03/08/2017
የ12ኛ ክፍል የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና በአገር አቀፍ ደረጃ ለፈተና ከቀረቡ ተማሪዎች ውስጥ 41 በመቶ የሚሆኑት ከ350 በላይ ማምጣታቸውን ሀገር ዓቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡
የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከአጠቃላይ ተፈታኞች 70 በመቶውን ድርሻ የሚይዙ ሲሆን 49.1 ከመቶ የሚሆኑት የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ከ350 በላይ ውጤት ማምጣታቸውን የኤጀንሲው ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ዘሪሁን ዱሬሳ አስታውቀዋል፡፡
በዘንድሮ የፈተና ውጤት ከአጠቃላይ ተፈታኞች ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዙት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች በተሻለ ውጤት ማምጣታቸውንም ዶ/ር ዘሪሁን ጨምረው ገልጸዋል፡፡