12/12/2024
ሁለተኛ ቀኑን የያዘው የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የበይነ-መረብ ምዝገባ ሥልጠና በወላይታ ዞን እየተሰጠ ይገኛል።
በሥልጠናው መርሃ-ግብር ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚካኤል ሳኦል ሲሆኑ በንግግራቸውም የተማሪ ጉዳይ የሕይወት ጉዳይ ስለሆነ ባለሙያዎች የተማሪዎችን መረጃ ሲሞሉ በጥንቃቄ መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።
11/12/2024
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪወች የኦንላይን ምዝገባ ሥልጠና ተጀምሯል።
06/12/2024
የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሆን ለ83 ሁለተኛ ደረጃ ዋና ርዕሰ መምህራን፤ ለዞኑ ትምህርት መምሪያና ከወረዳና ከተማ መዋቅሮች ከተወጣጡ ትምህርት ባለሙያዎች ጋር በትምህርት አመራርና CPD/ ተከታታይ ሙያ ማሻሻያ ላይ ከ27-28/03/2017 ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
30/11/2024
የመጀመሪያው ዙር ከወረዳ ትም/ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና የትምህርት መምሪያ ማኔጅመንት ጋር የጋራ መግባቢያ መድረክ ዛሬ በ21/03/2017 ዓ.ም ተካሂዷል።
ዛሬ ከ23ቱም መዋቅር የትምህርት ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት መድረክ የእስካሁን አፈፃፀም ግምገማ ተደርጎ የቀጣይ አቅጣጫም የተቀመጠበት ሲሆን በአጭር ጊዜ ትምህርትን "ከስብራት ወደ ብስራት" የሚል መሪ ቃል በማንገብ መደረኩ ተጠናቋል።
በወላይታ ሶዶ።
28/11/2024
አዲሱ የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሚካኤል ሳኦል ከመምሪያችን አጠቃላይ ሰራተኞች ጋር የተደረገ የትውውቅ እና የ2ኛ ዙር መስክ ምልከታ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ።
26/11/2024
የወላይታ ዞን የትምህርት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሚካኤል ሳኦል ከትምህርት መምሪያ ማኔጅመንት አካላት ጋር ትውውቅ እና የሥራ ስምሪት አድርገዋል።
10/09/2024
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚገኙ ለሁለት መቶ ሀምሳ ዝቅተኛ ገቢ ለአላቸው ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
**
ወላይታ ሶዶ ጳጉሜ 5/2016 ዓ.ም ወ/ሶ/መ/ጉ/ጽ/ቤት ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚገኙ ለሁለት መቶ ሀምሳ ዝቅተኛ ገቢ ለአላቸው ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አበባየሁ ሲሞን እንደተናገሩት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የትምህርት ቁሳቁስ ወሳኝ መሆኑን የገልፁት ሀላፊው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ሥራ የገባ ተቋም ቢሆንም ከቴሌኮም ከመደበኛ አገልግሎት ባሻገር በማህበራዊ ዘርፉ እያደረገ ያለውን አሰተዋጽኦ አድንቀዋል ።
ከወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ተወካዮች አቶ በጎነህ ለማ እንደተናገሩት በትምህርት መዋቅር ወሳኙ የትምህርት ግብዓት ቁሳቁስ ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 250 ዝቅተኛ ገቢ ለአላቸው ተማሪዎች ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው ።በቀጣይ የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍና የትምህርት ጥራት ለማምጣት የትምህርት ቁሳቁስ ወሳኝ በመሆኑ የግል ባለሀብቶች ተቋማት የሳፋሪኮም አይነት ተቋማት የሚያደረጉትን አሰተዋጽኦ ሌሎችም ሊማሩ እንደሚገባ ተናግረዋል ።
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኤክሰተርናል ኦፊስ ማናጀር ቤካ ዳባ እንደተናገሩት ሲፋሪኮ ኢትዮጵያ ከቴሌኮም ከመደበኛ አገልግሎት ባሻገር ከማህበራዊ ሀላፊነት እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል ።በዚህም መሠረት በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚገኙ 250 በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል ።
21/08/2024
የ2016 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች ውጤት ከሥር በተቀመጠው ሊንክ ማየት ይቻላል።
403 Forbidden
21/08/2024
በ2016ዓ.ም የሀገር አቀፍ 8ኛ ክፍል ፈተና በክልል ደረጃ ከፍተኛ ዉጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች፤
እንኳን ደስ አላችሁ!!
20/08/2024
"አንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ" በሚል ቃል በተሰበሰበው ሀብት የታተመው መጽሐፍ ስርጭት ማስጀመሪያ መርሃግብር በወላይታ ሶዶ እየተካሄደ ነው
ወላይታ ሶዶ፤ነሐሴ 14/2016 በርዕሰ መስተደድር ጥላሁን ከበደ ሀሳብ አመንጪነት "አንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ" በሚል ቃል በተሰበሰበው ሀብት የታተመው መጽሐፍ ክልላዊ ስርጭት ማስጀመሪያ መርሃግብር በወላይታ ሶዶ እየተካሄደ ይገኛል።
በርዕሰ መስተደድር ጥላሁን ከበደ ሀሳብ አመንጪነት "አንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ" በሚል ቃል በተጀመረው ኢንሼቲቭ መሰረት በ2017 ትምህርት ዘመን ክልላዊ 1ኛ ደረጃ መጽሐፍ ስርጭት ማስጀመሪያ መርሃግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ "ሊጋባ ትምህርት ቤት" በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመርሃግብሩ ርዕሰ መስተደድር ጥለሁን ከበደ፣ የክልሉ በም/ር/መስተዳድር ማዕረግ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ፣ የክልል፣ የዞንና የወላይታ ሶዶ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
17/08/2024
የወላይታ ዞን ም/ዋና አስተዳዳሪ እና የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎበዘ ጎዳና በጉኑኖ ከተማ በአንድ ጀንበር የሚሰሩ ቤቶችን ለመገንባትና ለማደስ የሚያስችል መርሃግብርን በይፋ አስጀምረዋል።
"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በጉኑኖ ሐሙስ ከተማ በአንድ ጀንበር የሚጀምር ቤቶችን ለአረጋዊያንና ለአቅመ ደካሞች ለመገንባትና ለማደስ የሚያስችል አንድ አዲስ ቤትና አንድ የማሳደስ ቤት የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ሠራተኞች ባደረጉት የገንዘብ ድጋፍ የበጎነት ስራ ተከናውኗል።
15/08/2024
ለ2017 የትምህርት ዘመን ከ4ኛ እስከ 6ኛ ክፍል በሁሉም የትምህርት ዓይነት መማርያና ማስተማሪያ መጽሐፍት መረከብ ጀምረናል። ስለዚህ ከቀን 20/12/2016 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም መዋቅሮች ለመረከብ ዝግጅት እንድታደርጉ እንጠይቃለን።