Shone tvet college

Shone tvet college Name :-SHONE POLY TECHNIC COLLEGE

ታህሳስ  28/04/2018 ዓ.ም ሾኔ!የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሻለ ተካልኝ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደ...
06/01/2026

ታህሳስ 28/04/2018 ዓ.ም ሾኔ!
የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሻለ ተካልኝ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል (ገና) በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!
የገና በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን ሲል ከሰማይ ሰማያት ወርዶ በከብቶች በረት ከድንግል ማሪያም የተወለደበትን ዕለት የምንዘክርበት በዓል ነው።
የሰው ልጆች ከነበሩበት ዝቅታ የመውጣታቸው ተስፋ የተበሰረበት እና ከጨለማ ወደ ብርሃን የመምጣታቸው ምዕራፍ የተጀመረበት ታላቅ በዓል ነው ።
የክርስቶስ ልደት የልዩነትን ግንብ ያፈረሰ፣ የጠብን ግድግዳ የናደ፣ የጥላቻን መጋረጃ የቀደደ፣ የተዋረዱትን ያከበረ፣ የተለያዩትን አንድ ያደረገ፣ የተበተኑትን የሰበሰበ እና የሰው ዘር ትርፍ እንደገና ያደሰ በዓል ነው፡፡
በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትንና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ወገኖቻችንን በመርዳት፣ በመተሳሰብ፣ በይቅርባንይነት፣ በመግባባት፣ በወንድማማችነት፤ በእህታማማችነትና በአብሮነት መንፈስ ካለን በመካፈል በጋር እንዲናከብር ብለዋል ::
መልካም የገና በዓል!!
የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ተሻለ ተካልኝ
ታህሳስ 28/04/2018 ዓ.ም

ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም።የማ/ኢ/ክ/ቴ/ሙ/ት/ሥ/ቢሮ  የ6 ወር ስራ አፈጻጸም በሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ   የ6 ወር  የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ና የክትት ና ምልከታ የክልሉ ቴ/ሙ/ሥ/ቢሮ ም...
29/12/2025

ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም።
የማ/ኢ/ክ/ቴ/ሙ/ት/ሥ/ቢሮ የ6 ወር ስራ አፈጻጸም በሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ6 ወር የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ና የክትት ና ምልከታ የክልሉ ቴ/ሙ/ሥ/ቢሮ ም/ሃላፊ አንዲሁም የሀድያ ዞን ቴ/ሙ/ት/ሥ/መምሪያ ሀላፊ በተገኙበት ግምገማ የክትትል ና የምልከታ ተካሄደ ።
በዚህም የሪፖርተ የግምገማ ላይ ከአስተዳደር ሠራተኞችና አሰልጣኞች የተለያዩ ጥያቄዎች ና አስተያየት ተነስተው ዝርዝር ነገሮች ላይ ውይይት ተደርጓል ።እንዲሁም እንደዞን የመምህራያው እና የክልሉ ት/ሥ/ቢሮ ም/ሃላፊ የየራሳቸውን የወሰዱ ሲሆን የነበሩ ክፍተቶችን ኮሌጁ እንደኮሌጅ ዞን እንደዞን ክልል እንደክልል የወሰዱ ሲሆን በቀጣይ ችግሮችን የሚፈቱበትን የጋራ አቅጣጫዎች ተቀምጧል ።
በግምገማው መድረክ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና የቢሮው ም/ል ሃላፊና የተቋማት አቅም ግንባታና ሥልጠና ዘርፍ ሃላፊ ኢንጂነር ሰለሞን ፈርሻ እንዲሁም የሀድያ ዞን ቴክ/ሙያ ት/ሥል/መምሪያ ሃላፊ አቶ ተስፋዬ እርስቱን ጨምሮ የክልልና የዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፍዎች ተገኝተዋል።
በተጨማሪም በግምገማ መድረክ ላይ የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኃላፊዎች ማኔጅመንትና ሠራተኞች ተገኝተዋል።
የክልልና የዞን የድጋፋዊ ክትትል ልዑክ በኮሌጁ የተሠሩ ሥራዎችን ተዘዋውሮ ምልከታ ያደረገ ሲሆን በስልጠና ላይ ያሉ ተማሪዎችንም ጎብኝተዋል።
በውይይት መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ቴ/ሙ/ት/ሥ/ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኢንጅነር ሰለሞን ፈርሻ እንደተናገሩት ከሆነ ኮሌጁ ወደ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ካደገ አጭር ግዜ ቢሆንም እያሳየ ያለው ውጤት አመርቂ እንደሆነ ገልጸው በሀገር ውስጥ ከሚገኙ አቻ ኮሌጆች ጋር ተወዳዳሪ እንድሆን የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።
በመቀጠልም የድጋፋዊ ክትትል ልዑክ ቡድን አባል እና የሀድያ ዞን ቴ/ሙ/መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ እርስቱ እንደገለጹት ከሆነ ኮሌጁ በአጭር ግዜ የተሻለ ውጤት እያስመዘገባ ያለ መሆኑን ተናግረው ለተመዘገበው ውጤት የማኔጅመንቱና የሠራተኛው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
በመጨረሻም የኮሌጁ ዲን አቶ ተሻለ ተካልኝ በግምገማው መድረክ ለይ እና በጉብኝት ወቅት የታዩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል ጉድለቶችን ለማሻሻል እንደምሠሩ ገልጸዋል።

ከወቅቱ ጋር መናበብ የሚችልና ጉድለቶችን አርሞ መንቀሳቀስ የሚያስችል የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራተጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ተገብቷል፤ሆሳዕና፤ታህሳስ፣10/2018ዓ.ምየማዕከላዊ ኢትዮጵያ...
19/12/2025

ከወቅቱ ጋር መናበብ የሚችልና ጉድለቶችን አርሞ መንቀሳቀስ የሚያስችል የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራተጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ተገብቷል፤

ሆሳዕና፤ታህሳስ፣10/2018ዓ.ም
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጤና ቢሮ በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራተጂ ዙሪያ ለሴክተሩ ባለሙያዎች፤ የዞን መምሪያ ሀላፊዎች፤ ለኮሌጅ ዲኖችና ባለድርሻ አካላት ሀላባ ከተማ ላይ ስልጠና እየተሠጠ ነው።

የቢሮ ሀላፊ አቶ አሰፋ ደቼ ስልጠናውን ሲከፍቱ ፣ ከወቅቱ ጋር መናበብ የሚችልና ጉድለቶችን አርሞ መንቀሳቀስ የሚያስችል የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራተጂክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል።

አዲሱ የስልጠና ስትራተጂ ከዚህ በፊት የነበሩ፣ ጉድለቶችን አርሞ የስልጠና ጥራትና የዘቱን ማሳደግ የሚያስችል መሆኑን የቢሮ ሀላፊው የገለፁ ሲሆን ፣ ቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራዎችን ከወቅቱ ተለዋዋጭነት ጋር ማናበብ የሚያስችልና የተለያዩ የህብረተሠብ ክፍሎችን ታሳቢ ያደረገ ፣ እንዲሁም ለችግሮቻቸው መፍትሄዎች በማመንጨት ቅኝት የተዘጋጀ መሆኑንም አብራርተዋል።

አዲሱ ስትራተጂክ ዕቅድ ፣ እያደገ ያለው የኢንዱስትሪ ዘርፍ ፣ አርሷደሩና የከተማው ነዋሪ ከተቋሙ የሚፈልጋቸውን አገልግሎቶች መስጠትና ምላሾች ማስገኘት የሚያስችል መሆኑንም ጭምር ሀላፊው አመልክተዋል።

ከስራ ፍላጎቶች ጋር ቀጥተኛ ትስስር ላላቸው ፍላጎቶች ትኩረት የሚሰጠው አዲሱ ስትራተጂክ እቅድ ፣ ስልጠና የወሰዱ ዜጎች ቀላል በሆነ መንገድ ወደ ስራ የሚሰማሩበትን መንገድ የማመላከት ሚና እንዳለውም የቢሮ ሀላፊው አስረድተዋል።

ይኸው ወጣቶች ለስራ አቅም የሚሆናቸውን ዕድሎች የሚያስጨብጠው ስትራተጂክ ዕቅድ ፣ ወጣቶች በስራ ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ቅኝት መዘጋጀቱ ተጠቁሟል።

የህብረተሠቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማቶችን ማረጋገጥ በሚያስችል፣ እንዲሁም ምርታማነትን ማሳደግ በሚያስችል መንገድ የተዘጋጀውን ስትራተጂክ እቅድ ላይ በመመርኮዝ በተቋሞቻችን የሚሰጡ ስልጠናዎችን መቃኘት ይገባናል ሲሉ አቶ አሰፋ አሳስበዋል።

ታህሳስ 07/04/2018 ዓ.ም ሾኔ ዛሬ ታህሳስ 07/04/2018 ዓ.ም በሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር "በሚል መሪ ቃል የፀረ-ሙስና የፀረ-ምግባር ቀን ...
16/12/2025

ታህሳስ 07/04/2018 ዓ.ም ሾኔ
ዛሬ ታህሳስ 07/04/2018 ዓ.ም በሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር "በሚል መሪ ቃል የፀረ-ሙስና የፀረ-ምግባር ቀን በተለያዩ ፕሮግራም ና ከክልል በወረድ ሰነዶች ላይ ውይይት በማድረግ ቀን ተከበረ።
የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በሀገራችን ለ21ኛ እና እንዲሁም በክልላችን ለ3ኛ ግዜ
እየተከበረ ያለውን የፀረሙስናና የፀረ ምግባር ቀንን ከኮሌጅ አስተዳደር ሠራተኞችን ና ከኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን
እንዲሁም የአሠልጣኞችና ጥሪ ከተደረገላቸው ከሾኔ ከተማ አስተዳደር ከመጡ ባለድርሻ አካላት ጋር ከክልል በወረዱ
ሰነዶች ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ና ሀሳቦች ላይ አስተያየት በመስጠት ቀኑን ተከብሮል ውሏል ሲል የኮሌጁ ኮምኒኬሽን አስታውቋል ።

የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 2018 ዓ.ም

የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ የሚገኘው የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት የሥራና ክህሎት ሚስቴር መቋቋሙን ተከትሎ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል ...
26/10/2025

የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ የሚገኘው የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት

የሥራና ክህሎት ሚስቴር መቋቋሙን ተከትሎ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አንዱ ነው፡፡

ከዚህ ቀደም ስምሪቱ በርካታ ህገወጥ አሠራሮች በሰፊው የተንሰራፉበት ነበር፡፡

በመሆኑም ለተሻለ ህይወት እና ሥራ ወደ ተለያዩ ሀገራት የሚሄዱ ዜጎቻችን ላልተፈለገ ወጪ እና እንግልት ሲዳረጉ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በላይ በርካቶች ለሞት እና ለከፍተኛ አካል ጉዳት ሲዳረጉ ቆይቷል፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ፍልሰት አይቀሬ ነባራዊ ሁኔታ መሆኑን ከግምት በማስገባት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ስርዓቱን ለማሻሻል የተለዩ የሪፎርም ሥራዎችን እየተገበረ ይገኛል፡፡

የሪፎርሙ አጠቃላይ መነሻና መዳረሻ የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ሲሆን ይህንን ዕውን ለማድረግ አዲስ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ፀድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጓል፡፡፡

በውስጥ አቅም በልፅጎ ሥራ ላይ የዋለው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱን ከማዘመኑም በላይ ዜጎች ከመነሻ እስከ መዳረሻ ሀገራት ድረስ ይገጥማቸው የነበረውን አላስፈላጊ ወጪ እንዲቆምና የነበረው እንግልትም እንዲቀንስ አድርጓል፡፡

በውጭ ሀገር በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ላይ ለመሰማራት ለሚፈልጉ ዜጎች ሥርዓተ-ትምህርት ተቀርጾ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙና በተመረጡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ስልጠና እንዲወስዱና ብቃታቸውንም በምዘና እንዲያረጋግጡ የሚያስችል ስርዓት ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ይህም ዜጎች ከሙያ ባለፈ ስለሚሄዱበት ሀገር ባህል፣ ቋንቋና መሰል ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ጭምር በስነ-ልቦና ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርግ ነው፡፡

ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ጆርዳን፣ ኳታር፣ ቤሩት እና ኩዌት የመዳረሻ ሀገራትን ለማስፋት በተደረገው ጥረት የሁለትዮሽ ስምምነት የተደረገባቸው ሀገራት ናቸው፡፡

በ2018 በጀት ዓመት የመዳረሻ ሀገራትን ለማስፋትና የሰለጠኑና በከፊል የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ለበሥራ ስምሪቱ ተጨቃሚ ለማድረግ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት እየተዘረጋ ይገኛል፡፡

የውጪ ሃገር የሥራ ስምሪት አዲሱን አዋጅ አስመልክቶ ለሁሉም ኤጀንሲዎች ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ተሠርቷል፡፡ የሥራ ውላቸው ተጠናቆ የሚመለሱ ዜጎች በቴክኖሎጂ እንዲስተናገዱ ተደርጓል፡፡

በ1ኛው ሩብ አመት በዉጭ አገር ሥራ ስምሪት የተሰማሩ ኤጀንሲዎች የበይነ መረብ ስርዓትን በመጠቀም በመዳረሻ ሀገራት ከሚገኙ 366 ኤጀንቶች ጋር የሁለትዮሽ አጋርነት/partnership/ እንዲፈራረሙ ተደርጓል፡፡ 166 ኤጀንሲዎች በበይነ መረብ ስርዓት የተመረመረ እና የታደሰ ፈቃድ ማግኘት ችለዋል፡፡

የመዳረሻ ሀገራትን ማስፋት፣ የዜጎችን ደህንነትና ክብር ለማስጠበቅ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ማጠናከርና የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማላቅ በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት በትኩረት የሚሠሩ ሥራዎች ናቸው፡፡

ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

አስደሳች ዜና ለትምህርትና ሥልጠና ፈላጊዎች በሙሉ የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና መርሃ ግብር የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ  በሆነው መሠረት ለሥልጠና ፈላጊዎች ምዝ...
18/10/2025

አስደሳች ዜና ለትምህርትና ሥልጠና ፈላጊዎች በሙሉ የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና መርሃ ግብር የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ በሆነው መሠረት ለሥልጠና ፈላጊዎች ምዝገባ መጀመራችንን እንገልፃለን ።

ይህ ለአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች ደመወዝ ጭማሬ ለክልሎች የተላለፈበት ዝርዝር ነው።👉ለትግራይ ክልል  -  481,545,815.40 ብር👉ለአማራ ክልል  -  2.009,068,537.61 ብር👉ለኦ...
11/10/2025

ይህ ለአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች ደመወዝ ጭማሬ ለክልሎች የተላለፈበት ዝርዝር ነው።
👉ለትግራይ ክልል - 481,545,815.40 ብር
👉ለአማራ ክልል - 2.009,068,537.61 ብር
👉ለኦሮሚያ ክልል - 2,615,822,048. 42 ብር መተላለፉን ሠነዱ ይጠቁማል።የገንዘብ መጠኑን የያዘው ደብዳቤ ከታች ተያይዟል።

ዘንድሮ የተመረቃችሁ ሰልጣኞች እንኳን ደስ አላችሁ እያ በድጋሚ መልካም ምኞቱን ይገልፃል ።
11/10/2025

ዘንድሮ የተመረቃችሁ ሰልጣኞች እንኳን ደስ አላችሁ እያ በድጋሚ መልካም ምኞቱን ይገልፃል ።

በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የተከለከሉ እና የእርምት እርምጃ የሚያስከትሉ ተግባራት   ---------------------------------------------------------...
11/10/2025

በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የተከለከሉ እና የእርምት እርምጃ የሚያስከትሉ ተግባራት
-------------------------------------------------------------------------------------------------
** ፈቃድ ባልተገኘበት ተቋም ስልጠና መስጠት፤
** ባልተፈቀደለት የሥልጠና መስክ ስልጠና እየሰጠ የተገኘ ተቋም፤
**ፈቃድ ሳያድስ ሲያስተምር የተገኘ ተቋም፤
** በባለሥልጣኑ ከተሰጠው የደረጃ ስያሜ ውጪ ሌላ የደረጃ ስያሜ ሲጠቀም የተገኘ ተቋም፤
** በሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ከሚያዘጋጀው የሙያ ደረጃ እና ስርዓት ትምህርቱ ወጭ ሲያሰለጥን የተገኘ ተቋም፤
** የሥልጠና መስክ አሰልጣኞች አዛውሮ ወይም ቀይሮ ሲገኝ፤
** ስልጣን ባለው አካል የወጡ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና መግቢያ መስፈርቶችን ያላሟሉ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ስልጠና የሰጠ ተቋም፤
** ከተፈቀደለት ሰልጣኝ ቁጥር በላይ መዝግቦ ሲያሰለጥን የተገኘ ተቋም፤
** የተማሪ መረጃ አያያዝ፣ አጠባበቅና አላላክ፤
** ባለሥልጣኑ የተሰጠውን የፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት ደብዳቤ በግልጽ ለተገልጋዩ ህብረተሰብ በሚታይ ሁኔታ ያለጠፈ ወይም ያላሳወቀ ተቋም፤
** ባለሥልጣኑ የተሰጠውን የፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት ደብዳቤ በግልጽ ለተገልጋዩ ህብረተሰብ በሚታይ ሁኔታ ያለጠፈ ወይም ያላሳወቀ ተቋም እና
** ሐሰተኛ ሰነዶች እና ትክክለኛ አድርጎ ማቅረብ ናቸው፡፡

የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ - https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም - https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www.neta.gov.et ይከታተሉን፡፡

የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ5ኛ ጊዜ በተለያዩ የሥልጠና ዘርፎች ያሠለጠናቸውን ሠልጣኞች በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ፡፡‎‎መስከረም 24/2018 ዓ.ም‎‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትም...
04/10/2025

የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ5ኛ ጊዜ በተለያዩ የሥልጠና ዘርፎች ያሠለጠናቸውን ሠልጣኞች በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ፡፡

‎መስከረም 24/2018 ዓ.ም

‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ቢሮ በሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 5ኛ ዙር የተማሪዎች ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርና ሥልጠና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የክልሉ የተለያዩ ቢሮዎች የስራ ኃላፊዎች፣የሀዲያ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና መምሪያ የስራ ኃላፊዎች፣ ተመራቂዎች፣ የተመራቂ ቤተሰቦችና ጥሪ የተገኘላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

‎የምረቃውን ሥነ-ሥርዓት በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የከፈቱት የሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ተሻለ ተካልኝ የዛሬውን የሠልጣኞች የምረቃ በዓል ከወትሮው ከምናከብራቸው በዓላት ልዩ የሚያደርገው ሁለት ዐቢይ ምክንያቶች እንዳሉ አውስተው ኢትዮጲያ ሀገራችን በብዙ እልህና ቀጭት ህዝቦቿን በማስተባበር የገነባችውን ታላቁን የህዳሴ ግድብ ጨርሰን ባስመረቅንበትና ኮሌጃችን ወደ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅነት ባደገ ማግስት መሆኑ በዓሉን የደመቀና ድርብ ድል ያደርገዋል ብለዋል፡፡

‎አቶ ተሻለ አያይዘውም ኮሌጁ በዘርፉ ተልዕኮ መነሻነት በላፉት ዓመታት በአጫጭር፣ ዝቅተኛና መካከለኛ ደረጃ ሙያተኞችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ሥራ እንዲሰማሩ በማድረግ በክልሉ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አብራተው በዛሬው ዕለት በሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የንድፈ ሀሳብና የተግባር ሥልጠና አጠናቀው ለምረቃ የቀረቡ ሠልጣኞች ከሰባት የትምህርት ክፍሎች ሲሆን በአጠቃላይ ሴት 145 ወንድ 89 በድምሩ 234 ተመራቂዎች ለዛሬው ዕለት ምረቃ መብቃታቸውን ነግረውናል፡፡

‎ሀገራችን ኢትዮጲያ የጀመረቺውን የብልጽግና ጉዞ ስኬት መዳረሻ እውን ለማድረግ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ የሚጫወተው ሚናና አበርክቶ እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑም ባሻገር ዜጎች በመልካም ሥነ-ምግባር የታነጹ፣ በኢኮኖሚ ራሳቸውን ከመቻል አልፎ ለሀገር ግንባታ አስተዋጽዖ የሚያደርጉ፣ እንዲሁም ሀገራቸውን ኢትዮጵያ ለመገንባት በሚደረገው ሁሉ አቀፍና ዘርፈ ብዙ ተሳትፎ የራሳቸውን ድርሻ በመወጣት ተወዳዳሪና አምራች እንዲሆኑ በማስቻል ረገድ የጋራ ተጠቃሚነትን በማስፈን ጠንካራ ሀገር ተረካቢ ማንነት ያላቸውን ሠልጣኞችን ማፍራት እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡

‎የዛሬ ሠልጣኞች መመረቅ የመጨረሻ ግብ እንዳልሆነ በመገንዘብና አጽንዖት በመስጠት በሕይወታቸው የሚገጥማቸውን ዉጣ ውረድ በመቋቋም ሥራ ፈጣሪ፣ በራስ የሚተማምን፣ ዘመኑን የዋጀና በመልካም ሥነ-ምግባሩ የበለጸገ ዜጋ በመሆን ኢትዮጲያንና ህዝቦቿን ለማገልገል ቀን ተሌት በመትጋት ወደ ብልጽግና የምንጓዝበትን ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን በትጋትና በትዕግስት መወጣት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ቢሮ ምክትልና የሥልጠናና ተቋማት አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የዕለቱ የክብር እንግዳ ኢ/ር ሰለሞን ፈርሻ በበኩላቸው ለዕለቱን ተመራቂዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት የሚያበረክተዉ አስተዋጽዎ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው ይህ የስልጠና መስክ ዜጎችን በንድፈ ሀሳብ፤ በክህሎት እና በአመለካከት የዳበረ ብቃት የሚያስታጥቅ ስራ ፈጣሪ ዜጎች ከማፍራት አንጻር ሚናዉ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
‎ምክትል ቢሮ ኃላፊው አያይዘውም ዜጎች ዉስጣቸዉ ያለውን ተስጥዎ እንዲያወጡ እና እንዲያበለጽጉ የሚያስችል፤ፈጠራ የሚያነሳሳ፤ዘላቂ የሆነ የስራ ዕድል ለመፍጠር የሚ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ፣ሆሳዕና ፣ መስከረም 23 ፣ 2018 ዓ.ምየማዕከላዊ  ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) የተለያዩ...
04/10/2025

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ፣
ሆሳዕና ፣ መስከረም 23 ፣ 2018 ዓ.ም

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) የተለያዩ ሹመቶችን በሸግሽግና አዳዲስ ሹመቶችን ሰጥተዋል።
በዚህም መሠረት፦
1/ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋዬ - ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሀላፊ
2/ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሺድ - የገቢዎች ቢሮ ሀላፊ
3/ አቶ ዳንኤል ዳምጣው - የፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊ
4/ ኢንጂነር ሸሪፍ ሀሰን - በካቢኔ ማዕረግ - የውሃ ስራዎች ስራ አስኪያጅ
5/ አቶ ደስታ ተስፋዬ - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የትምህርት ቢሮ ጽህፈት ቤት ሀላፊ
6/ አቶ ራህማቶ ቦካ - የትምህርት ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ
7/ ኢ/ር አንድነት ወንባርጋ - በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ - የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽነር
8/ ዶ/ር በፍቃዱ ገብረሃና - የፖሊሲ ጥናት ምርምር ምክትል ዳይሬክተር
9/ ዶ/ር ተስፋዬ አጋፋሪ - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የኢንቬስትመንትና ኢንዳስትሪ ልማት ቢሮ ማካሪ
10/ ወ/ሮ ወጋሜ ጴጥሮስ- - በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- የዴሞክራሲ ሰርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል - ሀብት ልማትና አሰተደደር ዘርፍ ሀላፊ
11/ ወ/ሮ ስምረት ሳሙኤል - በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- በዴሞክራሲ ሰርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል ስትራቴጂክ ፕላንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ሀላፊ

12/ አቶ አንዳለ ወልደሚካሄል- በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ- የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ፣ የሀይማኖት ጉዳዮች ዘርፍ ሀላፊ
13/ ኢ/ር ምትኬ አሰፋ - በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ-- የውሃ ስራዎች ምክትል ስራ አስኪያጅ
14 አቶ ሸረፋ ሌገሶ- በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ- የሰላምና ጸጥታ ቢሮ አማካሪ
15/ አቶ መላኩ ብርሃኔ- የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ - ምክትልና ንግድ ዘርፍ

16/ አቶ መስቀሉ መንጃ- - የሰለም ጸጥታ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ፣የመረጃ አሰባሰብ / አቅ/ አስ/ምላሽ አሰጣጥ ዘርፍ
17/ አቶ እያሱ ሻንቆ - የፍትህ ቢሮ ምክትል ሀላፊ
18/ ወ/ሮ በቱላ አብዳላ ፤- - በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ -ፍትህ ቢሮ አማካሪ
19/ አቶ ኑሪ ከድር ጸረ ሙስና ስነ ምግባር ኮሚሺን ምክትል ኮሚሽነር
20/ አቶ ገብሬ አስፋው - የፍትህ አካላት ማሰልጠኛና የህግ ምርምር ማዕከል ምትል ዳይሬክር
21 ወይዘሮ ታየች ሞላ- በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- በትም/ ስልጠና ጥ/ቁ/ባለስልጣን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ዘረፍ
22 አቶ ተክል አሼቦ - በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ - የህብረት ስራ ምክትል
23/ አቶ ተስፋዬ ኤርሲዶ- በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የህዝብ ተሳትፎ ማስተበባሪያ ጽ/ ቤት/ ሀላፊ
24/ አቶ ሱልጣን አሊ-- በወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የወጣት ዘርፍ ሀላፊ
24/አቶ ሁሴን ሳኒ- - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- ሳይንስና ኢንፎ፣ ቴክ/ ቢሮ አማካሪ
25/ አቶ አቢቲ አንሴቦ - አመራር አካዳሚ ምክትል
26/ አቶ ደስታ ዶሌቦ- ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ - ገበያ ልማት ዘርፍ
27/ አቶ አብረሃም ዓለሙ - መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሀላፊ
28/ አቶ አብዱል ባር ኡስማን - መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሀላፊ
29/ አቶ ሀይሉ ማቲዮስ - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ - ሚሊሻ ሃላፊ
30/ አቶ መሀመድ ኑር ሳሊሃ- በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- ባህልና ቱሪዝም ቢሮ - ቱሪዝም ዘርፍ ሀላፊ
31/ አቶ አዳነ ብሩ - ትምህርት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ-በመምሪያ ሀላፊ ማዕረግ
32/ ዶ/ር ፈ

በቀን 16/01/2018 ዓ.ም በሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ሥልጠና ቢሮ ባለሙያዎች በኮሌጁ በመገኘት  እየተሰሩ ያሉ በተለይ በ90 ቀን እቅድ...
26/09/2025

በቀን 16/01/2018 ዓ.ም በሾኔ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ሥልጠና ቢሮ ባለሙያዎች በኮሌጁ በመገኘት እየተሰሩ ያሉ በተለይ በ90 ቀን እቅድ፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ፣በውስጥ ገቢ አፈፃፀም፣በአረንጓዴ አሻራ አፈፃፀም የተሠሩ ሥራዎችን አድንቀው በቀጣይ መሻሻል ያለባቸውን ተግባራት ላይ ውይይት በማድረግ ተጠናቋል።
የሾኔ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ
ኮምኒኬሽን !!

Address

Shone Town
Shone
SHONEPOLYTECHNICCOLLEGE

Telephone

+251932005944

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shone tvet college posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category