27/05/2026
እንኳን ለ1447ኛው ኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌙
===================
የተከበራችሁ መላው የኮሌጃችን አካዳሚክ፣ አስተዳደር እና ክሊኒካል ባልደረቦቼ፣ ተማሪዎቻችን፣ በሕክምና ላይ የምትገኙ ታካሚዎቻችን እንዲሁም ደንበኞቻችን በሙሉ፤ እንኳን ለኢድ አል-አድሃ በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ! አደረሰን!
ኢድ አል-አድሃ የመስዋዕትነት፣ የመታዘዝ፣ የርህራሄ፣ የፍቅር እና የእርስ በርስ የመረዳዳት ታላቅ በዓል ነው።
የበዓሉን መልካም እሴቶች ጠብቀን የምናከብረው እንዲሆንልን እየተመኘሁ፤ በተለይም በዚህ የበዓል ቀን በሥራ ገበታችሁ ላይ በመገኘት ሕሙማንን ለምትንከባከቡ የጤና ባለሙያዎቻችን በሙሉ የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። በሕክምና ላይ ለሚገኙ ወገኖቻችንም ፈጣን ፈውስን እመኛለሁ።
✨ ኢድ ሙባረክ! ✨
ዶክተር ወኪል ወልዴ
በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር።
ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም.
21/05/2026
#62ኛው ዓለም አቀፍ #የነርሶች ቀን በድምቀት ተከበረ
===========
“ነርሶችን ማክበር ሕይወትን ማዳን ነው '' Empowered Nurses Save Lives'' በሚል መሪ ቃል 62ኛው ዓለም አቀፍ የነርሶች ቀን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ተከብሯል።
==================
በመድረኩ የተገኙት በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ወኪል ወልዴ፣ ነርሶች የጤና ሥርዓቱ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ገልጸዋል።
ዕለቱ የተከበረው የነርሶችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በመገንዘብና ለሚያበረክቱት አገልግሎት ዕውቅና ለመስጠት መሆኑንም ጠቁመዋል ዶክተር ወኪል ።
አክለውም፣ ነርሶች በሥራቸው ውስጥ ብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ቢያሳልፉም፥ በሚያደርጉት ድጋፍና እርዳታ ከሞት የሚተርፉ ሕሙማንን ማየት ትልቅ ደስታ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
የጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ፥ የጤና ትምህርትና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር ታከለ ተክሉ (ፒ.ኤችዲ) በመዝጊያ ንግግራቸው ፥ከ1952 ዓ.ም ጀምሮ ሙያውንና ሞያተኞችን አክብሮ ና ደግፎ የቆየውን ማሕበሩን አመስግነው፥ ለማሕበሩና ለነርሶች አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ቃል እንገባለን ብለዋል
በሆስፒታሉ የጤና አገልግሎት ምክትል ኮርፖሬት ዳይሬክተር ዶክተር ተገኝ ባሼ በበኩላቸው፣ ነርሶች ለታካሚዎች በትጋት የሚያደርጉት ርኅራኄ፣ ክብካቤና እገዛ ለጤና ሥርዓቱ ቁልፍ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
62ኛው ዓለም አቀፍ የነርሶች ቀን በፓናል ውይይት፣ በትጋት ለተለዩ ነርሶች ዕውቅና በመስጠት ፣በደም ልገሳ፣ በታካሚዎች ጉብኝት፣ በጤና ትምህርት እና በጽዳት መርሃ ግብሮች ተከብሯል።
በመድረኩ የተለያዩ ሀሳቦች፣ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በፕሮግራሙም የማኔጅመንት አባላት፣ ነርሶች፣ ተማሪዎች እና ሌሎች እንግዶች ተሳትፈዋል።
#የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት
ግንቦት 13/2018 ዓ.ም.
16/05/2026
በድኅረ ማርቨርግ ቫይረስ ክትባት ምርምር ሂደት ላይ የባለድርሻ አካላት ውይይት መድረክ ተካሄደ
አርማውር ሐንሴን ምርምር ኢንስቲትዩት ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በድኅረ ማርቨርግ ቫይረስ ክትባት ምርምር ሂደት ዙሪያ የባለድርሻ አካላት ውይይት አካሂዷል።
በመድረኩ የማርቨርግ በሽታ ምላሽ ሂደት የተደረጉ ጥረቶች፣ የተገኙ ተሞክሮዎች፣ የሕብረተሰብ ተሳትፎ እና የባለድርሻ አካላት ሚና ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ተሳታፊዎችም የምርምር ሥራዎች በመንግሥትና በባለድርሻ አካላት ድጋፍ ሊጠናከሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።
“ዕውቀትን በተግባር!”
የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት
ግንቦት 08/2018 ዓ.ም
09/05/2026
ለአቶ ኢሳያስ አቦ #በጡረታ የክብር ሽኝት ተደረገላቸው ።
============
አቶ ኢሳያስ አቦ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ማኔጅመንት አባል፥ ከተቋሙ በጡረታ በክብር ተሸኙ።
ማኔጅመንት አባላትና የሽኝቱ ታዳሚዎች መልካም ሥነምግባራቸውን ፣ትጋታቸውንና የሥራ ተነሳሽነታቸውን ገልጸው ፤ በቀሪ ዘመናቸው ሁሉ መልካም እንዲገጥማቸው ተመኝተዋል።
አቶ ኢሳያስ አቦ በበኩላቸው ፦ከማኔጅመንቱ ጋር የነበራቸው ቆይታቸው መልካም እንደሆነ ገልጾ ፤
4ዐ ዓመት ሙሉ በሥራ ዓለም ሲቆይ የረዳኝና ሞገስ የሰጠኝን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ ብለዋል።
በመጨረሻም የተቋሙ አመራሮች እንዲሁም መላው ስታፍ ላሳየኝ ፍቅርና እና ክብር ሽኝት ልባዊ ምሥጋና አቀርባለው ብለዋል ።
ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት
ግንቦት 1/2018 ዓ.ም
08/05/2026
_ማስታወቂያ #የሬዚዳንት #ተማሪዎች #ምዝገባ ቀን ፤
=============
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ሬዚዳንት ሀኪሞች የምዝገባ ቀን.ግንቦት 👇........መሆኑን እናሳውቃለን 👇
07/05/2026
እንኳን ለዓለምአቀፉ ሚድዋይፎች ቀን አደረሳችሁ!
Day of , 2026
========
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ
ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
ዓለምአቀፉ የሚድዋይፎች ቀን በድምቀት ተከበረ።
- -—------------------------
በዓሉ "ዓለማችን #1ሚሊዮን፥ ሀገራችን ደግሞ
ሃያ ሺህ " #ሚድዋይፎችን ትፈልጋለች በሚል መሪ ቃል ነው የተከበረው።
በሚድዋይፎች ላይ ኢንቨስት እንዲደረግ የተጠየቀ ሲሆን፤ መንግስታትና አጋር ተቋማት ሚድዋፎችን በመቅጠር፣ በማብቃት፣ በማበረታታት እና በመደገፍ የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናት ጤና እንዲሻሻል በትኩረት ሊሠራ ይገባልም ተብሏል በመድረኩ ።
የጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ የጤና ትምህርትና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር ታከለ ተክሉ(ፒ.ኤችዲ) እንዲሁም የጤና አገልግሎት ምክትል ኮርፖሬት ዶክተር ተገኝ ባሼ ዕለቱን አስመልክተው ንግግር አድረገዋል ።
ረ/ፕሮፌሰር ተክሉ ማረማ መምህርና የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማሕበር ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ አባል ሀገራዊና አህጉርአዊ የዘርፉን ጥናታዊ መረጃ ለታዳሚዎች ገለፃ ያደረጉት ሲሆን፤ በዘርፉ የተሠሩ አውንታዊ ሥራዎችና ተግዳሮቶች ተዳስሷል።
ሲ/ር ምሥጥራዊት ቀድራላ በደቡብ /ኢትዮጵያ ክልል የማሕበሩ ፕረዚዳንት ፣ መምህራን ፣ ሚድዋይፎችና የዘርፉ ተማሪዎች እንዲሁም እናቶች በዓሉን ታድመዋል።
በመርሐ ግብሩ። ፥ የደም ልገሳ ፣ ዕውቅና ለጠንካራሚድዋይፎች ፣ለወለዱ እናቶች ስጦታ እንዲሁም ሌሎች አስተማሪ ሁኔቶቾ ተካሂዷል።
ሚድዋፎች፤ በተለይም አገልግሎት በማይደርስባቸው ማህበረሰቦች ውስጥ ደህንነቱ የተጠበቀ እርግዝና፣ ወሊድ እና የድህረ ወሊድ እንክብካቤ እንዲኖር ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ።
የዘገበው የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ነው።
ሚያዝያ 29,2018 ዓ.ም
04/05/2026
#እንኳን _ደስ _አላችሁ ! _እንኳን _ደስ _አለን!
በማርበርግ ቫይረስ ክሊኒካዊ የሙከራ ክትባት ወቅት ላሳየው ልዩ ሳይንሳዊ ክትትልና ለላቀ ሕክምና አገልግሎት ላበረከተው አስተዋጽኦ እና የምርምር ደንቦች ፣ሥነምግባር መስፈርቶችንና የመረጃ ትክክለኛነትን ለማረጋገጥ ላሳየው ስኬታማ ትጋት ፣ ጥራትና ደኅንነቱ የተጠበቀ ምርምር እንዲካሄድ በማስቻል ላበረከተው አስተዋጾ የዕውቅና ምስክር ወረቀት ተበረከተ።
በዩኒቨርስቲው ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕረዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶክተር ) እንዲሁም በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ወኪል ወልዴ በተገኙበት ተበርክቷል ።
ሆስፒታላችን የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝን ለመቆጣጠር ሰፊ ጥረት እና ርብርብ ሲደረግ እንደነበር ይታወቃል ።
በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ !መላው የሆስታላችን ማህበረሰብ በሙሉ ።
ሚያዝያ 26/2018 ዓ.ም
25/04/2026
"ወባን ለማጥፋት እንነሳ፣ አሁንም እንችላለን!"
የዓለም ወባ ቀን!
ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
20/04/2026
#እንኳን #ደስ #አላችሁ! እንኳን ደስ አለን !
#የኦክስጅን #ማምረቻ ማሽን ተከላ ሥራ ተጠናቆ ምርት መጀመሩን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።
=========
#በሰዓት #600 #ሊትር #የማምረት አቅም ያለው እንደሆነ ነው የተገለፀው።
=======
የመጀመሪያው ምርት የጥራት ደረጃ አግባብነት ተረጋግጦ ዛሬ የማምረት ሂደቱ በይፋ ተጀምሯል።
ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንዲሁም ለአካባቢው ጤና ተቋማት የኦክስጅን እጥረት የሚቀርፍ ይበል የሚያሰኝ አገልግሎት እንደሆነ ጭምር ተጠቅሷል።
በኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ባለቤትነት ከአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፕሮጀክት አገልግሎት /UNOPS/ በ300 ሚሊዮን ብር የተገነባ መሆኑ ተገልጿል።
# የዘገበው ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ነው
ሚያዝያ 12/2018