Denbel Internet Cafe and English Learning Center

Denbel Internet Cafe and English Learning Center Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Denbel Internet Cafe and English Learning Center, School, ZWAY DUGIDA, Ogolcho.

03/08/2017

የ12ኛ ክፍል የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና በአገር አቀፍ ደረጃ ለፈተና ከቀረቡ ተማሪዎች ውስጥ 41 በመቶ የሚሆኑት ከ350 በላይ ማምጣታቸውን ሀገር ዓቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከአጠቃላይ ተፈታኞች 70 በመቶውን ድርሻ የሚይዙ ሲሆን 49.1 ከመቶ የሚሆኑት የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ከ350 በላይ ውጤት ማምጣታቸውን የኤጀንሲው ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ዘሪሁን ዱሬሳ አስታውቀዋል፡፡

በዘንድሮ የፈተና ውጤት ከአጠቃላይ ተፈታኞች ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዙት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች በተሻለ ውጤት ማምጣታቸውንም ዶ/ር ዘሪሁን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

31/07/2017
30/07/2017

የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ይፋ ይሆናል:- ኤጄንሲው

የ12ኛ ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ከሐምሌ 28 ቀን 2009 ዓ.ም ጀምሮ ይፋ እንደሚሆን አገር አቀፍ የትምህርት ምዝናና ፈተዎች ኤጄንሲ ገለጸ፡፡

ኤጄንሲው በድረገጽ እንዳሰፈረው የአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (10ኛ ክፍል) ውጤት ደግሞ ከነሐሴ 25 ቀን 2009 ዓ.ም በኋላ ይፋ ይሆናል፡፡

ሐምሌ 23፤2009

23/07/2017

ይህን ያውቁ ኖሯል/ለጠቅላላ ዕውቀት
o ወፎች አይሸኑም ፤ (እንኳንም አልሸኑ እኛ ሸንተን ምን ተጠቀምን )
o ጉንዳኖች ፈፅሞ አይተኙም፤ሳንባ የላቸውም ፤ሰራተኛ ጉንዳን እስከ 7 ዓመት ሊኖር ይችላል ፤ንግስቷ ግን እስከ 15 ዓመት ልትኖር ትችላለች:: (ድሮውንም ደህና ሰው አይበረክትም)
o ሻርክ ብቸኛው የማይታመም እንሰሳ ነው ፤ ምንም አይነት በሽታ አያጠቃውም ካንሰርን ጨምሮ:: (ተመርምሮስ ያውቃል ለመሆኑ)
o ፈረሶች እና ላሞች የሚያንቀላፉት ቆመው ነው:: (ይህን ያጠና ሰው በማንቀላፋት እና በመተኛት መሀል ያለውን ልዩነት የሚያውቅ አይመስለኝም)
o ንቦች ሁለት ሆድ ሲኖራቸው ፤አንዱ ለማር ሲሆን ሁለተኛው ለሚመገቡት ምግብ ማስቀመጫ
ያገለግላቸዋል::( እኛም አንዱ ለክትፎ ሁለተኛው ደሞ ለሽሮ ቢሰራልን የመጀመሪያው ስራ ፈት ይሆን ነበር)
o ትልቁ ነጭ ሻርክ ከሶስት ወር በላይ ሳይበላ መጓዝ ይችላል:: (የሀገሬ ሰው እድሜ ልኩን መች በልቶ ያውቃል)

o የአህያ አይን አቀማመጥ በአንድ ግዜ አራቱንም እግሮች ማየት ያስችሉታል: (እኔ ደግሞ ሶስቱንም ማየት እችላለሁ)
o ዶልፊን ውሀ ውስጥ እስከ 24ኪ.ሜ ርቀት ያለ ድምፅ በቀላሉ መስማት ይችላል:: (ይሄንን ነበር ለስለላ መጠቀም)

o ማንኛውም ሁለት የሜዳ አህያ (zebra) አንድ አይነት መስመር አይኖራቸውም:: እኛስ መች ኖሮን ያቃል
o ቢራቢሮ የሚቀምሱት(taste) በሗላ እግራቸው ነው:: (ሰዎች ደሞ በመሀል እግራቸው)
o የወንድ ሸረሪት የወሲብ አካል በአንዱ የእግሩ ጫፍ ላይ ይገኛል::( የሰውም ያው ነው)

o አሳማ በተፈጥሮዉ ወደ ሰማይ ማየት አይችልም:: ( ለዚ ነው ፈሪሀ እግዜር ያልፈጠረበት)

o የሌሊት ወፍ ምንግዜም ከዋሻ ሲወጡ ወደ ግራ ይበራሉ:: (ወንዶች ምንግዜም ከቤት ሲወጡ አይናቸው አያርፍም)

o ወንድ የወባ ትንኝ አይናደፍም ሴቷ ብቻ ናት መናደፍ የምትችለው:: እና ወንዶቹ ሆያ ሆዬ ይጫወታሉ
o የዱር አይጥ (Rat) በፍጥነት መራባት የሚችሉ ሲሆን በ18 ወራት ብቻ 2 አይጦች 1 ሚሊዮን ዘመዶችን ማፍራት ይችላሉ::
o አንድ ንብ አንድ የሾርባ ማንኪያ ማር ለማዘጋጀት ከ 4000 በላይ አበቦችን መጎብኝት አለባት ::( አንድ ሰው ሀብት ለመሰብሰብም ከዛ የበለጠ መስራት ይኖርበታል)
o ቀንድ አውጣ ለ3 አመት መተኛት ይችላል:: (ከማን ጋር)

o ዝሆኖች ከ3ማይል ላይ ማሽተት ይችላሉ:: (ጆሮህን ደፍነህ ጥሩ አሽታች ነህና )
o ኦይሰትር(Oyster) የተባለ የአሳ ዝርያ ከአንዱ ፆታ ወደ ሌላኛው እንዲሁም ወደ ነበረበት ፆታ ለወሲብ ብቻ በሚመቸው ፆታውን መቀያየር ይችላል:: (ታየኘ ይሆ ነገር ለሰውም ቢቻለው)
o ድመት በህይወት ዘመኗ እስከ 100 ግልገሎች ትወልዳለች፡፡ (የኛ ድመት ሠው ብትሆን ኖሮ ቤታችንን አበበች ጎበና ታስመሰለው ነበር ማለት
ነው ለማንኛውም ተርፈናል)
o ድብ የእድሜው ጣሪያ 80 አመት ድረስ ነው፡፡ (ጫት አይቅም አይጠጣ ሰማኒያ ድረስ ምናባቱ ይሰራል)
:
o ፍየሎች ሴቷን ፍየል ማማለል ሲፈልጉ እርስ በእርስ ይዋጋሉ፡፡ (ATM ማሽን ጋር ቀብረር ብለው ቢቆሙ አፍሰው ይሄዱ ነበር ጅሎች)
:
o የወባ ትንኝ 47 ጥርሶች አሏት፡፡ (ምን አለበት ከነከሱን አይቀር ከሰው ወደ ሰው በሽታ እንዳያስተላልፉ አንድ ጥርስ ለአንድ ሰው እያደረጉ ቢነድፉን ኪራይ ሰብሳቢ ሁላ)
:
o አይጦች የራሳቸው ያልሆነ ልጅ አጥብተው ያሳድጋሉ፡፡ (ሰዎች ግን የራሳቸውን ልጅ በጡጦ ያሳድጋሉ)
:
o አዞ ምላሱን ወደ ውጪ ማውጣት አይችልም፡፡ (ብር ቆጥሮ አያውቅም ማለት ነው)
:
o ቀበሮ በዘመኑ አንዴ ብቻ ነው ፍቅረኛ የሚኖረው ምናልባት ሚስቱ ብትሞት እንኳን ሌላ ሚስት አይፈልግም፡፡ (ማን ያውቃል ሰው ሳያይ ሹገር ዳዲ
ይሆናል)
:
o ሴቷ ካንጋሮ ከወንዱ ካንጋሮ የምትለየው ደረቷ ላይ ባለው ከረጢት ነው፡፡ (ሴቶች ደረታቸው ላይ ሚልክ ሀውስ ሲኖራቸው እኛ ደሞ እንደሌለን
ማለት መሰለኝ)

ቡና ጠጡና “ዕድሜ ጥገቡ” - ጥናትአንዲት ስኒ ቡና! አቦል ካለበለዚያም እስከ በረካው - የብዙ ሰው ሱስና የለት ተለት ቀጠሮው ነው። በተለይ በጠዋት “ፉት” የተባለች እንደሁ አህ!!! መልካ...
22/07/2017

ቡና ጠጡና “ዕድሜ ጥገቡ” - ጥናት

አንዲት ስኒ ቡና! አቦል ካለበለዚያም እስከ በረካው - የብዙ ሰው ሱስና የለት ተለት ቀጠሮው ነው። በተለይ በጠዋት “ፉት” የተባለች እንደሁ አህ!!! መልካም ቀን ተጀመረ ማለት ነው…
አንድ ሰሞኑን የወጣ አዲስ የጥናት ሪፖርት ደግሞ “ምን ቀን ብቻ? ዕድሜ ሙሉ እንጂ!” ይላል። በቀን ሦስት ስኒ ቡና የሚያጣጥሙ ሰዎች ከማይጠጡቱ ለተሻለ የዘመን ርዝማኔ እንዲሁ እንዳጣጣሙት ይኖራሉ፡፡
ሳይንቲስቶቹ ጥናቱን ያደረጉት ዕድሜአቸው ከ35 ዓመት በላይ በሆነ ቁጥራቸው ከግማሽ ሚሊየን በበዛ በአሥር የአውሮፓ ሃገሮች ውስጥ በሚኖሩ ጤናማ ሰዎች ላይ መሆኑን ሪፖርታቸው አሳይቷል።
“ባንዲት ስኒ ቡና ዋጋዋ ባነሰ፣ (የዛሬን አያድርገውና) ስንት ዕድሜ ረዘመ ስንቱ ሰው ታደሰ።” ብሎ ይፅፍ ይሆን ጠቃሽ?! ለማንኛውም “ቡና ጠጡ!”

>>>

Ethiopia | VOA- Amharic News July 21 , 2017...

13/07/2017

አስፋልት ለዝዋይ ዱግዳ ?
በ 5/6/2008 ጥዋት 2 ሰዓት ላይ በ ኢቢሲ (EBC) በተላለፈው ዜና በ ዝዋይ ዱግዳ ወረዳ የሚገኙ አርሶ አደሮች ማግኘት ከሚገባቸው ምርት ውስጥ 96 ከመቶ የሚሆነውን ማጣታቸውንና በቀጣይ የመስኖን ስራ በማስፋፋት ዘላቂ መፍትሄ መንግስት እንደሚሰጥ መገለጡ ቢያሲደስተንም ፤ የወረዳችንን ሁለንተናዊ ችግር ሊፈታ የሚችለው የአስፓልት መንገድ መዘንጋቱ ግን መፍትሄው ዘላቂ መሆኑን ? ያደርግበታል በመስኖ ለጉድ ተመርቶ በአስተማማኝና ፈጣን መንገድ እጦት በርካሽ ሲሸጥ ? ወረዳችን ለዋና ከተማችን ባላት ቀረቤታ አስፓልት ኖራት ቢሆን ኖሮ ይሄኔ እነ ባቱ፤ ሻሸመኔና ሀዋሳ ያገኛቸውን ትላልቅ ካምፓኒዋች ለመሳብ በተሻለች ነበር፤ የከርሰ ምድር ውሃዋ፤ ከታር ወንዝና ደንበል ሃይቅ የጥቃቅን ባለሀብቶች ጥቃቅን ወተር ፓምፖች ማላገጫ ለመሆን ባልተገደዱ፤ የወረዳችን አርሶ አደሮች እንደዚ የከፋ ድርቅ ሲከሰት በነኚ ካምፓኒዎች ውስጥ በቀን ስራ እንካን ተቀጥረው ችግሩን ባለፉት ኖሮ፤ ልጆቻችን የቀን ስራ ፍለጋ ዝዋይ፤ሞጆና ቢሾፍቱ ጎዳናዎች ላይ ባልተንከራተቱ፤ ለሎጅ ና ለተለያ መዝናኛዎች ምቹ የሆኑት የተፈጥሮ ጸጋዋቻችን አፋቸውን ባልከፈቱ፡፡ የወረዳችን አስፓልት ማጣት በደሉ መች በዚ በቃና፤ አዋራው በዋናው መንገድ ላይ ዘመናዊ ሆቴሎች፤ የኤሌክትሮኒክስ፤ የልብስና የጌጣ ጌጥ መሸጫ ሱቆች ማየት ነስቶን በአሰላ አስፓልትላይ መጋተትና መመላለስ መለያችን ሆናል፡፡ አንድ ልጨምር ወረዳችን ተዝቆ የማልቅ ለግንባታ ስራ የሚውሉ አሸዋ፤ ሪዳሽ፤ ኮሚቼና ኖራ አፈር ቢኖራትም እሴት ተጨምሮባቸው እንደ ቡሎኬት፤ ፖል፤ ሲሚንቶና ወደ ሌሎች የግንባታ ግብአቶች ተቀይረው እስከ ዋና ከተማችን ደረስ እንዳይቀርቡ ባለ ሀብቱ በየትኛው መንገድ መቶ ሀብቱን ያፍስ፡፡ እንዲሁ ልነካካው ብየ እንጂ አስፓልት ለዚች ወረዳ ምን ማለት እንደሆነ መግለፁ . . .፡፡ ግን ትልቁ እውነታ መንገድ ሁሉን ያመጣል፤ ሁሉን ይወስዳል፡፡ ለኛ ደሞ ችግራችንን ሸኝቶ ኑራችንን ያሻሽላል፡፡ እናም አሁን የዝዋይ ዱግዳ ካቢኔዋች፤ አባቶች፤ ባለ ሃብቶች ፤ በተለያየ ቦታ የምትገኙ በየደረጃው ተሰሚነት ያላቹ ልጆቻችን፤ ቀለም ቀመሶቹ የመንግስት ሰራተኞችና ወዳጆቻችን በአንድላይ ድምጻችንን ለሚመለከተው አካል ባለን አቅም የምናሰማበት ወቅት ነውና በያገባኛል ስሜት ተፈላልገን አንድ እርምጃ ብንጀምር መንገዱ ሁለት ዞኖችን ከማገናኘቱ ና በአሁኑ ሰዓት እያስተናገደው ካለው የተሸከርካሪ ፍሰት አንፃር የሚጮህ ከተገኘ ይሰማል፤ ከአንካካን ይከፈታል፡፡ እስኪ መስማማቶዋንና ወዳጃችን መሆንዎን like, share or comment በማድረግ ያሳዩን?

05/07/2017

………" የምትችል ከሆነ ከማንም የበለጠ ደግ ሁን፤ ቢሆንም ደግነትህን
አትናገር!!"
፦………" ራሱን ያጎበጠ ሰው መቼም ሌሎችን አቅንቶ አያውቅም!!"
፦………" ችግርን በጥቅም ላይ እንደማዋል ጣፋጭ ነገር የለም!!"
፦……" የእብደት የመጀመሪያ ምልክት እራስን አዋቂ አድርጎ ማሰብ ነው!"
፦……" መጥፎ ቀን የምንለው መጥፎ ሃሳብ ያሰብንበት ቀን ነው!!"
፦………" ድህነትን አትፈርበት! የሚያሳፍርህ ነገር ቢኖር የአዕምሮ ድህነት
መሆኑን እወቅ!!"
፦………" ቃል ለመግባት የዘገየህ፤ ከገባህ ደግሞ የፈጠንክ ሁኑ!!"
፦………"የአንተን ውድቀት ለሚመኙ ስትል ራስህን አሻሽል!!"
፦………" መጀመሪያ ራስህን እወቅ! ጠንካራ ጎኖችህን ይበልጥ አጠንክርህ
በድክመትህ ላይ ፈጥነህ ዝመትባቸው!!"
፦………" የተፃፈውን ሁሉ አንብበህ በህሊና መዝገብህ ከመፃፍህ በፊት
በህሊናህ ሚዛንህ አብጠርጥር!!"
፦………" ምላስህን ካልጠበካት እስዋ አትጠብቅህም!!"
፦………"መከራን እና የተወረወረ ድንጋይን ዝቅ ብሎ ማለፍ ብልህነት
ነው!!"
፦………" መስጠት የማያውቁ ሰዎች ሌሎች ሲሰጡ ይታመማሉ!!"
፦……" ራሱን ያወቀ ሰው ሁልጊዜ በኑሮው ደስተኛ ነው!!"
፦………" ጠንካራ ሞራል የህይወት ተስፋ ነው!!"
፦………" ጨዋ አንደበት የተዘጉ በሮችን ይከፍታል!!"
፦………" ዛሬን ስለነገ በመጨነቅ ካሳለፍከው ዛሬን በቅጡ መኖር
ተስኖሃል!!"
፦………" ቁርጡን ያወቀ ሰው ምርጫ ይኖረዋል!!"

04/07/2017

የትምህርት ጥራቱ በአስደንጋጭ ሁኔታ አሽቆልቁሏል
ተባለ፡፡
ከዓለም የትምህርት ደረጃ ምደባ አንፃር፣150ዓመት ያህል የትምህርት ጥራት ወደ ኃላ ቀርቷል፡፡
✍አዲስ አድማስ ጋዜጣ
- የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ማንበብና መፃፍም ሆነ ሂሳብ ማስላት
አይችሉም
- የኮሌጅ ተመራቂዎች የ8ኛ ክፍል ፈተናን በብቃት ማለፍ
አልቻሉም
በአሁኑ ወቅት የአገሪቱ የትምህርት ጥራት ደረጃ በአስደንጋጭ
ሁኔታ እያሽቆለቆለ መምጣቱን ሰሞኑን ይፋ የተደረገ አንድ ጥናት
አመለከተ፡፡
የኮተቤ መምህራን ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከእንግሊዙ
ዱርሃም ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያደረገው ጥናት፤ በአማራ፣
በደቡብ ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኙ 10
ኮሌጆች ላይ ያተኮረ ሲሆን የትምህርት ጥራቱ በአስደንጋጭ
ሁኔታ እያሽቆለቆለ መምጣቱን ይጠቁማል፡፡ ጥናቱን በኮተቤ
ኮሌጅ አዳራሽ ያቀረቡት የፊዚክስ ተመራማሪና መምህር ዶ/ር
መስፍን ታደሰ፣ “ተማሪዎች በተለይም በፊዚክስና በሂሳብ
ትምህርቶች እጅግ ደካማ ሆነዋል” ብለዋል፡፡ የትምህርት
ጥራቱን አስመልክቶ የተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና
አጥኚዎች ያደረጉትም ሆነ በራሱ በዩኒቨርሲቲው የተካሄዱ
ጥናቶች እንደሚያመለክቱት፤ የአገሪቱ የትምህርት ጥራት
ከዓለም አቀፉ መስፈርት እጅግ ያነሰ ደረጃ ላይ ይገኛል በማለት
ዶ/ር መስፍን አብራርተዋል፡፡
በ2013 እ.ኤ.አ በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም
(UNDP) የተሰራውን አንድ ጥናት ዋቢ በማድረግ ተመራማሪው
እንደገለፁት፤ በአገሪቱ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን
ለመከታተል ብዙ ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ይገባሉ፤ ይህንን
ለማድረግ የሚያስችል ዕድልም በስፋት አለ፤ ሆኖም ተማሪዎቹ
ከት/ቤት ሲወጡ ማንበብና መፃፍም ሆነ ሂሳብ ማስላት
አይችሉም፡፡
“የትምህርት ጥራቱ እጅግ አሳፋሪ ደረጃ ላይ ደርሷል” ያሉት ዶ/
ር መስፍን፤ “የልጆቹ የዕውቀት ደረጃም በአለማቀፍ ደረጃ
ከሰፈረው አማካይ ቫልዩ አንፃር 150 ዓመታት ወደ ኋላ መቅረቱ
በጥናት ተረጋግጧል” ብለዋል፡፡ አለማቀፍ ፈተናዎችን በመስራት
ረገድም ቢሆን በኢትዮጵያ የተመዘገበው ውጤት በጣም ዝቅተኛ
መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ጥናቱ በመምህራን ኮሌጆችና በተለያዩ ት/ቤቶች ላይ መደረጉን
የጠቀሱት ዶ/ር መስፍን፤ “ከኮሌጅ ተመርቀው 7ኛና 8ኛ
ክፍሎችን ለማስተማር ዝግጁ ከሆኑ መምህራን መካከል ለዚሁ
ጥናት የተመረጡት የ12ኛ ክፍል ፈተናን ተፈትነው ማለፍ
አለመቻላቸውንና የ8ኛ ክፍል ፈተናንም በብቃት ማለፍ
እንዳልቻሉ ገልፀዋል፡፡ “የጥናት ውጤቱ የሚያመለክተው
ከኮሌጅ እየተመረቁ የሚወጡት መምህራን፣ ከደረጃ በታች
መሆናቸውን ነው፤ ይህ ደግሞ እጅግ አሳሳቢ ነው” ብለዋል፡፡
የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚደረገውን ጥረት ያግዛል
በሚል ከእንግሊዙ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቅርቡ
የተደረገው ይሄው ጥናት፤ የተማሪዎችን የአስተሳሰብ አቅም
ከሌሎች አገራት ጋር በማነፃፀር ውጤቱን ይፋ አድርጓል፡፡
“በኢትዮጵያ የሚገኙ የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች አስተሳሰብ፣
አሜሪካና ሲንጋፖር በመሳሰሉ የአደጉ አገራት ከሚገኙት የአንደኛ
ክፍል ተማሪዎች አስተሳሰብ ጋር እኩል ነው” ይላል፡፡
በትምህርት ጥራት ረገድ የሚታየው ችግር ተጨባጭና በእግሩ
ቆሞ የሚሄድ ነው ያሉት ዶ/ር መስፍን፤ የትምህርት ጥራቱን
ለማሻሻል መሰረታዊ ችግሮችን በማስወገድ ለለውጥ መነሳት
ይኖርብናል ብለዋል፡፡ ለትምህርት ጥራት ማሽቆልቆል ዋነኛ
ምክንያቶች ተብለው ከተጠቀሱት ጉዳዮች መካከል የሥርዓተ
ትምህርቱ (ካሪኩለም) ክብደት፣ ለጋሾችን መሰረት ያደረገው
የትምህርት ሥርዓትና ለመምህርነት ሙያ የሚሰጠው አነስተኛ
ግምት የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡ “በተለይም ለመምህርነት

Address

ZWAY DUGIDA
Ogolcho

Telephone

0911829269

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Denbel Internet Cafe and English Learning Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category