31/03/2023
መጋቢት 18/2015 ዓ/ም
ወላይታ ሶዶ
የደቡብ ክልል ትም/ቢሮ በ2014 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ስብራት መንስዔዎችና መፍትሄዎች ላይ በወላይታ ሶዶ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የንቅናቄ መድረክ ተጠናቀቀ።
በዕለቱ በክልሉ ም/ር/መ/ማ/የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትም/ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያጋጠመውን የት/ት ስብራት መንስዔዎችና መፍትሔዎች በተመለከተ ሰነድ ቀርቧል፡፡ በቀረበውም ሰነድ ላይ ውይይት ከተደረገ በኋላ ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የዕለቱ ክቡር እንግዳ የክልሉ ር/መስተዳደር አቶ ርስቱ ይረዳው ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም በ2014 የት/ት ዘመን በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና በክልሉ ውስጥ በት/ት ዘመኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ትም/ቤቶች የማበረታቻ ሽልማትና የዕውቅና ሠርተፊኬት ተበርክቶላቸው የንቅናቄው መድረክ ተጠናቋል።
የቢሮው መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት