Muja Maryam Secondary School

Muja Maryam Secondary School This page help for its follower to get daily Information about everything done by the school

1. የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ተሳትፎ ለላቀ እድገትና ትራንስፎርመሽን                                            ህዳር 29/2008 ዓ/ምበየዓመቱ ህዳር 29 በአገ...
13/12/2015

1. የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ተሳትፎ ለላቀ እድገትና ትራንስፎርመሽን
ህዳር 29/2008 ዓ/ም
በየዓመቱ ህዳር 29 በአገር አቀፍ ደረጃ የሚከበረዉ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓል ዘንድሮ ለ10ኛ ጊዜ በብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ተሳትፎ ለላቀ እድገት እና ትራንስፎርመሽን በሚል መሪ ቃል በጋምቤላ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት በጋምቤላ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ይከበራል።
በዓሉም የሚከበረዉ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች የደርግ ስርዓትን በመገርሰስ በአገራችን አዲሱ የፌደራል ህገ-መንግስት በጋራ ስምምነት ተመካክረዉ ያፀደቁበት የጋራ የቃልኪዳን ሰነድ በመሆኑ ነዉ። አዲሱ ህገ-መንግስት እንደከዚህ በፊት የነበሩት ህገመንግስታት በጥቂት ግለሰቦች ተዘጋጅቶ ለኢትዮጸያ ህዝብ የተሰጠ ሰነድ አይደለም ። ይበልጥ የህገመንግቱን ረቂቅ ያዘጋጀዉ ልዩ ልዩ አመለካከቶችን የሚወክሉ ግለሰቦች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የመስኩ ባለሙያዎች እና የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ተወካዮች በአባልነት በተካተቱበት የህገመንግስት አርቃቂ ኮሚሽን(constitutional drafting commission ) ሲሆን በረቂቁም ላይ የኢትዮጵያ ህዝቦች ከተወያዩበት በመጨረሻ ተወካዮቻቸዉን መርጠዉ በላኳቸዉ አባላት በተቋቋመዉ 538 ኣባላት ያሉት የህገ-መንግስት አፅዳቂ ጉባኤ ህዳር 29 ቀን 1987ዓ/ም ፀድቋል። የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄሮሰቦችና ህዝቦች የሉዓላዊነታቸዉ መገለጫ የሆነዉን ህገ-መንግስት ልዩ ልዩ ባህሪያት ከሚባሉት መካከል፡- የኢትዮጵያ የስልጣን በለቤቶች ማድረጉ፣ ሃይማኖታዊ መንግስት እዉቅና አለመስጠቱ፣ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች የራሳቸዉን እድል በራሳቸዉ የመወሰን መብትና እስከ መገንጠል መብት የሰጠ በመሆኑ፣ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በራሳቸዉ ቋንቋ የመናገር፣የመጽሃፍ፣ የማሳደግና ባህሉን የመግለጽ፣ የማዳበርና የማስፋፋት እንዲሁም ታሪኩን የመንካባከብ መብትን እንዲጠቀሙ ያደረገ በመሆኑ፣ ህዝቡ የመሬት ባለቤት ማድረጉ፣ የፈደሬሽን ምክርቤት በስርዓቱ የተሰጠዉ ሚና የተለየ በመሆኑ ከሌሎች ማለትም 1931 ፣ 1955 እና 1987 ዓ/ም ህገ መንግስታት ለየት ያደርገዋል። ስለዚህ ሃገሪቱ የጀመረችዉን የልማት፣ የሰላምና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እና መካከለኛ ገቢ ካላቸዉ አገሮች ተርታ ለማሰለፍ ዘንድ ህገ-መንግስቱ በሁሉም ዜጎች ሊታወቅና ሳይሸራረፍ ሊተገበር ይገባል።
የበዓሉ መከበር ፋይዳዉ ወይም አስፈላጊነቱ
የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ልዩነታቸዉን ጠብቀዉ በአንድነት ፣ በፍቅር እና በመቻቻል እንዲኖሩ የሚያደርጋቸዉ የጋራ እሴት እንዳላቸዉ ለዓለም አቀፍ ማህረሰብ ለማስተዋወቅ እድል ይፈጥርላቸዋል
ብዙ ቋንቋዎች ስንናገር የማንስማማ ይመስለላቸዉ ለነበሩ ሰዎች መግባባት እንደምንችል በተግባር ለማሳየት ያስችላል
የኢትዮጵያን ብዙህነት አጉልቶ ለማሳየት ፣ የብዙህነታችን እና የጥንካሬያችን ምልክት መሆኑን ለማሳየት፤ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች በአዲስ መንፈስ አንድነታቸዉን ኣጠናክረዉ ድህነትና ኃላቀርርነትን በተባበረ ክንዳቸዉ በማጥፋት የሃገራችን ህዳሴ እዉን ለማድረግ ያስችላል፡፡
ህገ-መንግስታዊ መርሆዎችን ሳይሸራረፉ ለመተግበርና ለማስቀጠል፣ በልዩነት መካከል ያለዉን አንድነት ለማጠናከር ፣የጋራ እሴቶችን ለመገንባት ፣ጠንካራ ሀገራዊ የባለቤትነት ስሜት ፣ በህዝቦች መካከል የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል እንዲፈጠር፣ መልካም ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ፣ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
በአጠቃላይ ሀገራችን የያዘቹ የልማት ፣ የሰላምና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ይበልጥ እውን ለማድረግ ቀጣይ ለምንሰራቸዉ ስራዎች ቃል የምንገባበት እለት ነዉ።
የብሄሮች፣ብሄረሰቦችና ህዝስቦች ቀን የተከበረባቸዉ ቦታዎችና የነበሩ መሪ ቃሎች

በ1999ዓ/ም በፌደሬሽን ምክርቤት አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ከተማ ተከበረ ”ህገ-መንግስታችን ቃልኪዳናችን የአብሮነት መገለጫ ነዉ”
በ2000 ዓ/ም በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት በሃዋሳ ከተማ ”የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰኖችና ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ አንድነት ለልማት ”
በ2001 ዓ/ም በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ከተማ ”ዴሞክራሲያዊ ፍትሃዊነት በመጠቀም አንድነታችን እናጠናክራለን ”
በ2002 ዓ/ም በሀረር፣ አፋር፣ ሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ ከተማ አሰተዳደር የጋራ አዘጋጅነት በድሬዳዋ ከተማ “ መቻቻል ለዴምክራሲ ለአንድነትና ለልማት“
በ2003 ዓ/ም ከዓለም አቀፍ የፌደራሊዝም ስብሰባ ዋዜማ በአዲስ አበባ ከተማ “የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች እጅ ለእጅ ተያይዘን የሃገራችንን ህዳሴ የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ እናደርሳለን“
በ2004 ዓ/ም በትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት በመቀለ ከተማ “ህገ-መንግስታችን ለብዝሃነታችን ለአንድነታችንና ለህዳሴያችን“
በ2005 ዓ/ም በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት በባህርዳር ከተማ “ብዙም አንድም ሆነን በመለስ ራእይ በህገ-መንግስታችን ለህዳሴያችን “
በ2006 ዓ/ም በኢትዮጵያ ሶማሊያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት በጅግጅጋ ከተማ “ህገ-መንግስታችን ለህዳሴያችን “
በ2007 ዓ/ም በቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት በአሶሳ ከተማ “በህገ-መንግስታችን የደመቀ ኢትዮጵያዊነታችን ለህዳሴያችን“
በ2008 ዓ/ም በጋምቤላ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት በጋምቤከላ ከተማ “የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ተሳትፎ ለላቀ እድገት እና ትራንስፎርመሽን “

የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር የትምህርት ክፍል የሙ/ማ/አጠ/2ኛ/ደ እና የከፍ/ት/መሰ/ት/ቤት ተማሪዎችን የተማሪ መማክርት ሲያስመርጡ
13/12/2015

የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር የትምህርት ክፍል የሙ/ማ/አጠ/2ኛ/ደ እና የከፍ/ት/መሰ/ት/ቤት ተማሪዎችን የተማሪ መማክርት ሲያስመርጡ

07/03/2015

የሙጃ ማርያም አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ እና የከፍተኛ ትምህርት መሰናዶ ት/ቤት አጭር ታሪከ
የሙጃ ማርያም ት/ቤት በ1963 ዓ.ም የተቋቋመ ሲሆን በወቅቱም ያስተናግደዉ የነበረዉ ከ1ኛ-8ኛ ክፍል ቢሆንም መንግስት ለትም/ት ተደራሽነት በሰጠዉ ከፍተኛ ትኩረት ምክንያት በ1998 ዓ.ም ወደ 2ኛ ደረጃና የከፍተኛ ት/ት መሰናዶ ሊሸጋገር ችሏል፡፡ ት/ቤቱም በ01 ቀበሌ በግዳን ወረዳ በሰሜን ወሎ ዞን በ33172 ሜትር ስኩየር ቦታ ሰፍሮ የሚገኝ ሲሆን ከዞኑ 76 ኪ.ሜ፣ ከክልሉ 328 ኪ.ሜ እና ከአገሪቱ መዲና ደግሞ በ596 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡የ2ኛ ደረጃን ለማቋቋም ከበፊት ማለትም የመጀመሪያ ደረጃ በተጨማሪ 9450000 ብር ወጭ እንዳስወጣ ይነገራል፡፡ ት/ቤቱ የ2ኛ ደረጃ እና የከፍተኛ ትምህርት መሰናዶ ስራዉን ሲጀምር በ18 ወንድ እና 7 የሴት በጥቅሉ 25 መምህራን ሲሆን በጊዜዉ ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎች ብዛት 822 የወንድ እና 300 የሴት በድምሩ 1122 ተማሪዎች ናቸዉ፡፡ ባሁኑ ወቅትም ማለትም 2007ዓ.ም 58 የወንድ እና 13 የሴት በድምሩ 71 መምህራኖች ያሉት ሲሆን በተጨማሪም 8ወንድ እና 5 የሴት በጥቅሉ 13 የአስተዳደር ሰራተኞች ይገኛሉ፡፡
መረጃ፡-
የት/ት ዘመን ለመማር የተመዘገቡ ምርመራ
ወንድ ሴት ድምር
1998 822 300 1122
1999 1079 348 1427
2000 892 348 1240
2001 1045 658 1703
2002 785 600 1385
2003 543 449 992
2004 492 440 932
2005 640 529 1169
2006 707 569 1276
2007 778 739 1527

በ2007 ዓ.ም በት/ቤቱ ያሉ ተማሪዎች አደረጃጀቶች
የክፍል ደረጃ የልማት ቡድን ብዛት የልማት ቡድኑ መሪዎች የ1 ለ 5 ተጠሪዎች
ወ ሴ ድ ወ ሴ ድ
9ኛ 20 20 20 40 88 52 140
10ኛ 10 10 10 20 50 16 66
11ኛ 3 3 3 6 21 1 22
12ኛ 3 3 3 6 15 2 17
ድምር 36 36 36 72 174 71 245


1998 ዓ.ም
የመምህር ብዛት፡ ወ = 18፣ ሴት=7፣ ድምር = 25
የተማሪዎች ብዛት፡ ወ = 822፣ ሴ = 300 ድምር = 1122
የግንባታ ወጭ 9,480,000 የኢት ብር

2007 ዓ/ም፡
የመምህር ብዛት፡ ወ = 58፣ ሴ = 13፣ ድምር = 71
የተማሪዎች ብዛት፡ ወ = 778፣ ሴ = 739፣ ድምር=1527

24/02/2015

ስለ ሙጃ ማርያም አጠቃላይ የከፍተኛ ትምህርት መሰናዶ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እና አጠቃላይ ስለግዳን ወረዳ ማወቅ የምትፈልጉ ማንኛዉም የሶሻል ኔትዎርክ ተጠቃሚዎች በሙሉ https://www.facebook.com/pages/Muja-Maryam-Secondary-School/824168960973035 ይህን ሊንክ በመጫን መጠቀም ትቸህላላቸሁ፡፡
ለበለጠ መረጃ [email protected] ያነጋግሩን. ፈጣን ምላሽ እንሰጣለን፡፡

This page help for its follower to get daily Information about everything done by the school

የሙጃ ማርያም አጠቃላይ የከፍተኛ ትምህርት መሰናዶ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የእግር ኳስ ቡድን፡ ና በለዉ……..ና፣………..ቴክኒክና ሙያና በለዉ……..ና፣………...ግብርናና በለዉ……..ና፣…………አሰተ...
18/02/2015

የሙጃ ማርያም አጠቃላይ የከፍተኛ ትምህርት መሰናዶ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የእግር ኳስ ቡድን፡
ና በለዉ……..ና፣………..ቴክኒክና ሙያ
ና በለዉ……..ና፣………...ግብርና
ና በለዉ……..ና፣…………አሰተዳደር
ና በለዉ……..ና፣…………..ሲቭል ሰርቪስ
ና በለዉ……..ና፣………….ኮሙንኬሽን
ና በለዉ……..ና፣……..….ሁሉንም

16/02/2015

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በየካቲት 5/07 ዓ.ም ውሎው በሰሜን ወሎ ዞን የሚገኙ የ9 ወረዳዎችን የትምህርት እንቅስቃሴ ጎበኝቷል፡፡
በዚህ የተሞክሮ ልውውጥ ጉብኝት በ9 ወረዳዎች የሚገኙ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የመጀመሪያ ደረጃና የ2ኛ ደረጃ የትምህርት ተቋማት የተጎበኙ ሲሆን በዚህም ጉብኝት የቅድመ መደበኛና የተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርትም የጉብኝቱ አካል ነበሩ፡፡ 500 የሚሆኑ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች የተሳተፉበት ትምህርታዊ ጉብኝት ተጠናቋል፡፡ ከተጎበኙት ወረዳዎች አንዱ ሙጃ ማርያም አጠቃላይ የከፍተኛ ትምህርት መሰናዶ ት/ቤት ሲሆን ት/ቤቱ በሁሉም የትምህርት ዘርፎች በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ነዉ በተለይም ደግሞ በኢ.ኮ.ቴ የትምህርት ዘርፍ በዞኑ ብሎም በክልሉ ሞዴል የሚሆን ስራ ተሰርቷል ሲሉ በዕለቱ የተገኙት የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተናግረዋል፡፡

12/02/2015

Fig1. Mount Aboye gara site

ESSS has taken a giant step forward to realize one of its main objectives, that is, to enable Ethiopia to reap the benefits accruing from space science and technology, through International Astronomical Observatory in the highland of Lalibela.

Experts have pinpointed the highlands Around Lalibela as the promising sites for a future astronomical and space observatory from which to explore space. Observatory site selection involves in-depth investigation and years of study and evaluation.

According to a preliminary study undertaken around Lalibela, which include Mount Abune Yosef (Lasta district,4280 M Above Sea Level), Mount Abohaye gara(Gidan District 4140 M, above sea level) and Mount Mahe Wadla (Gashena District, 3800 M Above Sea Level), are considered potential sites for an international observatory. Some of the observational factors that affect astronomical research include cloud cover, temperature, rain fall, sky-brightness, humidity, wind speed, atmospheric turbulence, aerosol, seismicity, integrated soil and factors related to altitude. Among these factors, the meteorological factor that has been collected from Ethiopian metrological agency around these mountains show the feasible potential of the sites.

In all these potential sites, living quarters have now been fully completed. Millions of birr worth equipments to conduct the feasibility study is being transported to the nearest town of Mount Abune Yosef and Mount Abohaye gara sites. The third site, Mount Mahe Wadla delayed at least for one year. It is believed by September the two sites, Mount Abune Yosef and Mount Abohaye gara will be functional and all trained personnel from different universities in the area will commence their study and research.

Fig2. Shipping the necessary equipments to the sites

The success of this project so far would have not been possible if it were not be for the region’s government administration, zone and woreda official’s momentous contribution. Even local residents and farmers in all sites have shown a sense of urgency by participating in various activities to see the fruits of this project. What a moving, heartwarming story is that they often cross up to 7 km of the treacherous mountains to see if they can help in any ways.

Fig3. Engineers and Professionals at Telescope resting Site at Mount Aboy gara

ESSS unrelenting effort for the development of space science and technology in the country managed to boost support from corporate sectors as well. MH engineering deserves a special thanks and acknowledgment for being a major player from day one in assisting the society through advising and providing various engineering services for both Entoto Observatory site and Lalibela project free of charge.

Fig4. Mr. Tefera Waluwa briefing the local residents

During the visit to the Mount Aboye gara site by engineers and other professional, Mr. Tefera Waluwa, Board chairman of the society remarks “There are also a lot of individuals who dedicate their time and effort, and I think we should recognize and appreciate them. In addition, I believe this kind of gesture motivates the people who are already volunteering, and those who plan to do so." He further added that,” our society is leading by example and intends to promote what volunteer work can bring to a society and solve valuable challenges in our communities and furthermore, can better empower ourselves and others to create political, economic and social change”

ESSS IEC (Information, Education and Communication) Committee

July 22, 2013

ተማሪዎች በመማሪያ ክፍል ዉስጥ
23/01/2015

ተማሪዎች በመማሪያ ክፍል ዉስጥ

የጆሮ ማዳመጫ (Earphone) ሲጠቀሙ የሚያደምጡት የድምፅ መጠን ዝቅተኛ ሊሆን እንደሚገባው ባለሞያዎች መከሩአሁን አሁን በተለይ በወጣቱ ዘንድ እየተስፋፉ ከመጡ ልምዶች መካከል ሙዚቃዎችን፣ ...
23/01/2015

የጆሮ ማዳመጫ (Earphone) ሲጠቀሙ የሚያደምጡት የድምፅ መጠን ዝቅተኛ ሊሆን እንደሚገባው ባለሞያዎች መከሩ
አሁን አሁን በተለይ በወጣቱ ዘንድ እየተስፋፉ ከመጡ ልምዶች መካከል ሙዚቃዎችን፣ ፊልሞችንና የሬዲዮ ፕሮግራሞችን በጆሮ ማዳመጫ እየሰሙ መንቀሳቀስ ይጠቀሳል፡፡
ነገር ግን ስንቶቻችን እንሆን ወደ ጆሯችን የሚደርሰውን የድምፅ መጠን አመጣጥነን የምንለቀው?
በአይነትነና በጥራት እየተበራከቱ የመጡት የጆሮ ማዳመጫ መሳሪያዎች ወደ ጆሯችን የሚልኩትን የድምፅ መጠን ዝቅተኛ ማድረግ እንደሚገባንና ፤ይህን ማድረግ ካልቻልን በጊዜ ብዛት ለከፍተኛ ድምጾች መጋለጥ የመስማት ችሎታችንን ሊያሳጣን እንደሚችል ባለሞያዎች አስጠንቅቀዋል፡፡
ሰው በተሰበሰበባቸውና ጫጫታ በሚበዛባቸው አካባቢዎች የጆሮ ማዳመጫ መሳሪያዎች መጠቀም ካለብን የምንሰማውን ድምፅ መጠን ከመጨመር ይልቅ የምንጠቀምበትን የጆሮ ማዳመጫ ልንቀይር ይገባል፡፡ ለምሣሌ ለእንደነዚህ አይነት ቦታዎች ከውጭ የሚመጣውን ድምፅ ወደ ጆሯችን የማያሳልፉ ወደ ጆሮ ውስጥ የሚገቡ ወይም ጆሯችንን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍኑ ማዳመጫዎችን ብንጠቀም ይመረጣል ይላሉ ባለሞያዎቹ፡፡
እርስዎም የጆሮ ማዳመጫ የሚጠቀሙ ከሆነ ከላይ የቀረበውን ምክር ተግባራዊ በማድረግ ጆሮዎትን ይታደጉ፡፡
ምንጭ፡- http://www.cnet.com

CNET is the world's leader in tech product reviews, news, prices, videos, forums, how to's and more.

. የተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋቶች ደህንነትተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋቶች ማለት ኢንፎርሜሽኖችን (ዳታዎችን) ለማስቀመጥና ለማንቀሳቀስ የምንጠቀምባቸው ኤሌክትሮኒክ መሳርያዎች ሲሆኑ ሲዲ፣ ዲ...
23/01/2015

. የተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋቶች ደህንነት

ተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋቶች ማለት ኢንፎርሜሽኖችን (ዳታዎችን) ለማስቀመጥና ለማንቀሳቀስ የምንጠቀምባቸው ኤሌክትሮኒክ መሳርያዎች ሲሆኑ ሲዲ፣ ዲቪዲ፣ ፍሎፒ፣ ዩኤስቢ፣ ኤስዲ ካርዶች፣ ሃርድ ዲስኮች እና የመሳሰሉትን ያጠቃልላሉ፡፡
በየቀኑ ለተለያዩ አላማዎች የምንጠቀምባቸው እነዚህ የኢንፎርሜሽን ቋቶች ታዲያ የተለያየ የደህንነት ስጋቶችን ይዘው ይመጣሉ፡፡ ለምሳሌ በዋናነት የማልዌር ስጋት ማለትም በቀላሉ በቫይረሶች የመጠቃትና ቫይረሶችን የማሰራጨት ስጋት፣ በአካል ደግሞ የመሰረቅ፣ የመጥፋት ብሎም ጉዳት የመድረስ ስጋቶች ይጠቀሳሉ፡፡ በመሆኑም በውስጣቸው ያሉ ኢንፎርሜሽኖችና የሚገናኙበትን ኮምፒዩተርና የኢንፎርሜሽን ስርአት ደህንነት አደጋ ላይ ይጥላሉ፡፡
ቀጥለው ያሉ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በመጠቀምም እነዚህን ስጋቶች መቀነስ ይችላሉ!!
-->የማያዉቁትን ተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋት ከኮምፒዩተርዎ ጋር አለማገናኘት፣ ካገናኙም ስካን ማድረግዎን አለመርሳት፣
-->ሁል ጊዜም የታደሰ ፀረ ቫይረስ ሶፍትዌር መጠቀም፣
-->ተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋቶች እንዳይሰረቁና እንዳይጠፉ
ጥንቃቄ ማድረግ፣
-->ሚስጥራዊ ኢንፎርሜሽኖችን ተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋቶች ላይ አለማስቀመጥ፣
-->ለግልና ለስራ ወይም ለትምህርት የምንጠቀምባቸውን ተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋቶች መለያየት፣
-->በሚጠቀሙበት ኮምፒየተር ላይ የሚገኘውን አውቶ ራን (ተንቀሳቃሽ የኢንፎርሜሽን ቋቶች ሲሰኩ ወዲያውኑ እንዲከፈቱ የሚያስችለው ፊቸር) ዲስ ኤብል ያድርጉ፣ አውቶ ራንን በተለያዩ የዊንዶውስ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች ላይ ዲስኤብል ለማድረግ የሚያስችሉ ደረጃዎች የሚከተለውን ሊንክ በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ፣ http://support.microsoft.com/kB/967715

The updates that this article describes correct the "disable Autorun registry key" enforcement in Windows.

23/01/2015

1000 likes we want!!!!

Address

Muja

Telephone

+255332120209

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Muja Maryam Secondary School posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Muja Maryam Secondary School:

Shortcuts

Share

Category