መ/ ኃ/ቀሲስ ሰሎሞን ያለው

መ/ ኃ/ቀሲስ ሰሎሞን ያለው Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from መ/ ኃ/ቀሲስ ሰሎሞን ያለው, School, የቆሎ ተማሪ, Mizan Teferi.

✥✥✥ ?✥✥✥          ➗➗➗➗➗➗➗➗➗✅ የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ፡፡ ስድስት ቀን ሥራ፡፡ ተግባርህንም ሁሉ አድርግ፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው...
21/05/2023

✥✥✥ ?✥✥✥
➗➗➗➗➗➗➗➗➗
✅ የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ፡፡ ስድስት ቀን ሥራ፡፡ ተግባርህንም ሁሉ አድርግ፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፡፡
አንተ፥ ወንድ ልጅህም፥ ሴት ልጅህም፥ ሎሌህም፥ ገረድህም፥ ከብትህም፥ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ፤ እግዚአብሔርም በስድስት ቀን ሰማይንና ምድርንም፥ ባሕርንም ያለባቸውንም ሁሉ ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን ዐርፏልና፤ ስለዚህ እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታልም፡፡”
ዘጸ. ፳፥፲–፲፩፡፡
➛ ሰንበት የተባረከ ቀን ነው፡፡ በጌታም ዘንድ የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ይህ ትእዛዛት ከመጻፋቸው በፊት እግዚአብሔር ለሕዝቡ ለእሥራኤል የሰጠው ቀዳማዊ ትእዛዝ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝቡ ይፈጽመው ዘንድ ከመሰጠቱ በፊት እግዚአብሔር ራሱ በተግባር የፈጸመው ትእዛዝ ነው ሊባልም ይችላል፡፡ እንግዲህ በዚህ መሠረት ቀዳማዊ ትእዛዝ መሆኑን ካረጋገጥን፤ እግዚአብሔርንም ከሥራው ሁሉ በማረፍ ሰንበትን ለእረፍት የባረከውና የቀደሰው መሆኑን ካወቅን እኛ ደግሞ የበለጠ ልናከብረውና በሥራም ልንፈጽመው የሚገባን አይደለምን? በመጽሐፍም ደግሞ “እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው ቀደሰውም፤ እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ አርፏልና፡፡” በማለት የተነገረው ቃል ይህን ትእዛዝ በዓለም መጀመሪያ እግዚአብሔር አምላክ የስድስቱ ቀናት ተግባሩን ከፈጸመ በኋላ በማረፍ ለዕረፍት የሠራልን መሆኑን የሚያስረዳ ነው፡፡ ዘፍ. ፪፥፫፡፡

➤መጽሐፍ “እግዚአብሔር እርሱ ዐርፎበታልና ሰባተኛውን ቀን ባረከው” ይላል፡፡ ነገር ግን “ዐርፎአልና” የሚለው ቃል ትርጉምና ፍች ያስፈልገዋል፡፡ እግዚአብሔር በባሕርዩ ድካም የሚስማማውና ዕረፍትም የሚያስፈልገው አይደለም፤ ታዲያ “ዐርፎአልና” የተባለው ምን ለማለት ተፈልጎ ነው? ስለ ዕረፍት የሚነገረው አድካሚ ሥራ ላለበት ነው፡፡ እግዚአብሔር ዐርፏልና ሲባል የትኛውን አድካሚ ሥራ ሠርቶ ነው? የሚል ጥያቄ መነሣቱ አይቀርም፡፡እግዚአብሔር ዓለም ለመፍጠር ትእዛዝ ከመስጠትና ከመናገር በቀር ያደረገው አንዳች ነገር እንደሌለ መጻሕፍት ይመሠክራሉ፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዳዊት “እርሱ ተናግሯልና፥ ሆኑም፤ እርሱም አዘዘ፥ ጸኑም” በማለት የተናገረው ይህንኑ የሚያረጋግጥ ነው፡፡ መዝ. ፴፪፥፱፡፡

➤በዚህ መሠረት እርሱ “ብርሃን ይሁን” ባለ ጊዜ ይሆን ነበር፤ “ከሰማይ በታች ያሉ ውኆች ይሰብሰቡ” ባለ ጊዜም እንዲሁ ይሰበሰቡ ነበር፤ ምድርም ዘርን ታብቅል ባለጊዜ ታበቅል ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ ከቃሉ የተነሣ ከመሆን በቀር በእግዚአብሔር ላይ ያስከተሉት ድካም አልነበረም፡፡ነገር ግን የማዳን ሥራው በእርግጥ አድካሚ እንደነበር ደግሞ እናስተውላለን፡፡ እርሱ ሰውን ለማዳን ሰው መሆን ነበረበት፤ መለኮታዊ ልዕልናውን ትቶ ክብሩን በፈቃዱ ዝቅ አድርጎ በትሕትና አርአያ ገብርን መንሣት ነበረበት፤ ከኃጢአት በቀር ሰው የሠራውን ሁሉ መሥራት ነበረበት፤ መሰደብ፣ መንገላታት፣ መሰቀልና መከራን ሁሉ ለመቀበል፣ መሞትና ከሙታን መነሣት ሁሉ በእርሱ መፈጸም ነበረባቸው፡፡ በዚያ የመጨረሻው የመከራ ቀን፤ በዕለተ ዓርብ የኃጢኣትን ኃይል፣ ሞትንም በሞት ድል ነሥቶ የኃጢኣት ደመወዝ የሆነውን ሞትን አስወገደው፡፡ ሮሜ ፮፥፳፫፡፡

➤ይህንንም በዕለተ ሰንበት /እሑድ/ በትንሣኤው አተመው፤ ፍጹም የሆነውም የእግዚአብሔር ዕረፍት የሰው ልጆችን መዳን ማረጋገጥ ነውና፡፡ ከዚህ በመነሣት ነው እሑድ ሰንበተ ክርስቲያን ወይም የጌታ ቀን የተባለው፡፡ ቅዱስ ዳዊትም “ዛቲ ይእቲ ዕለት ኅሪት ዕለተ መድኃኒት እንተ ባቲ ንትፈሣህ ወንትሐሠይ፤ ይህች እንደሰትባት ዘንድ እግዚአብሔር ያዘጋጃት ቀን ናት” በማለት መናገሩ ለዚሁ ነው፡፡መዝ. ፻፲፰፡፡

➤ሰንበትን ማክበር ከዐሠርቱ ትዕዛዛት በፊት በተግባር የነበረ ነው፡፡ በመሆኑም እግዚአብሔር ለሙሴ በሰጠው ጽላት ላይ በጻፈው ጊዜ “ትቀድሰው ዘንድ አስበው” በማለት እሥራኤል ቀድሞውኑ የሚያውቁትን ይህን ትእዛዝ እንዲያስታውሱት አድርጓል፡፡ ዐሠርቱን ትእዛዛት የምናገኘው በኦሪት ዘጸአት ምዕራፍ ፳ ሲሆን እግዚአብሔር ሥራውን ፈጽሞ /የመፍጠር ሥራውን/ በተግባር ከገለጠው በተጨማሪ በትእዛዝ መልክ ሰንበትን ማክበር እንደሚገባ የተነገረው በዘጸአት ምዕራፍ ፲፮ ነው፡፡

➤እግዚአብሔር ለእሥራኤል ኅብስተ መናን ከሰማይ ባዘነበላቸው ጊዜ በየዕለቱ የሚበቃቸውን ያህል ይሰበስቡ ነበር፡፡ በስድስተኛው ቀን ግን በሌሎቹ ዕለታት ከሚለቅሙት በእጥፍ ይለቅሙ እንደነበር ተጽፏል፡፡ ነቢዩ ሙሴም “እግዚአብሔር የተናገረው ይህ ነው፡- ነገ ዕረፍት፥ ለእግዚአብሔርም የተቀደሰ ሰንበት ነው፤ የምትጋግሩትን ጋግሩ፤ የምትቀቅሉትንም ቀቅሉ፤ የተረፈውን ሁሉ ለነገ አንዲጠበቅ አኑሩት አላቸው፡፡ ዘጸ . ፲፮፥፳፫፡፡ እንደታዘዙትም አኖሩት፤ አልሸተተም፣ ትልም አልሆነበትም፤ ሙሴም “የእግዚአብሔር ሰንበት ዛሬ ነውና ብሉት፤ ዛሬ በሜዳ አታገኙትም፡፡ ስድስት ቀን ልቀሙት፤ ሰባተኛው ቀን ግን ሰንበት ነው በእርሱ አይገኝም፤ . . . እግዚአብሔር ሰንበትን እንደሰጣችሁ ዕዩ፤ ስለዚህ በስድስተኛው ቀን የሁለት ቀን እንጀራ ሰጣችሁ፤ ሰው ሁሉ በሥፍራው ይቀመጥ፤ በሰባተኛው ቀን ማንም ከሥፍራው አይሂድ . . . ሕዝቡም በሰባተኛው ቀን ዐረፈ፡፡ዘጸ. ፲፮፥፴ - ፴፪፡፡

➤በዚሁ መሠረትም እነርሱ ሰንበትን ቀደሱት፤ በሰንበትም ምንም ነገር አልሠሩትም፤ ምግባቸውን ፍለጋ እንኳ ከቤት አልወጡም፤ ምግብም አላበሰሉም፤ ዐረፉበት እንጂ፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ የዓርብን እንጀራ በእጥፍ አብዝቶ ሰጣቸው፤ ባረካቸውም፡፡ እግዚአብሔር አምላክ የሰንበትን አከባበር ከመና አሰባሰብ ጋር አያይዞ አዘዘ፤ ይህ የሚያስረዳን ከዐሥርቱ ትእዛዛት አንዱ ክፍል ሆኖ ከመሰጠቱ አስቀድሞ ሰንበትን ማክበር በእሥራኤል ዘንድ የሚታወቅና በሥራም ላይ የነበረ መሆኑን ነው፡፡

➤እግዚአብሔር ከሌሎች ትእዛዛት ሁሉ በፊት ያስቀደመው ሰንበትን ስለማከበር የሰጠውን ትእዛዝ ነው፡፡ ይህ ትእዛዝ ደግሞ ጥብቅ ነው፡፡ ይኸውም ሰንበትን ያላከበረ ሰው እንዲገደል በተሰጠው ትእዛዝ ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔርም ለሙሴ “ለእናንተ ቅዱስ ነውና ሰንበትን ጠብቁ፤ የሚያረክሰውም ሁሉ ፈጽሞ ይገደል፥ ሥራንም በእርሱ የሠራ ሰው ሁሉ ከሕዝቡ መካከል ተለይቶ ይጥፋ፡፡ . . . ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር የተቀደሰ የዕረፍት ሰንበት ነው፤ በሰንበት ቀን የሚሠራው ሁሉ ፈጽሞ ይገደል፡፡” ሲል የተናገረው ቃል የዚህን ትእዛዝ ጥብቅነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ዘጸ. ፴፩፥፲፬ - ፲፭፡፡

➤በተጨማሪም “ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር የዕረፍት ሰንበት የተቀደሰ ቀን ይሆንላችኋል፤ የሚሠራበትም ሁሉ ይገደል፡፡ በማደሪያዎቻችሁ ውስጥ በሰንበት ቀን እሳትን አታንድዱ፡፡” በማለት የተነገረው የዚህን ትዕዛዝ ክብደት የሚያመለክት ነው፡፡ ዘጸ. ፴፭፥፪፡፡

➤ነቢዩ ሕዝቅኤልም ሰንበትን ስለሚሽሩ ሰዎች ብዙ ጊዜ ተናግሯል፡፡ “ልጆች ግን ዐመፁብኝ . . . በሥርዓቴም አልሄዱም፥ ሰንበታቴን አረከሱ፤ በዚህም ጊዜ፡- መዓቴን አፈስስባቸዋለሁ ቁጣዬንም በምድረ በዳ እፈጽምባቸዋለሁ” ሲል ተናግሯልና እያለ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡ ሕዝ ፳፥፳፩፡፡

➤ነቢዩ ሙሴ “እግዚአብሔር ሰንበትን እንደሰጣችሁ እዩ” በማለት መናገሩ የዚህን ስጦታ ዓላማና ምክንያት አስተውሉት ለማለት ነው፡፡ ሰንበትም የእግዚአብሔር ስጦታ እንጂ በሰው ልጆች ላይ የተጫነ ሸክም ወይም ዕዳ አይደለም፡፡ የፈጠረን እግዚአብሔር ደካማ ባሕሪያችንን ስለሚያውቅ ከሳምንቱ ዕለታት አንዱን ሰንበት አድርጎ ለዕረፍት ሰጠን፡፡ ከድካማችን የተነሣም በየዕለቱ መሥራት አንችልምና ሰንበትን ማክበር ለሥጋም ጠቃሚ ነው፡፡
ዘዳ. ፭፥፲፬-፲፭፡፡እግዚአብሔር ሰንበትን የሰጠበት ሌላው ምክንያት ሰው በዚህ ዓለም ሲኖር ለሥጋዊ ፍላጎቱ ብቻ ሲቃትትና ሲደክም ሥጋውንም ብቻ ሲያስብና ለሥጋዊ እርካታ ብቻ ሲሠራ እንዲውል ብቻ ሳይሆን ሥጋውን አሳርፎ የነፍስ ሥራ እንዲሠራበት በዚህ ዓለም ባረፈው ዕረፍት የማያልፈውን ሰማያዊ ዕረፍተ ነፍስ እንዲያስብ፣ እንዲመኘው፣ እንዲለምንና በሕይወት ዘመኑም ስለሰጠው መንፈሳዊ በረከት እግዚአብሔርን እንዲያመሰግንበት ጭምር ነው፡፡ ማር. ፪፥፳፯፡፡

➤አምላካችን እግዚአብሔር እንደተናገረው ሁሉ ሰንበት የዘለዓለማዊና የመንፈሳዊ ዕረፍት ምልክት ሆኖ የተሰጠ ጸጋ ነው፡፡ “እኔ የምቀድሳችሁ እግዚአብሔር እንደሆንሁ ታውቁ ዘንድ በእኔና በእናንተ ዘንድ ለልጅ ልጃችሁ ምልክት ነውና ሰንበቶቼን ፈጽሞ ጠብቁ፡፡” እንዲል፡፡ ዘጸ. ፴፩፥፲፫፡፡

➤ ሰንበት የሚመጣው አማናዊ ዕረፍት ምሳሌ ሆኖ የተሰጠ የብሉይ ኪዳን ሕግ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ሕግ መሠረት በሰንበት ዕረፍተ ሥጋ ይደረጋል፡፡ ይህም በኋላ ዘመን በክርስቶስ ቤዛነት ለተገኘው ድኅነት ለዕረፍተ ነፍስ ምሳሌ ነበር፡፡ በሐዲስ ኪዳን የተገለጠው የክርስቶስ ትንሣኤ በሰንበተ ክርስቲያን ተፈጽሟል፤ ሰንበተ ክርስቲያንም የሰው ልጆች ለዘለዓለም ዐርፈው ከእግዚአብሔር ጋር በደስታ የሚኖሩበት ምሥጢረ ትንሣኤ የተገለጠበት የድኅነት ዕለት ነው፡፡እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን በፈጠረ ጊዜ በሰባተኛው ቀን ማረፉ፣ የማዳን ሥራውን ፈጽሞ ሞትን ድል በማድረግ ለእኛ የሰጠው የሰንበተ ክርስቲያን ምሳሌ ነበር፡፡ ሰንበተ ክርስቲያን የተባለ እሑድም ለዘለዓለም የምናርፍበትን የዕረፍት ቀን የሚያመለክት ነው፡፡ “በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው” እንደተባለው ሞት በተሻረበት ትንሣኤ ስንነሣ ያንጊዜ እኛም የዘለዓለሙን ዕረፍት እናርፋለን፡፡
፩ቆሮ. ፲፭-፳፬-፳፰፡፡

➤ስለሆነም የክርስቲያኖች ሰንበት ከቅዳሜ እሑድ ወደ መሆን ተቀየረ ወይም ተለወጠ፤ ሰንበተ ክርስቲያንም ተባለ፡፡ ይኸውም እሑድ ከበረ ማለት እንጂ ቅዳሜ ፈጽሞ ተሻረ ማለት አይደለም፡፡ “በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ” የሚለው ትእዛዝ በሰንበት ተኝታችሁ ዋሉ፣ ሥራ ፈታችሁ ተቀመጡ የሚል ትርጉም ያለው አልነበረም፡፡ በሌሎች ቀናት ከሚሠራው ሥራ ለየት ያለ መንፈሳዊና መልካም ሥራ እንዲሠራበት የተሰጠ ነው እንጂ፡፡ ሰንበትም በስንፍና ያለአንዳች ሥራ የሚያሳልፉት ሳይሆን መልካም ሥራ እንዲሠራበት የተሰጠ ነው እንጂ፡፡ ሰንበትም በስንፍና ያለአንዳች ሥራ የሚያሳልፉት ሳይሆን መልካም ተግባር እየፈጸሙ በመንፈሳዊ ሥራ ተጠምደው የሚያከብሩት የጌታ ቀን ነው፡፡ አይሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይከራከሩት የነበረው በሰንበት ለምን መልካምና መንፈሳዊ ሥራ ሠራህ? ለምን አስተማርክ? ለምን ድውያንን ፈወስክ? በማለት ነበር፡፡
ማቴ. ፲፪፥፲፤ ሉቃ. ፲፬፥፫፡፡መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጌታ ቀን የተባለች ሰንበትን በመንፈሳዊ ሥራ ተጠምዶ ማሳለፍ እንደሚገባ ለማስተማር ብዙ ድውያንን ይፈውስና በምኩራብ በመገኘት ያስተምር ነበር፡፡ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ዕውር የነበረውን ሰው የፈወሰው በዕለተ ሰንበት ነበር፡፡ “ኢየሱስም ጭቃ አድርጎ ዓይኖቹን የከፈተበት ሰንበት ነበር፡፡” እንዲል፡፡ ዮሐ. ፱፥፲፬፡፡ እጁ የሰለለችውን ሰው በፈወሰ ጊዜም በሰንበት መፈወስ የተፈቀደ ስለመሆኑ ሲነግራቸው “ከእናንተ አንድ በግ ያለው በሰንበትም በጉ በጉድጓድ ቢወድቅበት፥ ይዞ የማያወጣው ሰው ማነው? ስለዚህ በሰንበት መልካም ሥራ ተፈቅዷል አላቸው፡፡
ማቴ. ፲፪፥፲-፲፫፡፡ ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባትን ሴት ከፈወሰ በኋላ የምኩራብ አለቃውን “እናንተ ግብዞች፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በሬውን ወይስ አህያውን ከግርግሙ ፈትቶ ውኃ ሊያጠጣው ይወስደው የለምን? ይህችም የአብርሃም ልጅ ሆና ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያሠራት በሰንበት ቀን ከዚህ እሥራት ልትፈታ አይገባምን? አለው፡፡ ሉቃ. ፲፫፥፲-፲፮፡፡ በቤተ ሳይዳ ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ድውይ የነበረውንም ሰው የፈወሰው በሰንበት ነበር፡፡ዮሐ. ፭፥፪--፲፩፡፡ ሆዱ የተነፋውንም ሰው የፈወሰው በሰንበት ነበር፤ሉቃ. ፲፬፥፩-፮፡፡

➤ከዚህም በላይ ደቀመዛሙርቱ እሸት ቀጥፈው በመብላታቸው የተነሣ ፈሪሳውያን በተቃወሙት ጊዜ “ሰንበት ስለ ሰው ተፈጥሯል እንጂ ሰው ስለሰንበት አልተፈጠረም” በማለት ሰው በሰንበት መልካም ሠርቶ መንፈሳዊ ጥቅም ሊያገኝ እንደሚገባ አስተምሯል፡፡
ማር. ፪፥፳፫፡፡ “እኔ ምሕረትን እወዳለሁ፤ መሥዋዕትንም አይደለም” በማለት በሰንበት ቀን ለድውያን የተደረገው ምሕረት ሰንበትን መሻር አለመሆኑን በሰንበትም ይህን መሰል መንፈሳዊ ተግባር መፈጸም የሚገባ መሆኑን አስረድቷል፡፡ ማቴ . ፲፪፥፯፡፡ከሁሉም በላይ ሰንበት ለመንፈሳዊ ሥራ እንዲውል እግዚአብሔር ማዘዙ በመጽሐፍ ተመዝግቧል፤ “ሰባተኛው ቀን ግን የዕረፍት ሰንበት ነው፤ የተቀደሰ ጉባኤ ይሆንበታል፡፡ ዘሌ. ፳፫፥፫፡፡

➤ይህም በዕለተ ሰንበት መንፈሳውያን ስብሰባዎች ይደረጉበታል ማለት ነው፡፡ በተጨማሪም እግዚአብሔር “በየሰንበቱ ሥጋ ለባሽ ሁሉ በፊቴ ይሰግድ ዘንድ ዘወትር ይመጣል” በማለት የተናገረው ሰንበት የአምልኮ መፈጸሚያ ቀን መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ኢሳ. ፷፮፥፳፫፡፡ በሌላ ምንባብ ደግሞ የሚቃጠለው መሥዋዕትና የእህሉም ቁርባን በሰንበት ቀን እንዲቀርብ አዝዞአል፡፡ ሕዝ . ፵፮፥፬፡፡
ቅዱሳት መጻሕፍትም የሚነበቡት በዕለተ ሰንበት ነው፤ “ሙሴስ ከቀደሙት ትውልድ ጀምሮ በሰንበት በሰንበት በምኩራቦች ሲያነቡ በየከተማው እርሱን የሚሰብሰኩ አሉት፡፡” እንዲል፡፡ የሐዋ. ፲፭፥፳፩፡፡

➤ ሰንበት የአምልኮ መፈጸሚያ ብቻም ሳይሆን የማስተማሪያ ዕለት ጭምር ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰንበት ያስተምር እንደነበር ሁሉ ደቀ መዛሙርቱ ሐዋርያትም እንደእርሱ እንደመምህራቸው በሰንበት ያስተምሩ እንደነበር ቅዱሳት መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡
ማር. ፮፥፪፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በየሰንበቱም ሁሉ በምኩራብ ይነጋገር ነበር፤ አይሁድንና የግሪክን ሰዎች /ስለ ወንጌል/ ያስረዳ ነበር፡፡ የሐዋ. ፲፬፥፬፡፡በተሰሎንቄም እንዲሁ “የአይሁድ ምኩራብ ነበረ፡፡ ጳውሎስም እንደልማዱ ወደ እነርሱ ገባ፥ ሦስት ሰንበትም ያህል ከእነርሱ ጋር ከመጻሕፍት እየጠቀሰ ይነጋገር ነበር የሐዋ. ፲፯፥፩-፪፡፡

➤በሐዲስ ኪዳን ሰንበት ሁለት ነው፡፡
➛ዕለት ቅዳሚት እና
➛እሁድ ናቸው፡፡እነዚህም ማክበር እንደሚገባና ሥራ እንዳይሰራባቸው ሐዋሪያት በሲኖዶስ
አዘዋል፡፡ (አንቀጽ 65፤2)

🤳🤳🤳🤳 🤳🤳🤳🤳

➤ቅዳሜ የሚከበርበት ምክንያት እግዚአብሔር ስድስት ቀን ሰርቶ በእርሷስላረፈና በኦሪት በእግዚአብሔር የታዘዘ በእግዚአብሔር ተባርኮና ተቀድሶ የተሰጠ ስለሆነ ነው።
ዘጸ.20፤8 ሆኖም ግን በዘመነ ሐዲስ የክርስቲያኖች
የቀዳሚት ሰንበት አከባበር እንደ አይሁድ ለሰው የሚከብድ እንዳይሆን በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 19 ላይ ተገልጿል፡፡

🤳🤳🤳🤳 🤳🤳🤳🤳

➤እሑድ ማለት ‹‹አሐደ›› ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም የመጀመሪያ ማለት ነው፡፡ ይህቺ ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን›› በመባል ትታወቃለች፡፡ ዮሐንስም በራዕዩ ‹‹የጌታ ቀን›› ያላት ናት
ራእይ 1፤10 ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ ‹‹ዕለተ እግዚአብሔር› የሚላት ዕለተ እሑድ ናት፡፡ዕለተ እሑድ እንደ ሰንበት የሚከበርበት ምክንያቶች፡--እግዚአብሔር ሥራውን የጀመረባት ለሥነፍጥረት መጀመሪያ ዕለተ (ጥንተዕለት) ናትና
➛-ዕለተ ሥጋዌ ናት፡፡ ጌታ የተፀነሰባትና እርቅ የተወጠነባት የፍሰሐ ቀን፡፡
➛ዕለተ ትንሣኤ ናት፡፡ ጌታ ከሙታን ተለይቶ የተነሳባት ዕለት
➛-የቤተ/ክ የልደት ቅን ናት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋሪያት የወረደባት ኃይልና ፅናትን ያኙባት ዕለት
➛ጌታ በክበበ ትስብእት በግርማ መለኮት ዳግም በቅዱሳን መላእክቱ ታጅቦ በጌትነቱ ለፍርድ የሚመጣባት ታላቅ የፍርድ ቀን ናትና።
➛የተለያዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች የሚካሄዱባት ዕለት ናት
1ኛ ቆሮ 16÷1የሐዋሪያት ዘመንም በጤሮዓዳ ያሉ ክርስቲያኖች እሑድ ቀን ይሰበሰቡ ነበር። የሐዋ 20÷7

🤳🤳 ?🤳🤳

➤ቀደም ባሉ ዘመናት በተለይም በኢትዮጵያ ይህን በተመለከተ ብዙ ክርክሮች ተደርገው እንደነበር መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡ ፍትሐ ነገስት እንደ እሑድ ቀዳሚትን አትጠናቀቁ ቢልም በአገራችን በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን‹‹ቀዳሚት እንደ እሑድ ይከበር›› በሚሉና ‹‹እሑድ ብቻ ይከበር›› በሚሉ
በቤተ ተክለሃይማኖትና በቤተ ኤውስጣቴዎስ ሊቃውንት መካከል ውዝግብ ተነስቶ ነበር፡፡በመጨረሻም በወቅቱ የነበሩት የቤተክርስቲያን ሊቃውንት ተከራክረው በመተማመን መንፈስ ቅዱስ በገለጠላቸው መጠን ባስቀመጡት መሠረት
በቤተክርስቲያን ሁለቱን ቀናት ሳምንታዊ በዓላት በመሆን እንደ አንድ ቀን አድርገንና አስተካክለን እናከብራቸዋለን፡፡
✍️ቅዳሜ ተሽሯል በምትኩ እሑድ ተሰጠን የሚሉትን ቤተክርስቲያን አትቀበላቸውም፡፡ ‹‹እኔ ሕግንና ነቢያትን
ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ ልፈጽም እንጂ ለመሻር
አልመጣሁም››ማቴ 5፤7 ይላልና ጌታችን በኦሪት ላይ ወንጌልን እንደሠራ ሁሉ በቅዳሜ ላይም እሑድን ሰራ፡፡
ይህን ክርክር በተመለከተ በ1442 ዓ.ም ልዩ ስሙ ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በአባ ሚካኤልና በአባ ገብርኤል መሪነት ጉባኤ ተደርጐ ቅዳሜና እሑድ እኩል እንዲከበሩ ወስነዋል። ይህም በመጽሐፈ ብርሃን ሁለቱም ሰንበታት
አንድ ሆነው እንዲከበሩ በጉባኤው መስማማታቸውን ይገልፃል፡፡

➤ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ አትናቴዎስም በሰንበተ ክርስቲያን እንዲቀደስ በደረሰው ቅዳሴ ቁጥር 60-64 ‹‹በነቢዩ በዳዊት መዝሙር
በታወቀች በበዓላችን ቀን በእውነት ሃሌሉያ እንበል፡፡ እግዚአብሔር ሥራውን ይሠራ ዘንድ የጀመራት በእውነት የታወቀች ናት በእርሷም ደስ ይበለን፡፡በእርሷም ሐሴት እናድርግ፡ ትከብሩባት ዘንድ አክብሯት፡ዘመን ወር ለመባል በእርሷ የታወቃችሁ ሌሎች ዕለታት ሆይ የበዓላትን በኩር ኑ አመስግኗት ይህችውም የከበረች ሰንበተ ክርስትያን ናት›› በማለት የሰንበተ ክርስቲያንን ታላቅነት ተናግሯል፡፡የሮም ቄሳሮች ዕለተ እሑድ እንዳይከበር ከልክለው የነበሩ ሲሆን ተመልሶ እንዲከበር በአዋጅ የተደነገገው በንግሥት ዕሌኒ ልጅ በንጉሥ ቆስጠንጢኖስዘመን ነው፡፡

➤ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሥልጣን በያዘ ጊዜ ክርስቲያኖች የእምነት ነፃነታቸውን በማግኘታቸው ለቤተክርስቲያን ከሰጣቸው መብቶች ውስጥ አንዱ ከጌታ ትንሣኤ ጀምሮ ክርስቲያኖች ያከብሯት በነበረችው ዕለተ እሑድ ሥራ እንዳይሰራባትና የክርስቲያኖች የበዓል ቀን እንድትሆን በ321 ዓ/ም የታወጀው አዋጅ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን በሕገ መንግሥቱ አፅድቆ አወጀው እንጂ በክርስቲያኖች ዘንድ ዕለተ እሑድ ቀደም ሲልም የታወቀችና የተከበረች ዕለት ናት፡፡
በሰንበት የወደድነውን ሁሉ ልንፈጽምበት አልተሰጠንም፡፡
የሰንበት ውሎአችንን ለሰንበት ጌታ ለእግዚአብሔር ሰጥተን በዚህ ቀንም እርሱ ያደረገልንን ቸርነት እያሰብን በማመስገን፣ መንፈሳዊ ዋጋ የሚገኝባቸውን ቅዱሳት ተግባራት መፈጸም ይኖርብናል፡፡
👉👉👉👉 ።👉👉👉👉

✥  ?✥   ➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗✅ታዲያ እኛው እራሳችን ለራሳችን የምን ምክንያቶች ነን ? የጥፋት ወይስ የልማት ?" አንድ ዓይኑ የታመመ ሰው ፀሐይን ማየት ይከብደዋል ፤ ፀሐይዋ ችግር ኖ...
21/05/2023

✥ ?✥
➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗
✅ታዲያ እኛው እራሳችን ለራሳችን የምን ምክንያቶች ነን ? የጥፋት ወይስ የልማት ?
" አንድ ዓይኑ የታመመ ሰው ፀሐይን ማየት ይከብደዋል ፤ ፀሐይዋ ችግር ኖሮባት ሳይኾን ሰውየው ዓይኑ ስለታመመ፡፡ እኛም ቃለ እግዚአብሔርን ለመስማት ስንሰለች ዐይነ ልቡናችን የባሰ እየታወረ ነው የሚሔደው፡፡

✅ፈርዖን የእግዚአብሔርን ድምፅ አልሰማ ባለ ጊዜ ልቡናው ፀናበት፡፡ እግዚአብሔርም የፈርዖንን ልብ አደነደነ ተብሎ ተነገረ [ዘፀ.፬÷፳፩] ይህ ዓይነት አነጋገር የመጻሕፍት ልማድ ነው፡፡ "ለማይገባ አዕምሮ አሳልፎ ሰጣቸው" [ሮሜ.፩÷፳፰] ፤ "በታተናቸው" የሚሉ ኃይለ ቃላት በብዛት በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ተጽፈው እናገኛለን፡፡ ይህም ማለት ሰዎቹ እግዚአብሔርን ስላልፈለጉት ወደ ራሳቸው ፍላጎትና ምኞት ይሔዱ ዘንድ ፈቀደላቸው ማለት ነው፡፡ እንዲሔዱ ፈቀደላቸው ማለት ግን እግዚአብሔር ከሐሳባቸው ጋር ስላልተስማማ ደግሞም መመለስ ስላልፈለጉ እንደ ወደዱት እንዲሔዱ ዝም አላቸው ማለት እንጂ፡፡እግዚአብሔርን ስንርቀው የምንሔደው ወደ ሰይጣን ነው፡፡እግዚአብሔርም ለዚያ አሳልፎ ይሰጠናል፡፡ የፍርድ ዓይነትም በላያችን ላይ እንሸከማለን፡፡ እግዚአብሔር አሳልፎ ይሰጠናል ሲባል ግን እግዚአብሔር ወዶና ፈቅዶ ለሰይጣን አሳልፎ ሰጠን ማለት አይደለም፡፡ በፈቃዳችንና በውዴታችን ከእግዚአብሔር ስንርቅ በደላችን በእኛና በእግዚአብሔር መካከል ትቆማለች ፤ እንዳይሰማንና እንዳይምረንም ትከለክለዋለች [ኢሳ.፶፱÷፪] በደላችን ከእግዚአብሔር አቅም በላይ ኾና አይደለም ፤ እኛ ስላልወደድን እንጂ፡፡ መዝሙረኛው ክቡር ዳዊት ፦ "እነሆ ከአንተ የሚርቁ ይጠፋሉ" ያለው ይህንኑ ነው [መዝ.፸፫፥፳፯]

✅እግዚአብሔርም በነብዩ ሆሴዕ አድሮ "የአምላክህን ህግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ እተውሃለኹ" ብሏል [ሆሴ.፬:÷፮]፡ ዳግመኛም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፦ "ዶሮ ጫጩቶችዋን በክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ ፥ እናንተም አልወደዳችሁም፡፡" አለ [ሉቃ. ፲፫ ÷፴፬]፡፡

✅በነቢዩ ኢሳይያስ አድሮም ፦ "በመጣሁስ ጊዜ ሰው ስለ ምን አልነበረም? በጠራሁስ ጊዜ የሚመልስ ስለ ምን አልነበረም? መታደግ እንዳትችል እጄ አጭር ኾናለችን? ወይስ ለማዳን ኃይል የለኝምን?" ብሏል [ኢሳ.፶ ÷ ፪]
እግዚአብሔር በነዚህ ኃይለ ቃላት ሊያስተላልፍ የፈለገው መልዕክት
➛ለጥፋታችንም ኾነ
➛ለልማታችን ዋነኞቹ ምክንያቶች እኛው ራሳችን መኾናችንን መግለጥ ነው፡፡ እግዚአብሔር ምሕረቱ የበዛ መዓቱ የራቀ ቸርና ይቅር ባይ አምላክ ነው፡፡ በዘላለም ቅጣት ሲቀጣን እንኳን ፦ "የምዋቹን ሞት አልፈቅድምና" እንዲል [ሕዝ.፲፰ ÷ ፴፪] ደስ ብሎት አይቀጣንም፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኢየሩሳሌም በገዛ ፈቃዷ ስትጠፋ ያለቀሰላትም ለዚሁ ነው፡፡
ታዲያ እኛው
➛ እራሳችን
➛ለራሳችን የምን ምክንያቶች ነን ?
➛ የጥፋት ወይስ
➛የልማት ? "

[ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]

✥✥✥ ► ◄✥✥✥✅ በሸካ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በአስደናቂ የኪነ ሕንጻ ጥበብ ሲገነባ የቆየው የቴፒ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያን ከ12 ዓመታት በኋላ ...
21/05/2023

✥✥✥ ► ◄✥✥✥
✅ በሸካ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በአስደናቂ የኪነ ሕንጻ ጥበብ ሲገነባ የቆየው የቴፒ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያን ከ12 ዓመታት በኋላ ግንቦት 12/2015 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የካፋ ሸካ ቤንች ሸኮና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሰዋስዎ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሀላፊ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፡ እንዲሁም
➤የጠቅላይ ቤተክህነት ልዑካን
➤የሀገረ ስብከቱ ልዑካን
➤የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፡
➤ ሊቃውንት፣
➤በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በድምቀት ተመርቋል ፡፡

✅በዚህ ሕንጻ ቤተክርስቲያን፣
➛ በሀሳብ ፣
➛በገንዘብ ፣
➛በእውቀት ፡
➛በልዩ ልዩ መንገድ አሻራችሁን ያስቀመጣችሁ ፡ ከሩቅም ከቅርብም የምትገኙ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች እንኳንም ደስ አላችሁ።

✅በዕለቱም የካፋ ሸካ ቤንች ሸኮና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሰዋስዎ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሀላፊ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ቴፒ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን በማለት የካቴድራል ማዕረግ በመስጠት ተመርቋል።
እግዚአብሔር ይመስገን።

🇪🇹 #ኢትዮጵያዊው🇪🇹    ?// ===============✅ጥር - 13 ያረፉበት ቀን ስለሆነ አመታዊ ክብረ በዓላቸው ተደርጎ ይከበራል። ወርሃ ጥር በበዓላት ያሸበረቀ ወር ነው ( ከተራ፣ ጥም...
20/05/2023

🇪🇹 #ኢትዮጵያዊው🇪🇹 ?//
===============
✅ጥር - 13 ያረፉበት ቀን ስለሆነ አመታዊ ክብረ በዓላቸው ተደርጎ ይከበራል። ወርሃ ጥር በበዓላት ያሸበረቀ ወር ነው ( ከተራ፣ ጥምቀት፣ እረፍቱ ለፃድቁ አቡነ ሀራ ድንግል፣ ቃና ዘገሊላ፣ እረፍቱ ለፃድቁ አቡነ ዘርዓ ብሩክ፣ ዝርወተ አፅሙ ለልዕዳው ሰማእት ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ አስተርዮ ማርያም፣....) ብዙ በዓላት በዚህ ወር በድምቀት ይከበራሉ። ለአሁኑ ለአስተላልፋ ወደ ፈለኩት መልዕክት ወደ ፃድቁ አባታችን አቡነ ዘርዓ ብሩክ ልመልሳችሁ።
ነብዩን በነብይ ስም የሚቀበል የነበዩን ዋጋ ይወስዳል፥ ፃድቁን በፃድቅ ስም የሚቀበል የፃድቁን ዋጋ ይወስዳል። (ማቴ፦10፥41)
============================
✍✍✍🇪🇹 ኢትዮጵያ🇪🇹 ብዙ ያልተነገረላት ሰምና ወርቅ የሆነች ሀገር ነች። ከዕለታት አንድ ቀን ወደ ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ገዳም እግዚአብሔር ፈቅዶልኝ በሆነ ምክንያት ተጓዝኩ። በቆይታየም ከአንዳድ አባቶችና በረከት ለማግኘት ከሄዱ ምዕመናን ጋር በፍጥነት መግባባት ጀመርኩ። በተለይ ከአባቶች ጋር ያገኘሁት የመግባባት እድል በገዳሙ ውስጥ ያሉ መጻሕፍትን ስፈልግ እየተዋስኩ ለማንበብ ምቹ ሁኔታን ፈጠረልኝ። የብዙ ፃድቃን የተጋድሎ መጻሕፍት፣ የቅዱሳን ድርሳናት በብራና እንዲሁም በቀለም በያይነቱ በግዕዝ እንዲሁም በአማረኛ ቋንቋ ተተርጉመው ይገኙበታል። አብዛኞቹ የግዕዙ ቋንቋ ገፅ በገፅ በአማረኛ የተተረጎመላቸው ስለሆነ ያላስተማሪ እያነበቡ ለመረዳት ያስችላል።
✍✍✍በዚህ አጋጣሚ ነው ስለዚህ ፃድቅ 🇪🇹ኢትዮጵያዊ🇪🇹 አባት ስለ አቡነ ዘርዓ ብሩክ መጻሕፍትን ሳገላብጥ ለአምዕሮ ድንቅ የሆነ ታሪካቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ ማንበብ የቻልኩት። አሁን ላይ መለስ ብዬ የህይወት ማስታወሻየን ስመለከት ስለ ስንት ሰዎች እያወራን ለምን ለእነዚህ አይነት ቅዱስ 🇪🇹ኢትዮጰያዊ🇪🇹 አባት ምስክርነት ነፈኩአቸው በሚል ሀሳብ ውስጤ ስለተወቀሰ ምንም እንኳ ተጋድሏቸውን በአጭሩ መግለፅ እጅግ ቢከብድም በትነሹ ቀንጭቤ "ዝክረ ፃድቅ ለአለም ይሄሉ" ( የፃድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል) እንዳለው ዳዊት በመዝሙሩ (መዝ፦ 112፥6) እንደሚከተለው የፃድቁን መታሰቢያ በአጭሩ እነሆ።

✍✍✍የጻድቁ አባታችን የዘርዓ ብሩክ አባት እና እናት የተባረኩ ከቅዱሳን ወገን የነበሩ በፆምና ፀሎት የፀኑ ነበሩ። የአባታቸው ስምም ቅዱስ ደመ ክርስቶስ ሲባል እናታቸው ደግሞ ቅድስት ማርያም ሞገሳ ትባላለች ጻድቁ አባታችን ገና በእናታቸው ማህጸን እያሉ ነበር ብዙ ድንቅ ተአምራት የሚያደርጉት እግዚአብሄር መርጡአቸዋልና። ከክርስቶስ ልደት በኋላ በስምንተኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ ላይ በነሃሴ 27 ጻድቁ አባታችን ተወለዱ በ40ኛ ቀናቸውም ተጠምቀው በካህናት “ጸጋ ክርስቶስ” ተባሉ።

✍✍✍ ቤተሰቦቻቸው በእንክብካቤ ካሳደጉቸው በኋላ 7 አመትም በሞላቸው ጊዜ አቤቱ አምላኬ ሆይ የዚህን አለም ክፋቱን እንዳላይ አይነ ስውር አድርገኝ ብለው ሲጸልዩ አይናቸው ታውሩአል፤ ቤተሰቦቻቸውም ሊያስተምሩአቸው አስተማሪ ጋር ቢወስዱአቸው ታመው ተመልሰዋል የእግዚአብሄር ፈቃድ አይደለምና ነገር ግን የሚያስፈልጋቸውን እውቀት ፈጣሪ አምላክ ራሱ ገልጾላቸዋል:: ክህነትን እስከ ጵጵስና እራሱ መድሃኒአለም ክርስቶስ ሰቷቸዋል።
✍✍✍12 አመትም በሞላቸው ጊዜ አይናቸው በርቶላቸው ታላላቅ ተጋድሎን ማድረግ ጀመሩ፤ የሃጥያት ማሰርያን ያስሩና ይፈቱ ዘንድ ጵጵስናን በሾማቸው ጊዜ እግዚአብሄር ያወጣላቸው ሁለተኛ ስም “ዘርዓ ብሩክ” ይባል ነበር 3ኛው ስማቸው ደግሞ “ጸጋ እየሱስ”ይባላል:: ጻድቁ አባታችን በዚህ አለም በህይወተ ስጋ ሳሉ አቡቀለምሲስ እንደሚባሉና እንደ ዮሃንስ ወልደነጎድጉአድ እግዚአብሄር እሱ ወዳለበት ወደ ሰማይ አውጥቶ በገነት መካከል ያኖራቸው ነበር:: እግዚአብሄር አምላክ ለወዳጁ ለብጹዕ አባታችን ዘርዓ ብሩክ በጎ ነገር እንዳደረገለትና ያለ ድምጽ የሰማይ ደጆችን አልፎ የእሳት ባህርን ተሻግሮ ፈራሽ በስባሽ ሲሆን እንደ ህያዋን መላእክት በፍጥነት ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ከአድማስ እስከ አድማስ ይደርስ ዘንድ ከመላእክት የሚበልጥ 12 ክንፍን ሰጣቸው፤ መላእክትም ለሌሎች ቅዱሳን ያልተሰጠ ይህንን ስልጣን አይተው ለምድራዊ ሰው ይህ ነገር እንዴት ይቻላል እያሉ አደነቁ፤ ጻድቁ አባታችን ከፈጣሪ ዘንድ የመላእክትን አስኬማ,የሾህ አክሊል አምሳያ የሆነውን መንፈሳዊ ቆብን፣ ሰማያዊ ልብስን ተቀብሎ በጾም እና በጸሎት በልመና እና በስግደት እግዚአብሄርን ሲያገለግል ኖረ ከዛም በላይ ወንጌልን እጅግ ብዙ በማስተማር ደከመ🇪🇹 ከኢትዮጵያም🇪🇹 አልፎ ግብጽ ድረስ ገባ የእስክንድርያውን ሊቀ ጳጳስ አባ ዮሃነስን አገኘውና እርስ በርስ ሰላምታን ተለዋውጠው እጅ ተነሳሱ ተመልሶ ወደ ሃገሩ መጣ።🇪🇹 ኢትዮጵያ🇪🇹 ውስጥ እየተመላለሰ ወንጌልን አስተማረ እጅግ ስጋን በሚያስጨንቅ ትጋትም🇪🇹 የኢትዮጵያን🇪🇹 ህዝብ ማርልኝ እያለ እያለቀሰ ይጸልይ ነበር።
✍✍✍ አንድ ቀን አባታችን በንጉስ ጭፍሮች ተይዘው ሲሄዱ ዳዊታቸውን(መፅሀፍታቸውን) ለግዮን ወንዝ አደራ ሰተዋት ከ5 አመት በሁኋላ ሲመለሱ ግዮን ሆይ ዳዊቴን ግሺ መልሽልኝ ቢሏት አንድም የውሃ ጠብታ ሳይኖርባት ዳዊታቸውን ስትመልስላቸው ለደቀ መዝሙራቸው አሳዩትና ግዮንንም “ግሽ አባይ” ብለውታል እስካሁንም በዚሁ ስም የሚጠራው ከዚ በመነሳት ነው:: ይህ ቦታም በቅዱስ መፅሃፍት (ዘፍ፦ 2:10-23) ከተካተቱት ከኤዴን ገነት ከሚፈሱት አራት ትልልቅ ወንዞች ውስጥ🇪🇹 ኢትዮጵያን🇪🇹 የሚከበው የግዮን(አባይ) ወንዝ መነሻ እንደሆነ ታሪክ ያስረዳል።
✍✍✍ በወቅቱ በነበሩት በንጉሱ ጭፍሮች ታስረው እያለም ድንግል ማርያም መናን ከሰማይ እያመጣች ትመግባቸውና እንዲሁም ታፅናናቸው ነበር፤ ጻድቁ አባታችን እስር ቤቱን በታምራታቸው ስላንቀጠቀጡት ተፈተው በግዮን ወንዝ መነሻ አካባቢ ለ30 አመት ሲጸልዩ ፈጣሪ አምላክ ጸሎታቸውን ሰምቶ እጅግ ልዩ የሆነ ተጠቅሶ የማያልቅ ቃል ኪዳን ሰቶአቸዋል። ከአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጋርም በአንድ ቤተክርስቲያን ውስጥ አብረው ቀድሰዋል፤ ፀሀይን የማቆም ስልጣንም ተሰጧቸው ነበር፤ የተጣሉ ታላላቅ ዘንዶዎችን እስከማስታርቅና በሆዳቸው ውስጥ እስከማደር ድረስ ፀጋውን ታድለዋል።
✍✍✍ የሚያርፉበት እለት በደረሰ ሰዓት መልአከ ሞት ሊወስዳቸው መጥቶ እስኪደነግጥ እና ወደ ሁኋላ እስኪያፈገፍግ ድረስ ነው እግዚአብሄር ጸጋውንና ክብሩን ያበዛላቸው። በመጨረሻም ወርሃ ጥር በገባ በ13 ቀን በ482 አመታቸው ስጋቸው ከነፍሳቸው ተለይታ ገነትን ወርሰዋል:: አባታችን ገድል እኳን በዚች አጭር ጽሁፍ ይቅርና የገድላቸው መጽሃፍም አልበቃውም እግዚአብሄር አምላክ ከበረከታቸው እንዲያሳትፈን በማሰብ ጥቂት ከገድላቸው መጽሃፍ ላይ በመቀንጨብ አሰፈርኩ። ለእግዚአብሄር ምስጋና ይሁን
የጻድቁ አባታችን ምልጃ፣ ቃል ኪዳን፣ ረድኤት፣ በረከት አይለየን አሜን።
===============
✍✍✍🇪🇹 ኢትዮጰያ🇪🇹 አሁን ላይ አረም በዝቶባት ግራ ቢገባትም እኒህን የመሰሉ ብዙ ፃድቃን ያፈራች ሀገር ነች። አምላክ ወደ ቀደመው ክብሯ ይመልሳት። ሼር በማድረግ የዚህን ፃድቅ አባታችን ድንቅ ስራ ላልሰሙት በማሰማት የበረከቱ ተካፋይ እንሁን።
===============

🇪🇹

20/05/2023
✟ ።  ➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗✟ ትንሣኤ  በዋለ በ፮ኛው እሑድ የሚባል የሚዘመር የቅዱስ ያሬድ መዝሙር።ዛሬ የዘመነ ትንሣኤ የመጨረሻ እሑድ ነው። ምክንያቱም ቀጣይ ሐሙስ ዕርገት ስለሆነ ከዕር...
20/05/2023

✟ ።
➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗➗
✟ ትንሣኤ በዋለ በ፮ኛው እሑድ የሚባል የሚዘመር የቅዱስ ያሬድ መዝሙር።ዛሬ የዘመነ ትንሣኤ የመጨረሻ እሑድ ነው።
ምክንያቱም ቀጣይ ሐሙስ ዕርገት ስለሆነ ከዕርገት ጀምሮ ዘመነ ዕርገት ቀጥሎም ዘመነ ጰራቅሊጦስ እያለ የሚቀጥል ነውና።


"በ፫ ሃሌታ
ፋሲካ
ዛቲ ዕለት ቅድስት ይእቲ
ፋሲካ (አዝማች)
ዛቲ ዕለት ንትፈሣሕ ባቲ
ፋሲካ (አዝማች)
ንትፈሣሕ ባቲ ወንትኃሠይ ባቲ
ፋሲካ (አዝማች)
ዛቲ ዕለት ናኅይ ወዕረፍት
ፋሲካ (አዝማች)
ሰማይ ወምድር ይትፌሥሑ ባቲ
ፋሲካ (አዝማች)
ፋሲካ ፋሲካ ፋሲካ
ተዝካረ ትንሣኤሁ ለመድኃኒነ"
#ትርጉም
"ፋሲካ ማለት መሻገር ፣ ማለፍ ማለት ሲሆን በግሱ ስንተረጉመው ደግሞ ደስታ ማለት ነው።
ይህቺ ዕለት ቅድስት ናት።
ፋሲካ
ይህቺ ዕለት እንደሰትባት ዘንድ የምንደሰትባት ናትና እንደሰትባት።
ፋሲካ
በውስጥ በአፍኣ በነፍስ በሥጋ ፈጽሞ እንደሰትባት።
ፋሲካ
ይህቺ ዕለት ፈጽሞ ዕረፍት ናት ማለት የዕረፍት ቀን ናት።
ፋሲካ
ሰማይና ምድር ይደሰቱባታል።
ፋሲካ
ፋሲካ የክርስቶስ የትንሣኤው መታሰቢያ ናት።

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ጌታችን የተነሣባትን ቀን ዕለተ እሑድን ከሞት ወደ ሕይወት
ከሐሣር ወደ ክብር
ከጨለማ ወደ ብርሃን
ከሲኦል ወደ ገነት የወጣንባት፣ የተሸጋገርንባት፣ ያለፍንባት ሞትም እኛን ያለፈባት፣
በትንሣኤው ትንሣኤያችን የታወጀባት ዕለት ናትና "ፋሲካ" ይላታል። አንድም፦ ፍጹም ደስታን የተጎናጸፍንባት ዕለት ናትና
"ፋሲካ =ደስታ" አላት።ጨምሮም ቅድስት መሆኗን፣ ልንደሰትባት የሚገባ መሆኗን፣ ዕረፍት መሆኗን ፣ ሰማይና ምድር ይደሰቱባታል ብሎ በሰማይ ያሉ መላእክት በምድር የሚኖሩ ደቂቀ አዳም ደስ የሚሰኙባት መሆኗን ነግሮን ለአጽንዖተ ነገር " ፋሲካ ፋሲካ ፋሲካ" በማለት በደጊመ ቃል ያጸናውና "የክርስቶስ የትንሣኤው መታሰቢያ ቀን ናት" ይለናል። ስለሆነም ሁልጊዜ ስትመጣ የክርስቶስን ትንሣኤ በውስጣችን እናስባለን።
እኛም እንደምንነሣ በተስፋ "ንዜኑ ሞተከ እግዚኦ ወትንሣኤከ ቅድስተ ነአምን ዕርገተከ ወዳግመ ምጽአተከ" እያልን ስንሰብክ እንኖራለን። ሌላው ደግሞ ዘለዓለማዊውን ዕረፍት ስናስብባት እንኖራለንና ሊቁ እንዲህ አለ።

#ዓራራት
"ትንሣኤሁ ገብረ በሰንበት ወሰበረ ኆኃተ ብርት እግዚኣ ለሰንበት ሲኦለ ወሪዶ በነደ እሳት ተቤዘዎሙ ለቀደምት"
#ትርጉም
"ትንሣኤውን በሰንበት አደረገ። የብረት በሮችን ሰበረ። የሰንበት ጌታ በነደ እሳት ወደ ሲኦል ወርዶ የቀደሙትን ሰዎች አዳናቸው። በዓራራቱ ደግሞ ነደ እሳት ወደ አለባት ወደ ሲኦል ወርዶ ከአዳም ጀምሮ እስከ እርሱ(ክርስቶስ) የሞቱትን ነፍሳት ማውጣቱን ነው የሚገልጥልን።
"ቀነዮሙ ሞት እምአዳም እስከ ሙሴ ለእለሂ አበሱ ወለእለሂ ኢአበሱ"(ሮሜ፭፥፲፬) እንዲል። "እስከ" ን አግቢ አድርጎ ተርጉሞ ሙሴን ሳይቀር ማለት ነው።
#ዕዝል
"ከመ ንሳተፎ በሞቱ ወበተንሥኦቱ ተዘኪረነ ዘገብረ እግዚእነ እስመ አንሥአ ለነ ቤዛነ ወልዶ መድኅነ ላህም መግዝእ ተጠብሐ ዘወለደት ለነ ሐዳስ ጣዕዋ እስመ ከሠተ ምሥጢረ ኅቡዓ ወእዜኒ በንጹሕ ልብ ወበፈሪሐ እግዚአብሔር ንግበር ዘንተ በዓለ መንፈሳዊተ ቅድስተ ፋሲካ"
#ትርጉም
"ጌታችን ያደረገልንን አስበን በሞቱና በትንሣኤው እንተባበረው ዘንድ ማለት እንመስለው ዘንድ ይገባናል።
ልጁን መድኃኒት አድርጎ አስነሥቶልናልና። አዲሷ ጥጃ የወለደችው ፍሪዳ ታረደ። ተሰውሮ የነበረውን ምሥጢር ገለጠው። አሁንም በንጹሕ ልብና እግዚአብሔርን በመፍራት ይህንን መንፈሳዊ በዓል ማለትም ቅድስት የሆነች ፋሲካን እናክብር።"

➤ሊቁ ቅዱስ ያሬድ፦ ጌታችን ያደረገልንን ማሰብ እንዳለብንና በሞቱ ልንመስለው እንደሚገባ ያስተምረናል። በሞቱ ከመሰልነው ደግሞ በትንሣኤው ከእርሱ ጋር የምንተባበር መሆኑንም አያይዞ ይነግረናል።
✔️ ዘካርያስ "አንሥአ ለነ ቀርነ መድኃኒትነ እምቤተ ዳዊት ገብሩ" (ሉቃ፩፥፷፱) እንዳለ
ክርስቶስ ለእኛ መድኃኒት ሆኖ መምጣቱን ያስረዳል።
✔️አዲሷ ጥጃ ማለቱ በአሮጊቷ ላም በሔዋን ምክንያት ሞት ታውጆብን ነበር በአዲሷ ጥጃ በድንግል ማርያም ክርስቶስን መውለድ መዳናችንን ያስረዳል። "በእንተ ሔዋን ተአጽወ ኆኅተ ገነት ወበእንተ ማርያም ድንግል ተርኅወ ለነ ዳግመ" እንዲል ኤፍሬም።(ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ)
✔️አዲሷ ጥጃ የወለደችው ፍሪዳ ላም ታረደ ማለቱ ድንግል ማርያም የወለደችልን ክርስቶስ ስለ እኛ በመስቀል ተሰቅሎ ሥጋውን እንድንበላ ደሙን እንድንጠጣ የሰጠን መሆኑን ያስረዳል። ምክንያቱም ፍሪዳ የሚታረድ ሊበላ ነውና።
✔️በመጨረሻም በንጹሕ ልብና በፈሪሐ እግዚአብሔር ሁነን በዓለ ፋሲካን እናክብር በማለት ይመክረናል።

"ንግበር በዓለ በትፍሥሕት ቅድስተ ፋሲካ በኃሤት እንተ ባቲ አብ አንሥኦ ለወልዱ እሙታን"
#ትርጉም
"ቅድስት ፋሲካን በዓል አድርገን በፍጹም ደስታ እናክብር። በእርሷ አብ ልጁን ከሙታን መካከል አስነሥቶታልና።"
አብ አነሣው ማለቱ በሥልጣኑ አልተነሣም ማለት አይደለም በሥልጣን አንድ መሆናቸውን ለመግለጥ ነው።
አብ አንሥኦ
መንፈስ ቅዱስ አንሥኦ
ወተንሣእኩ በሥልጣነ ባሕቲትየ
ይላል መጽሐፍ እንዲህ ግን ስላለ መለያየት አይደለም በባሕርይ፣ በህልውና፣ በሥልጣን ፣ በፈቃድ ይህን በመሰለው ሁሉ አንድ ናቸውና።
"እስመ በፈቃዱ ወበሥምረተ አቡሁ ወመንፈስ ቅዱስ መጽአ ወአድኃነነ" እንዲል ኤፍሬም። (ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ)
#ሰላም
"እግዚኦ ሰማዕኩ ድምጸከ ወፈራሕኩ
ርኢኩ ግብረከ ወአንከርኩ
እግዚኦ መኑ ከማከ
ሙታነ አንሣእከ በቃልከ
እግዚኦ መኑ ከማከ
ሕይወተ ወሀብከ ወሰላመ ለነ ጸጎከ
እግዚኦ መኑ ከማከ
ንግበር በዓለ ፋሲካ ኵልነ
ምስለ ጻድቃኒከ ኅቡረ"
#ትርጉም
"አቤቱ ድምጽህን ሰምቼ ፈራሁ
ሥራህን አይቼ አደነቅኹ።(ዕንባ፫፥፪)
አቤቱ እንዳንተ ማነው?
ሙታንን በቃልህ አስነሣህ።
አቤቱ እንዳንተ ማነው?
ሕይወትን በጥንተ ተፈጥሮ በሐዲስ ተፈጥሮ ሰጠህ ሰላምንም ለእኛ ሰጠህ።
አቤቱ እንዳንተ ማነው?
ሁላችን ከጻድቃኖችህ ጋር በአንድነት በዓለ ፋሲካን እናድግ (እናክብር)።
🌹የነቢዩ ዕንባቆምን ትንቢት በመጥቀስ የእግዚአብሔር ድምጹ አስፈሪ እንደሆነ ሥራውም እጅግ አስደናቂ መሆኑን ይገልጣል።
🌹ሙታንን በቃልህ አስነሣህ በማለት "ጣቢታ ሆይ ተነሺ፣ አንተ ጎበዝ እልሃለሁ ተነሥ፣ አልዓዛር አልዓዛር ና ከመቃብር ውጣ" እያለ በቃሉ ሙታንን ማስነሣቱን ይሰብከናል።
🌹ሕይወትን ሰጠህ ማለቱ፦ በጥንተ ተፈጥሮ በነፍስ ሕያዋን አድርጎ የፈጠረን መሆኑን ያስረዳል።
በኋላም በመስቀል ላይ ራሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶ ለእኛ ሕይወትን ሰጥቶናልና።
"ዘዚአነ ሞተ ነሥአ ወእንቲአሁ ሕይወተ ወሀበነ" እንዲል ኤፍሬም (ወዳሴ ማርያም ዘዓርብ)
🌹ሰላምንም ለእኛ ሰጠህ ማለቱ፦ ጌታችን "“ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።” ( ዮሐ፲፬፥፳፯) እንዲል።
🌹ከጻድቃን ጋር ሁላችን በአንድነት በዓለ ፋሲካን እናድርግ ማለቱ፦ ጻድቃን በገነት እኛም በዚህ ዓለም በዓለ ፋሲካን እናከብራለን አለ ሊቁ።


✍️የሊቁ በረከት አይለየን!
የሳምንት ሰው ይበለን! አሜን!!!

፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠✥  ፲፩✥፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠"የሊቃውንት መምህር የቤተክርስቲያን ብርሃን ሊቁ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድን ሥርዓተ_ማኅሌት እንደ ሚከተለ...
18/05/2023

፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
✥ ፲፩✥
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
"የሊቃውንት መምህር የቤተክርስቲያን ብርሃን ሊቁ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድን ሥርዓተ_ማኅሌት እንደ ሚከተለው ተዘጋጅቷል።የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "
"
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
✥ #ነግሥ✥
ሰላም ለአብ ገባሬ ኲሉ ዓለም።
ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም።
ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም።
ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም።
ለሰማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም።
✥ #ዚቅ✥
ዜኖኩ ጽድቀከ ወነገርኩ አድኅኖተከ: ከሠትኩ ቃላቲከ ለሕዝብከ ኢትዮጵያ: በጸጋሁ ለመንፈስ ቅዱስ ወመሐርክዎሙ አነ: ይቤ ያሬድ ካህን።


ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘተጸውዖቱ መዓር።
ወለሥዕርትከ ጽዕድው ከመ ዘጌዴዎን ጸምር።
ማኅሌታይ ያሬድ ወነባቤ ሐዋዝ መዝሙር።
እመ ኮነ ብርዓ ሊባኖስ ወቀለመ ባሕር።
እምኢኀልቀ በተጽሕፎ ዘዚአከ ክብር።

✥ #ዚቅ✥
ያሬድ ማኅሌታይ ለእግዚአብሔር ካህኑ፡ ስብሐተ ትንሳኤሁ ዘይዜኑ፡ ኦሪት ቶታኑ ወወንጌል አሣዕኑ፡ ትርድአነ ነዓ በህየ መካኑ፡ ከመ ፀበል ግሁሣን ፀርነ ይኩኑ።

#ወረብ
ያሬድ "ካህኑ ለእግዚአብሔር"/፪/ /፪/
ትርድዓነ ነዓ በሕየ መካኑ ያሬድ ነዓ ትርድዓነ/፪/


ሰላም ለአእናፊከ እንበለ ሕፀፅ ወንትጋ።
ወለከናፍሪከ ዘነበባ ለቤተክርስቲያን ማኅሌተ ሕጋ።
ሊቀ ካህናት ያሬድ መስተሥርየ ጌጋይ ኮናኔ ሥጋ።
እለ ኪያከ የአኲቱ ወይዌድሱ እንግልጋ።
እምነ ትሩፍ ጸጋከ ኢይኅጥኡ ጸጋ።

#ዚቅ
ጸጋ ነሣዕነ ወህይወተ ረከብነ: በኃይለ ጸሎቱ ለያሬድ አቡነ: ኪያከ እግዚኦ ነአኲት ነሢአነ ጸጋ ዘእመንፈስ ቅዱስ።

#ወረብ
ጸጋ ነሣዕነ ወህይወተ ረከብነ በኃይለ ጸሎቱ ለያሬድ አቡነ/፪/
ኪያከ ነአኲት ነሢአነ ጸጋ ዘእመንፈስ ቅዱስ/፪/


ሰላም ለዘባንከ ዘተአጽፈ ክብረ።
ወለዕንግድዓከ ዘቦቱ ሐብተ አዕምሮ ኃደረ።
ያሬድ ትቤ እንዘ ትዌጥን መዝሙረ።
ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ።
ወለሙሴ አርአዮ ዘይገብር ግብረ።

#ዚቅ
ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ: ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ: በከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ።

#ወረብ
ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ/፪/
ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ በከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ/፪/

ሰላም ለልብከ ዘአፈድፈደ ጥበበ።
ወለኲልያቲከ ካዕበ።
አንቀጸ ብርሃን ያሬድ አመ ወጠንከ ነቢበ።
በመቅደሰ አክሱም ሰኮናከ ዘበማየ ጸጋ ተሐጽበ።
መጠነ ዓመት እምነ ምድር ልዑለ ተረክበ።

#ወረብ
ያሬድ አመ ወጠንከ ነቢበ አንቀጸ ብርሃን/፪/
መጠነ ዓመት ሰኮናከ ልዑለ ተረክበ እምነ ምድር/፪/

#ዚቅ
ውስተ ሰማያት ተመስጠ ግብተ: እምነ ሱራፌል ነሥአ ስብሐተ: ትንሣኤሁ ለወልድ ያሬድ ከሠተ: ተለዓለ መልዕልተ እምነ ምድር አመተ: እንዘ የኃሊ ዘድንግል ማኅሌተ።


መዝሙረ ማኅሌት ሐዋዝ ዘመዋዕለ ክረምት ወሐጋይ። ዘመፀው ወዘፀደይ።
ዘሠራዕከ ያሬድ ካህነ ዝማሬ ሠናይ።
ሰላምየ ድሉ እግዚኦ መካልየ ልዑል ሰማይ።
አኮ ዘወርቅ ወብሩር ጽሩይ።

#ዚቅ
ተወከፍ ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ: ወስዕለተነ ከመ መዓዛ ሠናይ: ተወከፍ ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ።

#ወረብ
ተወከፍ ጸሎተነ "ውስተ ኑኃ ሰማይ"/፪//፪/
ወስዕለተነ "ከመ መዓዛ ሠናይ"/፪//፪/


ሰላም ለአጥባትኪ ውስተ ምሥዋዓ ሕግ ጠረጴዛ።
ሀሊበ ቅዳሴ ንጹሐ እለ ከመ ፈለግ አውኃዛ።
እምቅንዓተ ዓለም ሐና ዘምግባረ ጠዋይ ግዕዛ።
አግዕዝኒ እግዝእትየ ወኩንኒ ቤዛ።
ከመ በደሙ ክርስቶስ ለሔዋን አግዓዛ።

#ዚቅ
ለዛቲ ብእሲት ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ: ወአግዓዛ እምዕኩይ ውስተ ሠናይ: እሞት ውስተ ህይወት: ወረሰየ ይዝክሩ ስማ ውስተ ኲሉ ምድር።


በትረ አሮን ማርያም ዘሠረጽኪ እንበለ ተክል።
ወጸገይኪ ጽጌ በኢተሰቅዮ ማይ ወጠል።
ወበእንተዝ ያሬድ መዓርዒረ ቃል።
ምስለ ሱራፌል ይዌድሰኪ ወይብል።
ሐጹር የዓውዳ ወጽጌረዳ በትዕምርተ መስቀል።

****** #ዚቅ
ናስተበቊአከ በእንተ ቃለ መዓርዒር ዘሱራፌል: ወበእንተ መዓዛ ውዳሴከ ለማርያም: ንስዕለከ ዝስኩ ማኅሌታይ ያሬድ።

#ምልጣን
አልቦ እምቅድሜሁ
ወአልቦ እምድኅሬሁ
ማኅሌታይ ሰብእ ዘከማሁ:
ያሬድ ካህን ለክርስቶስ ሰበከ ትንሣኤሁ:
ኢየዓዱ እንስሳ ወሰብእ እምነ ሠላስ ዜማሁ።


እምድኅረ ተንሥአ እሙታን መልዓ ስብሐቲሁ በጽዮን: ወተነግረ በመኃልየ መኃልይ ዘቤተክርስቲያን: በዘተሰምዩ ውሉዱ ውሉደ ብርሃን: ይኬልሕ ከመ ሱራፌል: ወጒህና ቃሉ ከመ ቃለ ቀርነ: አማን ጳዝዮን ዕንቊ ብርሃን ያሬድ ካህን።

ወስብሐት ወለመስቀሉ
ወወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ
ክቡር

✥✥✥► ◄✥✥✥            ✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟ወወሃብኮሙ ሲሳዮሙ ለሕዝበ ኢትዮጵያመዝ ፸፫፣፲፬ለኢትዮጵያ ሰዎችም ሲሳይን ሰጠሃቸው።============================ይህ...
18/05/2023

✥✥✥► ◄✥✥✥
✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟
ወወሃብኮሙ ሲሳዮሙ ለሕዝበ ኢትዮጵያመዝ ፸፫፣፲፬
ለኢትዮጵያ ሰዎችም ሲሳይን ሰጠሃቸው።
============================
ይህንን የቅዱስ ዳዊትን ኃይለ ቃል መተርጉማነ መጻሕፍት ሲተረጉሙ በኢትዮጵያ ምድር የሌለ የምግብም ሆነ የከርሰ ምድር ማዕድን እንደሌለ ፣ አንድም ለኢትዮጵያ ሰዎች ጥበብን ጸጋን ሰጠሃቸው፣ ፍጻሜው ግን ለኢትዮጵያ ሕዝብ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበትን የመላእክትን ምስጋና በዕዝል በግዕዝ ና በአራራይ የተዋበውን ማመስገኛ ጥበብ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ምግብ ነፍስን ሰጠሃቸው ማለት ነው ብለው ያመሰጥራሉ።
ይህ የማመስገኛ ዜማ ፣ጥበብ ደግሞ የተሰጠው በኢትዮጵያውያዊው ጻድቅ በቅዱስ ያሬድ አማካኝነት ነው። በዚህ ጻድቅ አማካኝነት የተደረሱት ማኅሌትና በእርሱ ዜማ የሚዜሙት ቅዳሴም ሆነ ሰዓታት በኢትዮጵያ ብቻ ነው የሚገኙት፣ ከዚህም የተነሳ ወወሃብኮሙ ሲሳዮሙ ለኢትዮጵያ ፣ ለኢትዮጵያውያን ልዩ ጸጋ ጥበብን ምግብ ነፍስን ሰጠሃቸው ማለት ነው። ለመሆኑ ይህን የመላእክትን ጥበብ ለኢትዮጵያውያን ከእግዚአብሔር የተቀበለው ቅዱስ ያሬድ ማን ነው?
ኢትየጵያዊዉ ቅዱስ ያሬድ ሚያዝያ ፭ ቀን ፭መቶ፭ ዓ/ም በአክሱም ከተማ ተወለደ፡፡እናቱ ታዉክሊያ/ክርስቲና/አባቱ ደግሞ ይስሐቅ/አብድዩ/ይባላሉ፡፡አባቱ የ አክሱም ጽዮን ቄሰ ገበዝ ነበር፡፡ያሬድ ሰባት ዓመት ሲሆነዉ አባቱ ስለሞቱበት እናቱ ት/ቤት ለማስገባት ወደ አጎቱ መምህር ጌዲዮን ጋር ወሰደችዉ፡፡አባ ጌድዮንም በአክሱም ቤተ ቀጢን(ቤተ ጉባኤ)መምህር ነበሩ፡፡ያሬድ ያኔ በትምህርቱ የሚያሳየዉ ዉጤት ደካማ ስለነበር ከሌሎች ህጻናት ጋር ሊወዳደር አልቻለም፡፡መምህሩ ጌዴዎን ለተግሣጽ ቢቀጡትም መታገስ ተስኖት ተስፋ ቆርጦ ከአክሱም ከተማ ወጥቶ ወደ እናቱ መንደር መደባይ ወለል ተጓዘ፡፡
ህጻን ያሬድ ከዛፍ ስር ተቀምጦ በምን ምክንያት ገጓደኞቹ በታች እንደሆነ ሲያዝን ሲተክዝ ቆየ፡፡ታደሰ አለማየሁ‹‹የቤተ ክርስቲያን ብርሀን ቅዱስ ያሬድ››በሚለዉ መጽሐፉ‹‹አንድ ትል የዛፉን ፍሬ ለመመገብ ፈልጎ ወደላይ እየወጣና እየወደቀ ተደጋጋሚ ሙከራ ሲያደርግ ከቆየ በኋላ በሰባተኛዉ ጊዜ ወጥቶ ፍሬዋን ሲመገብ ተመለከተ፡፡ያሬድም የዚህ ትል ተስፋ አለመቁረጥ ትዕግስቱን ጽናቱን ተመልክቶ‹እኔም ተስፋ ሳልቆርጥ ብዙ ጥረት ካደረኩ እንደዚህ ሊሳካልኝ ይችላል›ብሎ ወደ መምህሩ ለመመለስ ወሰነ ይላል››ያሬድ የ አጎቱ ምክርና ተግሣጽ ለሕይወቱ የሚጠቅም መሆኑን በመረዳቱ ትምህርቱን በትጋት ቢማርና ቢያጠና ያሰበዉ ደረጃ ለመድረስ እንደሚችል በመገንዘብ ወደ መምህሩ ጌዲዮን ጉባኤ ቤት ተመለሰ፡፡መምህሩም ተቀብለዉ አስተማሩት፡፡በአጭር ጊዜ አልገባ ያለዉ ትምህርት ተገልጾለት ትምህርቱን በሚገባ አጠናቀቀ፡፡በኋላም የብሉይና የሐዲስ መምህር ሆኖ በመምህሩ በጌዲዮን ወንበር ተተካ፡፡

የቅዱስ ያሬድ ዜማ እና ዓይነቶቹ
-----------------------------------------
የቅዱስ ያሬድ ዜማ በእግዚአብሔር ፈቃድ የተገለጸለት ለመሆኑ መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡ቅዱስ ያሬድ ዜማዉን ያዘጋጀዉ በሦስት ዓይነት ድምፅ ማለትም በግእዝ፣በዕዝል፣እና በዓራራይ ዜማ ነዉ፡፡እነዚህ የዜማ አይነቶች የአንዱ ድምፅ ከሌላኛዉ ድምፅ ያልተደበላለቀ ወጥ የሆነ ድምፅ አላቸዉ፡፡ዜማዎቹንም በስምንት ምልክቶች ቀምሮታል፡፡የምልክቶች አገልግሎትም በትምህርት ሂደት ጊዜ የጠቋሚነት ሚና በመጫወት ለዜማዉ መጠበቅ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ናቸዉ፡፡
ቅዱስ ያሬድና አፄ ገብረ መስቀል
ቅዱስ ያሬድ የተነሳዉ ዘጠኙ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ በገቡበት ዘመን ነዉ፡፡በዘጠኙ ቅዱሳን የተተረጎሙት ቅዱሳን መጻሕፍት
በቅዱስ ያሬድ የድርሰት ስራ ዉስጥ ጉልህ ድርሻ ነበራቸዉ፡፡ቅዱስ ያሬድ ከመጻሕፍቱ ያገኛቸዉን ምስጢራት ቃል በቃል እየጠቀሰ እንዲሁም ሐሳባቸዉን ጨምቆ በመዉሰድ በራሱ ቋንቋ እያራቀቀ ለድርሰቱ ተጠቅሞባቸዋል፡፡/ሰሎሞን ወንድሙ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ሕይወት፤1998 ገጽ15/፡፡
ቅዱስ ያሬድ ሙራደ ቃል በተባለ ቦታ ሆኖ ድምፁን ከፍ አድርጎ ሲያዜም ንጉሱ አፄ ገብረ መስቀል ከነሰራዊቶቻቸዉ ንግስቲቱ ከነደንገ ጡሮቿ ፣መሳፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ሊቃዉንቱና ካህናቱ አየመጡ ያዳምጡ ነበር ይላሉ ርእሰ ደብር ጥዑመ ልሳን ካሣ በመጽሐፋቸዉ፡፡
ቅዱስ ያሬድ በግእዝ፣በዕዝል በዓራራይ ዜማ ዝማሜ እየደረሰ እያለ ንጉሱ አፄ ገብረ መስቀል ተገኝተዉ ነበር፡፡በዜማዉ ተመስጠዉ አይን አይኑን እያዩ እንደ እርሱ እዘምማለሁ ብለዉ በያዙት የብረት ዘንግ ሳያዉቁት ቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ቸከሉት፡፡ሁለቱም በተመስጦ ስለነበሩ የሆነዉን ነገር አላስተዋሉትም ነበር፡፡ዜማዉ አብቅቶ ሁለቱም ከተመስጧቸዉ ሲነቁ የቅዱስ ያሬድ እግር ዘንጋቸዉ ተሰክቶ ብዙ ደም ፈሶት ነበር፡፡ንጉሡም ደንግጠዉ እጅግም አዝነዉ‹‹ደምህን አፍስሻለሁና የምትፈልገዉን ማንኛዉንም ነገር ጠይቀኝ እሰጠሃለሁ››ሲሉ ቃል ገቡለት፡፡ቅዱስ ያሬድም‹‹ይምለምነዉ አንድ ነገር አለ እርሱን ፈጽምልኝ››አላቸዉ፡፡‹‹የፈለከዉን ጠይቅ ፈቅጄልሃለሁ››አሉት፡፡እርሱም‹‹እስካሁን እግዚአብሔር በፈቀደልኝ መሰረት በዚህ ከተማ ከእርሰዎ ጋር ቆይቻለሁ፡፡ብዙ ደቀ መዛሙርትም ተክቼያለሁ፡፡ከእንግዲህ በኋላ የቀረኝን ዘመን በጸሎትና በብሕትዉና መኖር እንድችል ከከተማዉ ራቅ ወዳለ ቦታ ሔጄ ፈጣሪየን ማገልገል እፈልጋለሁ››ብሎ የንጉሱን ፈቃድ ጠየቀ፡፡
አፄ ገብረ መስቀልም የቅዱስ ያሬድን ቃል ሰማተዉ በዚያኑም በገቡለት ቃል መሰረት ፈቀዱለት፡፡ከዚያም ጉዞዉን ወደ ደቡብ አቅጣጫ ወደ ሰሜን ተራሮች አደረገ፡፡በዚያም አሁን በስሙ የታነጸዉ ቤተ ክርስቲያን ባለበት ቦታ ላይ በምናኔ ተወስኖ ፈጣሪዉን በብሕትዉና እያገለገለ ኖረ፡፡ምናኔ ደብረ ሐዊ ከተባለዉ ተራራ ላይ ብዙ ዓመታትን ካሳለፈ በኋላ በጸለምት ዋሻ በአንዱ ግንቦት 11 ቀን በ571 ዓ/ም ተሰወረ::

የቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች
=================
ቅዱስ ያሬድን ብቸኛ የግእዝ ሥነ ጽሑፍ መስራች አድርጎ ለማየት በቂ ምክንያት አለን፡፡እንዲያዉም የግእዝ ስነ ጽሑፍ መስራች ከማለት ይልቅ የኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ መሥራች ልንለዉ ይገባል፡፡/ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ኃይሌ የቅዱስ ያሬድ ታሪክና የግእዝ ስነ ጽሑፍ፤1999፤ገጽ3/ፕሮፌሰሩ በዚሁ ጥናታቸዉ እንዳብራሩት የግእዝ ስነ ጽሑፍን ለሁለት ልንከፍለዉ እንችላለን ይላሉ፡፡ምክንያቱን ሲያብራሩ፡-አንዱ ክፍል ከባህር ማዶ ተጽፈዉ ወደ ግእዝ የተተረጎሙትን መጻሕፍት ይይዛል፡፡ሁለተኛዉ ክፍል በቀጥታ በግእዝ የተደረሱትን ድርሰቶች ያጠቃልላል፡፡እነዚህም፡-የቅዱስ ያሬድ፣የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣የርቱዐ ሃይማኖት፣የ አፄ ዘርአ ያዕቆብ፣የ ዐርከ ሥሉስ፣የ አባ ባሕርይ ድርሰቶች የሚቀድም በ ግእዝ ቋንቋ የተደረሰ ድርሰት እስከ አሁን አለመገኝቱን ጥናቱ ያሳያል፡፡/1999፡3/
ቅዱስ ያሬድ ድርሰቶችን ሲያዘጋጅ ከቅዱሳን መጻሕፍት የወሰዳቸዉን ርእሰ ጉዳዮች በፈርጅ በፈርጁ እየለየ በድርሰት ሥራዎቹ እንደ ፈርጥ ተጠቅሞባቸዋል፡፡ብሉያትን ከሐዲሳት፣ከሊቃዉንት እያጣቀሰ ያለምንም ችግር የድርሰት ሥራዉን ሊያከናዉን ችሏል፡፡የቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች መንፈሳዊ ይዘት ያላቸዉ ናቸዉ፡፡በድርሰቶቹ የሚታዩት የቃላት አመራረጥ፣የ ዐረፍተ ነገር አወቃቀር፣የሚስጥር፣የዘይቤ አገላለጥ ቅዱስ ያሬድ ከፍተኛ የስነ-ጽሑፍ ተሰጥኦ እንደነበረዉ ለመረዳት ይቻላል፡፡በቅዱስ ያሬድ የተደረሱት የዜማ መጻሕፍት አምስት ናቸዉ፡፡እነርሱም ድጓ፣ጾመ ድጓ፣ዝማሬ፣ምሥዋዕትና ምዕራፍ ናቸዉ፡፡

፩•√ ድጓ፡-
-------------
የቅዱስ ያሬድ ትልቁ የዜማ መጻሕፍ ነዉ፡፡ድጓ ማለት ስብስብ ማለት ነዉ፡፡በዉስጡ የዓመቱን በዓላትና የሳምንታት መዝሙራት ሰብስቦ የያዘ ነዉ፡፡ይህ መጽሐፍ በዐበይት በዓላት በዜማ የሚቀርበዉን ምስጋና ሰብስቦ የያዘ የዜማ መድብል ነዉ፡፡ ድጓ በአራት ትልልቅ ክፍሎች ይከፈላል፡፡ይኸዉም፡-የዮሐንስ ድጓ፣አስተምህሮ ድጓ፣ጾመ ድጓ፣የፋሲካ ድጓ ተብሎ ይታወቃል፡፡

፪•√ ጾመ ድጓ፡-
-------------------
ሁለተኛዉ የዜማ መጽሐፍ ሲሆን የሚጠናና ለመምህርነት የሚያበቃ ነዉ፡፡ድጓ ቁጥሩ ከአስተምህሮ ሲሆን በዐቢይ ጾም የሚደርስ ራሱን የቻለ መጽሐፍ ነዉ፡፡

፫•√ ዝማሬ:-
---------------
ሦስተኛዉ የዜማ መጽሐፍ ነዉ፡፡ዝማሬ ምስጋና ማለት ነዉ፡፡ዝማሬ በጸሎተ ቅዳሴ ከድርገት በኋላ በቅዳሴ ማብቂያ አካባቢ የሚዜም የሚዘመር የጸሎተ ቅዳሴዉን ዓላማ ተከትሎ የሚሔድ ማለት ነዉ፡፡መጽሐፈ ዝማሬ በይዘቱ አምስት ነገሮች አሉት፡፡እነርሱም ኅብስት፣ጽዋ፣መንፈስ፣አኮቴት እና ምስጢር ናቸዉ፡፡

፬•√ መዋስዕት፡-
-----------------------
አራተኛዉ የዜማ መጽሐፍ ነዉ፡፡መዋስዕት የቃሉ ትርጓሜ ሁለት ዓይነት ነዉ፡፡አንደኛዉ ምልልስ ማለት ነዉ፡፡በግራና በቀኝ እየተመላለሰ ወይም እየተቀባበለ የሚባል ስለሆነ ነዉ፡፡የመዋስዕት ሁለተኛዉ ትርጉሙ ደግሞ የነፍስ መመላለስ(መሸጋገሪያ )ማለት ነዉ፡፡የ ኢየሱስ ክርስቶስን ጥምቀትን፣ሞቱን፣ትንሣኤዉን፣ዕርገቱን የሚያስረዳ ነዉ፡፡የመስዋዕት አገልግሎት ለሙታን ጸሎተ ፍትሐት ለማድረስ በበዓላትና በአጽዋማት ደግሞ ስብሐተ ነግሕ ለማድረስ ነዉ፡፡

፭•√ ምዕራፍ፡-
-----------------
የቅዱስ ያሬድ አምስተኛዉና የመጨረሻዉ የዜማ መጽሐፍ ነዉ፡፡የምዕራፍ ቀጥተኛ ትርጉሙ ማረፊያ ወይም ማሳረፊያ ማለት ነዉ፡፡ምዕራፍ ከመዝሙረ ዳዊት የተዉጣጣ ድርሰት ሲሆን የዳዊት መዝሙራትን በመስመር(ምዕራፍ)እየከፋፈለ የዜማዉን አይነትና ማሳረፊያ ይገልጻል።

የቅዱስ ያሬድ አስተዋጽኦ. ፣
-------------------------------
ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያን ለሀገርም ያደረገዉ አስተዋጽኦ ተዘርዝሮ አያልቅም፡፡በቤተ ክርስቲያንበ እያንዳንዱ አገልግሎት የሚወሳ ነዉ፡፡ሊቀ ሊቃዉንት ታፈሰ ደሳለኝ ስለ ቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰት አስተዋጽኦ ሲገልጹ‹‹የቤተ ክርስቲያናችን አምድ፣የውስጥ ማኅቶት፣የአፍ መብራት፣ በጠቅላላዉ የቤተ ክርስቲያን መንቀሳቀሻ ሕይወት ነዉ፡፡››በማለት ጽፈዋል፡፡/አይከብር፤1988፣18/፡፡ዶ/ር ዉቤ ካሣየም ቅዱስ ያሬድ ለሀገር ያበረከተዉን አስተዋጽኦ ሲገልጹ‹‹የቅዱስ ያሬድ ዜማ የመጠቁ፣የምንኮራባቸዉ፣የእኛን ማንነት ሊገልጹ የሚችሉ እና በድርሰቶቹ ዉስጥ ያሉት መልዕክቶች እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑ፣ከመጥፎ ነገር እንድንቆጠብ፣በጎ ነገርን እንድንይዝ፣ጥበብን እንድንፈልግ፣ሰላም እንዲኖረን የሚያስተምሩ ናቸዉ፡፡››ድርሰቶቹ ከመንፈሳዊዉ አስተምህሯቸዉ በተጨማሪ ሌሎች ሁኔታወችን በማንሳት የሚያብራሩ ናቸዉ፡፡››ብለዋል።

የቅዱስ ያሬድ ት/ቤት በኢትዮጵያ፣
----------------------------------------
በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እንደ ቅዱስ ያሬድ ብዙ የተጻፈለት፣የሚጻፍለት፣የተነገረለትና የሚነገርለት ኢትዮጵያዊ ቅዱስ የለም ማለት ይቻላል፡፡ቤተ ክርስቲያን ለቅዱስ ያሬድ ጽኑና ታላቅ ፍቅር የተነሣ ንጽሕናዉን‹ቅድስናዉንናመንፈሳዊ አገልግሎቱን አይታ በስሙ ጽላት ቀርጻ፣ቤተ ክርስቲያን አንጻ፣ገድል ጽፋ፣ ስታከብረዉና ስታመሰግነዉ ትኖራለች፡፡ሰሎሞን ወንድሙ‹‹ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ሕይወት››በሚለዉ መጽሐፉ ቤተ ክርስቲያን 1500 ዓመታት ያህል ለቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰት ሳትወጣ ተማሪ ቤት ከፍታ፣ወንበር ዘርግታ፣ዜማዉን ለትዉልድ እያስተማረች ስትገለገልበት መኖሯን ያስረዳል፡፡ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ኃይሌ ከዚህ የተለየ አስተያየት አላቸዉ፡፡‹‹የቅዱስ ያሬድ ታሪክና የግእዝ ስነ ጽሁፍ››በሚል ርእስ ባቀረቡት ጥናት‹‹የቅዱስ ያሬድ የኢትዮጵያ ታሪክ ሰዉ ሆኖ ሳለ ሊቃዉንቶቻችን ትምህርቱን ዓመታት እያሳለፉ፣መምህራን እያፈራረቁ፣በቅናት በጥንካሬና በኩራት ሲማሩ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ያሬድ ማን እንደሆነ ለማወቅና እኛንም ለማሳወቅ የሚገባዉን ምርምር ሲያደርጉ አልታየም፡፡››በማለት ያለዉን ክፍተት ያሳያሉ፡፡/1993፤3/፡፡ይሁን እንጅ አያሌ ኢትዮጵያንም የቅዱስ ያሬድን ዜማ ሲማሩና ሲያስተምሩ የሚያሳልፉትን ቤተ ክርስቲያን አክብራ፣ጠብቃ ስላቆየቻቸዉ ነዉ፡፡በቤተ ክርስቲያን የሊቅነት መስፈሪያ መለኪያ መስፈርት ሆነዉ ከሚቀርቡት ነገሮች አንዱ የያሬዳዊ ዜማ ዕዉቀት ነዉ፡፡ቤተ ክርስቲያኗ ለቅዱስ ያሬድ ያላትን አክብሮት ለመግለጽ በስሙ የሚጠራ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ምርያም ቅጽር አቋቁማለች፡፡ለመንግስትም ታሪኩን በማሳወቅ በአዲስ አበባ ከተማ ሰኔ 30 ቀን 1963 ዓ/ም በስሙ የሚጠራ የያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት እንዲከፈት አድርጋለች፡፡የሙዚቃ ት/ቤቱ ሲመረቅ ቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ‹‹ይህ ትምህርት ቤት እንዲቋቋም ያስቻለን ምክንያት ለዉጭዉ ሀገር ት/ቤት ብቻ አይደለም፡፡በመጀመሪያ የሀገራችን የዜማ ባሕልና ሥነ ሥርዓት ተጠብቆ በዚህ እንዲደራጅ በማሰብ ነዉ፡፡››በማለት ትምህርት ቤቱ የተከፈተበትን ምክንያት ገልጸዉ ነበር፡፡
በአጠቃላይ ቅዱስ ያሬድ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለዓለምም የመጀመሪያዉ ፈር ቀዳጅ በመሆኑ ዜማዉም ሆነ የዜማዉ መሳሪያ በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ መሠራት ያለበት መሆኑንና ቤተክርስቲያኒቱም ከቀድሞዉ በበለጠ ትኩረት መስጠት እንዳለባት የምሁራኑ ጥናት ያሳያል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
የአባታችን የቅዱስ ያሬድ በረከት ይደርብን።

Address

የቆሎ ተማሪ
Mizan Teferi
ኢትዮጵያ

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መ/ ኃ/ቀሲስ ሰሎሞን ያለው posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category