18/08/2026
በየም ዞን በሁሉ ትምህርት ቤቶች ሁሉም ተማሪዎች በአንድ ጀምበር እንደሚመዘገቡ ተገለፀ።
የ2019 የትምህርት ዘመን 3ኛ ዙር የአንድ ጀንበር ተማሪዎች ምዝገባ ነሐሴ 13/2018 ዓ/ም ይካሄዳል።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ አማኑኤል ሳምቢ እንደገለፁት በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ መደበኛ 6,034 ተማሪዎች ከ1ኛ _12ኛ 22,822 ተማሪዎችን በመሠረታዊ ጎልማሶች 5,429 ጎልማሶችን እና በልዩ ፍላጎት 605 ተማሪዎች ለመቀበል መታቀዱን ገልጸዋል።
በዞኑ በአንድ ጀንበር ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም የአዲስና ነባር ተማሪዎች ምዝገባ እንደሚካሄድም አስታውቋል።
የተማሪ ምዝገባ ሥራ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከዞኑ ወደ የመዋቅሮቹ የተመደቡ የትምህርት ባለሙያዎች ፣ የሁሉም የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ አደረጃጀቶች፣ የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶች የሴቶች ልማት ህብረት፣ የቀበሌ አመራሮች፣ ሐይማኖት ተቋማት እንዲሁም የተማሪ ወላጆች የድርሻቸውን እንዲወጡ የመምሪያው ሀላፊ ጥሪ አቅርበዋል።
የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች፣ መደበኛ ከ1ኛ_12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች፣ መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርትና ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተመዝጋቢዎች በተጠቀሰው ቀን ቀርቦ እንዲመዘገቡ አቶ አማኑኤል ሳምቢ አጥብቀው ያሳሰቡ ሲሆን እቅዱ እንዲሳካ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን በአግባቡ እንዲወጡም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ለበለጠ መረጃ!
📌በቴሌግራም https://t.me/yemtimert/174
📌 በፌስቡክ https://www.facebook.com/edu.gov.et