31/07/2024
ከዚህ ስር የሚታየው ጩምቦ ይባላል በምስራቅ ወለጋ የሆሮ ጉዱሩ ህዝብ ለበአላት በተለይ ላሚያከብራቸው ለታላላቆች የሚያቀርበው ለእንግዳ ክብር የሚሰራ ነው።
ምግቡ ከአፍለኛ ቀይጤፍ በድፎ ዳቦ መጠንና ቅርፅ የሚሰራ ሲሆን በደንብ የተቀመመ አይብ ይደፋበትና በባለ 6 መሽኛ ማሰሮ ጣፍጦ የተቀመመና የነጠረ። ቅቤ ዙሪያውን ይንጯረርበታል።
ቅቤው በራሱ በማሰሮ ሲዘጋጅ ጮሮርሳ የሚባል ሲሆን በመሶብ ቀርቦ ዙሪያውን ከ10 እስከ 20 ሰው አጥግቦ ቅቤው በእጅ አይበሉባ እስከ ክናድ ፈስሶ ተጠግቦ ተበልቶ ማወራረጃው ንፁህ የማር ጠጅ ወይም ቤት ያፈራው ጠላ ሊሆን ይችላል ከተበላ በሁላ ሰላም ነው ።
ይህንን ምግብ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሚኖሩ እና ሺናሻ ከሚባሉ ብሄረሰቦች ጋር በስም አንድ የሆነ በአሰራሩ መጠነኛ ልዩነት ያለው ካውም የሽናሻዎቹ ዳቤው በውስጡ ዶሮ ወጥ ና የዶሮው ስጋ ታጭቆ እንደሚሰራና ለሰርግ እንደሚቀርብ አንድ ቆየት ያልል የሺናሻ ባህል ዶክሜንተሪ ላይ ማየቴን አስታውሳለሁ።
ማንም ለትምህርትም ይሁን ለስራ።በግሩፕ ወደ ምስራቅ ወለጋ የምትሄዱ ሰዎች በትእዛዝ ጩንቦ ስሩልን ብትሉ የማይረሳ ትዝታ ይዛችሁ ትመለሳላችሁ። via muktarovich ousmanova