Damota Technology & Business College

Damota Technology & Business College

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Damota Technology & Business College, Education, VQ58+G23, Soddo, Sodo.

Photos from Damota Technology & Business College's post 02/08/2025

"ኮሌጁ ለዞናችን ትምህርት ሽፋንና ጥራት ላይ እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ ሌሎችም ተቋማት በአርአያነት ሊከተሉት ይገበዋል" ብለዋል አቶ ሚካኤል ሳኦል

ወ/ሶዶ፣ሐምሌ 26/2017ዓም
ዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ለ7ኛ ዙር በዲግሪና ዲፕሎማ በተለያዩ ሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ከ6 መቶ በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ

የዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ የምረቃ ፕሮግራም ላይ በተገኙበት መምሪያችን ያነጋገራቸው የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚካኤል ሳኦል የዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ለዞናችን ትምህርት ሽፋንና ጥራት እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ ሌሎችም ተቋማት በአርአያነት ሊከተሉት የሚገባ ተሞክሮ ነው ብለዋል።

ኮሌጁ ተመራቂዎቹ ከትምህርት ቆይታቸው በኋላ የት ገቡ? ምን እየሠሩ ነው? የሚለውን የሚከታተል ቦርድ አቋቁሞ እንደሚከታተል ያወሱት አቶ ተስፋዬ በCOC ፈተናም በንጽጽር የተሻለ የማለፍ ምጣኔ እንዳሳየም ተናግረዋል።

ኮሌጁ የትምህርቱን ዘርፍ ከመሠረቱ ለማገዝ ካለው ትልቅ ራዕይ የተነሳ በወላይታ ሶዶ ከተማ ዴሪ መንደር ላይ ሜትሮፖሊታን የተሰኘ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በመክፈት በ2018 ዓ.ም ወደ ሥራ ለመግባት እንደተዘጋጀም ጨምረው ገልጸዋል።

የዛሬ ተመራቂዎች በቀጣይ ጊዜያ ከኮሌጁ ባገኙት እውቀት ራሳቸውን በማገዝ ለትልቅ ደረጃ እንዲደርሱ በቀጣይ የኮሌጁ ድጋፍ እንደማይለያቸውም የኮሌጁ ባለቤትና ፕሬዝዳንት አቶ ተስፋዬ ጎኣ ገልጸዋል።

Photos from Damota Technology & Business College's post 02/08/2025

ኮሌጁ ለሀገራችን ብሎም ለዞናችን የተማረ የሰው ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የሚያደርገውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል የዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ ጎአ ተናገሩ።

ወ/ሶዶ፣ሐምሌ 26/2017
ዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ለ7ኛ ዙር በዲግሪና ዲፕሎማ በተለያዩ ሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ከ6 መቶ በላይ ተማሪዎችን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ማስመረቂያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ባለበት ፕሮግራም ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ ጎአ ኮሌጁ ለሀገራችን ብሎም ለዞናችን የተማረ የሰው ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የሚያደርገውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል ።

በፕሮግራሙ በክብር እንግድነት በመገኘት ለተመራቂዎች መልዕክት ያስላለፉት የወላይታ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማቸው ከፍያለው ተመራቂዎች ከግል ህይወታቸው ባሻገር ራዕይ ይዘው ለሀገርና ለህዝብ ብልጽግና እንዲሠሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ኃላፊው አክለውም ተመራቂዎች በኮሌጁ የቀሰሙትን ዕውቀት መንግሥት ካመቻቸው አሠራር ጋር በማሰናሰል ለሁለንተናዊ ብልጽግና እንዲተጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

Photos from Damota Technology & Business College's post 02/08/2025

የዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ለ7ኛ ዙር በዲግሪ ፣ በተለያዩ ደረጃዎችና ሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ከ6 መቶ በላይ ተማሪዎችን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ማስመረቂያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ይገኛል ።

ወ/ሶዶ፣ሐምሌ 26/2017
ዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ለ7ኛ ዙር በዲግሪ ፣ በተለያዩ ደረጃዎችና ሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ከ6 መቶ በላይ ተማሪዎችን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ማስመረቂያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ይገኛል ።

Photos from Damota Technology & Business College's post 02/08/2025

የዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ለ7ኛ ዙር በዲግሪ ፣ በተለያዩ ደረጃዎችና ሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ከ6 መቶ በላይ ተማሪዎችን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ማስመረቂያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ይገኛል ።

ወ/ሶዶ፣ሐምሌ 26/2017 (ወዞመኮጉ)
ዳሞታ ቴክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ ለ7ኛ ዙር በዲግሪ ፣ በተለያዩ ደረጃዎችና ሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ከ6 መቶ በላይ ተማሪዎችን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ማስመረቂያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ይገኛል ።

21/07/2025

እንኳን ደስ አላችሁ ፤ እንኳን ደስ አለን!



#የምረቃ #ሥነ-ሥርዓት ቅዳሜ ቀን #(26/11/2017 ዓ.ም) መሆኑ ተጠቆመ!



****************





ዳሞታ ቴክኖሎጂና ብዝነስ ኮሌጅ በመደበኛ፣በሳምንት መጨረሻ(weekend እና በርቀት (Distance) ትምህርት መርሀ ግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎችን ዕለት ቅዳሜ ቀን #(26/11/2017 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ዩንቨርሲቲ ገቢ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል፡፡





ዳሞታ ተክኖሎጂና ብዝነስ ኮሌጅ



ለእዉቀቶ ከፍታ ይመረጣል ዳሞታ!

Photos from Damota Technology & Business College's post 22/06/2025

#የሀዘን #መግለጫ



በዳሞታ ቴክኖሎጂና ብዝነስ ኮሌጅ ብዝነስ ማናጅመንትምህርት ክፍል 4ኛ ዓሜት ተማሪ ዘሩሁን ዋካ ሀላቦ ባደረባቸዉ ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በቀን 13/10/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ኮሌጁ በተማሪ ዘሩሁን ዋካ ሀላቦ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናጽን ይመኛል፡፡



ዳሞታ ቴክኖሎጂና ብዝነስ ኮለጅ

Photos from Damota Technology & Business College's post 08/06/2025

day @ Wsu after exit exam orientation

08/06/2025

#ማስታወቂያ

#ለመውጫ #ፈተና #ተፈታኞች #በሙሉ፥

ከሰኔ 02-10/2017 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል በሚሰጡ የመውጫ ፈተናዎች የምትቀመጡ ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትመጡበት ጊዜ ማንኛውም ዓይነት ሞባይል ስልክ ይዞ መምጣት ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን እናሳውቃለን።

ይህንኑ በመተላለፍ ይዞ የተገኘ ተፈታኝ ከፈተና የምሰናበትና የዲሲፕሊን ቅጣት የሚጠብቀው/ቃት መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።

ዩኒቨርሰቲው

08/06/2025

#የመውጫ #ፈተና #ዜና



ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ብሄራዊ መታወቂያ ( #ፋይዳ) መያዝ አለባቸው ተብሏል፡፡



*******



የከፍተኛ ትምህርት ቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ 10/ 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መግለጹ ይታወቃል።



የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) የ2017 የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 10 /2017 ዓ.ም. በ51 ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት ይሰጣል ብለዋል።



ዶ/ር ኤባ አክለውም ፈተናውን በ238 የትምህርት መርሃ ግብሮች ለ190 ሺ 787 ቅድመ መደበኛ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በበይነ መረብ ለመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡



ለፈተናው 102 ሺ 360 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ፤ 88 ሺ 422 ተማሪዎች ደግሞ ዳግም የሚፈተኑ መሆናቸውን የጠቆሙት መሪ ሥራ አስፈጻሚው ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት ሲመጡ #አገር #አቀፍ #ፋይዳ /ብሄራዊ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል፡፡



ተማሪዎቹ በፈተና ወቅት #ተንቀሳቃሽ #ስልክ፣ #ሜሞሪ ያለው #የእጅ #ሰዓት፣ #የራስ #ያልሆነ #መታወቂያ፣ #ያልተፈቀዱ #ሂሳብ #ማሽኖች፣ #አጫጭር #ማስታወሻዎች፣ #የተጭበረበሩ #ሰነዶች እንዲሁም #ማንኛውንም ዓይነት #የጦር #መሣሪያ ይዞ መገኘት #ክልክል መሆኑን አስገንዝበዋል ዶ/ር ኤባ።



ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ #አደንዛዥ #ዕጽ #ተጠቅሞ #መምጣት፣ #ከፈተና #አስፈጻሚዎች ጋር #አሉታዊ #ተጽእኖ #ያላቸው #ውዝግቦችን #መፍጠር፣ #ያለመታወቂያ #ካርድ ወደ ፈተና #ማእከል #መሄድ፣ #ያለፈቃድ #ፈተና ማዕከል መገኘት ፍፁም የተከለከሉ መሆኑ ተነግሯል።



ለሌላ ሰው መፈተን ፍጹም የተከለከሉ ዲሲፒሊን ጥሰቶች መሆኑም እንዲሁ።



ከሰኔ 2 እስከ 10/ 20017 በሚሰጠው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና 4 ሺ 17 ፈተና አስፈጻሚዎች እንደሚሳተፉ መረጃዎች ያመላክታሉ።



(ምንጭ: ኢ. ፌ. ዴ. ሪ ትምህርት ሚኒስቴር)







Damota Technology and Business College

08/06/2025

ማስታወቂያ



ለ መዉጫ ፈተና(Exit exam) ዙሪያ Orientation ነገ ዕሁድ 01/10/2017 ዓ ም ከቀኑ 7:30 በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በመመረቂያ አዳራሽ ዉስጥ ስለምሰጥ በቦታዉ በመገኘት እንድትከታተሉ ኮሌጃች ዳሞታ ቴክኖሎጂና ብዝነስ ኮሌጅ በጥብቅ ያሳስባል ።



ከኮሌጁ

07/06/2025

የከፍተኛ ትምህርት ቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ 10 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።



ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ብሄራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) መያዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡



****** ***** *****



ፈተናውን በ238 የትምህርት መርሃ ግብሮች ለ190 ሺ 787 ቅድመ መደበኛ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በበይነ መረብ ለመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁንም ዶክተር ኤባ ተናግረዋል፡፡



ለፈተናው 102 ሺ 360 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ፤ 88 ሺ 422 ተማሪዎች ደግሞ ዳግም የሚፈተኑ መሆናቸውን መሪ ስራ አስፈጻሚው ገልጸው ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት ሲመጡ አገር አቀፍ ፋይዳ /ብሄራዊ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸውም ኃላፊው አስገንዝበዋል፡፡



ተፈታኞች በፈተና ወቅት

👉 ተንቀሳቃሽ ስልክ ፣

👉ሜሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት ፣

👉የራስ ያልሆነ መታወቂያ፣

👉ያልተፈቀዱ ሂሳብ ማሽኖች፣

👉አጫጭር ማስታወሻዎች፣

👉የተጭበረበሩ ሰነዶች ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት ክልክል ነው።



ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ አደንዛዥ ዕጽ ተጠቅሞ መምጣት፣ ከፈተና አስፈጻሚዎች ጋር አሉታዊ ተጽእኖ ያላቸው ውዝግቦችን መፍጠር ፣ ያለመታወቂያ ካርድ ወደ ፈተና ማእከል መሄድ ፣ ያለፈቃድ ፈተና ማዕከል መገኘት ለሌላ ሰው መፈተን ፍጹም የተከለከሉ የዲሲፒሊን ጥሰቶች መሆናቸውንም ገልጸዋል፡



ከሰኔ 2 እስከ 10/ 20017 ለሚሰጠው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና 4 ሺ 17 ፈተና አስፈጻሚዎች እንደሚሳተፉም ጨምረው ተናግረዋል ፡፡

Want your school to be the top-listed School/college in Sodo?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address


VQ58+G23, Soddo
S**o