ የተከናወኑ ስራዎች፣ የኢንተርፕራይዝ ዕዳ አመላለስ፣ የውዝፍ ማዳበሪያ ዕዳ አመላለስ፣ የሰንበት ገበያ ከማጠናከር አኳያ የተከናወኑ ስራዎች፣ የወላይታ ዲቻ ድጋፍ የሀብት አሰባሰብ ስራዎች፣ በአጠቃላይ በቀበሌው በልማትና የመልካም አሰተዳደር ጉዳዮችን ላይና በቀጣይ በቀሪ ጥቂት ቀናት ለተግባራት መሳካት የህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሻለ መግባባት መፈጠር እንደሚገባ በመድረኩ ተገንዝበዋል።
በህዝብ ዘንድ የሚነሱ መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በፍጥነት፣ በጥራትና በጊዜ የለንም ስሜት ለመፍታት በቅንጅት መስራት እንዳለበት ከመድረኩ ተገልጿል።
በተላይ አሁን እየተከናወነ ያለው የ"ሐ" የግብር አሰባሰብ እና በፓርቲ ስራ ላይ በጥንካሬ የተስተዋሉ ተግባራትን አስፍቶ ማስቀጠል፤ ጉድለት የታየባቸውን አፈጻጸም ፈጥኖ በማረም በሚፈለገው ደረጃ ማድረስ የመድረኩ የትኩረት አቅጣጫ እንደሆነ እና መሬት ላይ ያለዉን ተግባር ወርዶ ምልከታ እንደሚደረግ ተገልጿል።
በለውጡ ጊዜ ምንም ያለምህረት የሚወስዱ እርምጃዎች መካከል የህገወጥ ግንባታ፣ አገልግሎት አሰጣጥ ችግር እና የመልካም አስተዳደር ችግር ላይ እጃቸውን ያሉ የተኛው ግለሰቦች ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወስዶ ተግባሩ እንደሚቀጥል ከመድረኩ በጥብቅ ተነስቷል።
በመጨረሻም ''አመራሩ ከተሰጠው በላይ መስራት ከሚጠበቅባቸው በላይ መፈፀም'' እንዳለበት በመድረኩ ተነስቶ ለቀጣይ ጥቅት ቀናት ተግባራትን በእኩል ሚዛን ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት አቅጣጫ ተቀምጧል።
10/07/2025
ከ550BC ጀምሮ የዎላይታ ብሔር የሚጠቀምበት የዘመን አቆጣጠር(Calandar)
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
የዎላይታ ጊዜ አቆጣጠር በጨረቃና በፀሐይ(Lunosolar) የሚሰላ እንደሆነ ጥናቶች በጠቁሙም ጥንት ዎላይታ ጀምሮ በጨረቃ እንደሚቆጠር ይታወቃል።
የአንድ ቀን(24 ሰዓት) ክፍፍል
Bakkaaliyaa 12:00 AM
Maallado 12:00-1:00 AM
Guuraa 1:00-4:00 AM
Poo7o 4:00-6:00 AM
Gallaassaa 6:00-9:00 AM
Omarissaa10:00-12:00 AM
Lenkkilenkkaa12:00-1:00 PM
Qammaa 2:00-6:00 P፡ተ
bilahiyaa 6:00-7:00 PM
henqelleelaa 7:00-8:00 PM
Hekka blahiyaa 9:00-10:00 PM
Jaabbiyaajooraa 9:00-10:00 PM
Wonttimaattaa 11:00-12:00 PM
የአንድ ወር( 30 ቀን/በአራት ገበያ) ክፍፍል
Koyro giya-Xuma ceggenaa ወሩ በገባ የመጀመሪያው ሳምንት
Naa77antto giya-Xeero ceggennaa ወሩ በገባ በሁለተኛው ሳምንት
Heezzantto gita-Poo7o ceggennaa ወሩ በገባ በሶስተኛው ሳምንት
Oydantto giya-Goobana የወሩ የመጨረሻው ሳምንት
የአንድ ዓመት (በአራት ወቅቶች/12 ወራት) ከፍፍል
አራት አንኳር ወቅቶች
Ofinttaa
Boniyaa
Badhdheesa
Balgguwaa
12 ወራት
1. Gifaata➢መስከረም
2. Gooluwaa➢ጥቅምት
3. Baraataa➢ህዳር
4. Duubbalaa➢ታህሳስ
5. Shachchaa➢ጥር
6. Longgiyaa➢የካቲት
7. Bullaalaa➢መጋቢት
8. Gabbaa➢ሚያዚያ
9. Laabooshaa➢ግንቦት
10. Guuliyaa➢ሰኔ
11. Caljjuwaa➢ሐምሌ
12. Kuushshaa➢ነሐሴ
13. Nucho - ጳጉሜ
02/06/2025
በኢትዮጵያ ከአክሱም ታቦተ ጺዮን ቀጥሎ ረጅም አመት ያስቆጠረው በደቡብ ኢትዮጵያ ቀዳሚው #ከዎላይታው #ንጉሥ ካዎ ሳቶ ሞቶሎሚ እስከ ሰሜን ሸዋ ድረስ የገዛው በሱ ዘመን
ጻዲቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ባለ ስድስት ክንፉ ወንጌል ሀ ብለው መስበክ የጀመሩት 800 ዓመት በላይ የሞላው ቦታ በታላቅ ድምቀት በኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ለዎላይታ ህዝብ ልዩ ጥቅምና ዝና አጎናጽፎ ተመርቋል።
07/05/2025
በወላይታ ሶዶ ከተማ ከጊዜ ወደ ጊዜ በተጨባጭ እየታየ የመጡ ለውጦች በምኞት የተገኙ ሣይሆኑ መላውን የከተማችንን ነዋሪዎች በማሳተፍ በየወቅቱ የመጡና የተፈራረቁ ቁርጠኛ አመራሮች የማስተባበር ውጤት ናቸው" ዶ/ር ፍሬው ሞገስ
*******
ወላይታ ሶዶ ሚያዝያ 29/3017 የወላይታ ሶዶ ከተማ የልማትና የመልካም አስተዳደር ህዝባዊ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ፍሬው ሞገስ ሁላችሁንም እንኳን በከተማ አቀፍ የሰላም የልማትና መልካም አስተዳደር ጉባዔ እንኳን በደህና መጣችሁ ያሉት ከንቲባው የሶዶ ከተማ አስተዳደር ራሱን ችሎ የከተማ አስተዳደር ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ አስካሁን ድረስ በተጓዘባቸው ውጣ ውረዶች ያስመዘገባቸው ስኬቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ በተጨባጭ እየታየ የመጡ ለውጦች እንዲሁም በምኞት የተገኙ አይደሉም ያሉት ከንቲባው መላውን የከተማችንን ነዋሪዎች በማሣተፍ በየወቅቱ የመጡና የተፈራረቁ ቁርጠኛ አመራሮች የአመራርና የማስተባበር ውጤት ናቸው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ከተማችን ዛሬ የደረሠችበት ደረጃ ስትደርስ እርስበርሣችን የነበረው አንድነት አንደተጠበቀ ሆኖ ከአንድነታችን ባልተናነሰ መልኩ ባለፉት ጊዜያት በየወቅቱ እያደገ የመጣውን የህዝባችንን የመልማትና የማደግ ፍላጐት የሚያቀጭጩ አለመግባባቶች ተስተውለዋል ያሉት ከንቲባው እነዚህን አለመግባባትና አለመደማመጥ ክስተቶች ከማንም በላይ የጐዱት ህዝባችንን ብቻ ነው ብለዋል፡፡
የዚህ ታላቅ ጉባኤ ዓላማም እንደከተማችን እንደ አጠቃላይ፤ እንደህዝብም የጐዳንን ይህንን ስንኮፍ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅሎ በመጣል ሁላችንም እንደ አንድ እጅ ለእጅ ተያይዘን የአንዳችንን ስህተት ሌላችን እያረምን አንተ ትብስ አንቺ ትብስ በመባባል ከተማችንን ብሎም ህዝቦቿን በልማትና መልካም አሰተዳደር እምርታ እንድታስመዘግብና የጋራችንን ቤት በጋራ ተባብሮ መሥራት ዓላማ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ጥላቻንና _ መገፋፋትን ወደ ጐን በመተው መከባበርን፤ወንድማማችነትንና ህብረትን ማጠናከር ይጠበቅብናል ሲሉም መክረዋል፡፡
26/04/2025
ወላይታ ድቻ በኢትዮጵያ ዋንጫ ለፍጻሜ አለፈ
በኢትዮጵያ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ወላይታ ድቻ ሸገር ከተማን 2 ለ 0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ወደ ፍጻሜ ማለፉን አረጋግጧል፡፡
ወላይታ ድቻ ለቀጣዩ የውድድር ዓመት ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ያደገውን ሸገር ከተማን ባሸነፈበት ጨዋታ ዘላለም አባተ እና ብዙዓየሁ ሰይፈ የማሸነፊያ ግቦችን አስቆጥረዋል፡፡
ወላይታ ድቻ ድሉን ተከትሎ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታቸውን ከሚያደርጉት መቻልና ሲዳማ ቡና አሸናፊ ጋር በፍጻሜው ይፋለማል፡፡
በተመሳሳይ ባለፈው ዓመት የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ የነበረው ወላይታ ድቻ በፍጻሜው በኢትዮጵያ ቡና ተሸንፎ ዋንጫውን ማጣቱ ይታወሳል፡፡
በኢትዮጵያ ዋንጫ ሻምፒዮን የሚሆነው ክለብ በቀጣዩ ዓመት የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ላይ ተሳታፊ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
እንኳን ደስ አላችሁ! ደስ አለን!
21/04/2025
ዎላይታ👉 መቼስ ከፈጣሪ የተቸረን ማሰብያችን እኛው ጋር ካለ የተከበሩ አቶ ጴጥሮስ ወልደማርያም ወደ ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት የዞናችን ነባራዊ ሁኔታ ምን እንደ ሚመስል በሚገባ እናውቃለን!!
👉በተለይ በተከታታይ ሶስት የዞን አስተዳዳሪዎች መመለስ ያልቻሉት የዎላይታ ዞን የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ በወቅቱ ያለመግባት ችግር በዘላቂነት እና በአጭር ግዜ ውስጥ ዕልባት ያገኘው በእርሳቸው ቆራጥ አመራር ነው!! በዚህም በርካታ የመንግስት ሰራተኞች ለከፋ አደጋ ከመጋለጣቸው አልፈው አሁን ላይ ወደ ቀድሞ ኑሯቸው መመለስ ችለዋል!!
👉የሰፊው ህዝባችን የዘመናት ጥያቄ ሆኖ የቆየው የዎላይታ ሶዶ ኤርፖርት (ሱማሜ ) አየር ማረፍያ በርካታ ውስብስብ ችግሮቹ ተፈተው ገንባታው እንዲጀመር የተደረገው በእርሳቸው የአመራርነት ግዜ ከመሆኑም በላይ ግንባታው በሚገባው ፍጥነት እንዲሄድ ከፍተኛ ክትትል በማድረግም ላይ ናቸው!!
👉ከሌዊ ግብርና ኮሌጅ የአስፓልት መንገድ ከፖለቲካ ፍጆታ አልፎ ወደ ተግባር እንቅስቃሴ የተገባውም በርሳቸው ግዜ እና በቆራጥ አመራርነታቸው ነው!! በሂደት ላይ ያሉ ብርካታ ልማቶችም እንዳሉ ልብ ማለት ያስፈልጋል!!
👉ድመት ድንገት ሲርባት ልጆቿን ቅርጥፍጥፍ አድርጋ ትበላለች አንድ አንድ የተራባችሁ የኛ ቤት አክቲቪስቶች የራሳችሁን ሰው የታላቁን የዎላይታን ህዝብ መሪ በልታችሁ መጎበዝ አሰባችሁ? እታገልለታለሁኝ የምትሉትን ታላቁን የዎላይታን ህዝብ ባህል ወግ እንዲሁም እሴት በትንሹ እንኳን የማታውቁ ከንቱዎች!!
ጥ ቅ መ ኞ ች_ተ ረ ጋ ጉ!!
በ Habtamu Endrias
24/03/2025
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጎሮቤታችን የሆነችውን ጁቡቲን 6v1 በሆነ በሰፊ ውጤት አሸነፈች።
🇪🇹ኢትዮጵያ 6 v 1 ጅቡቲ 🇩🇯