አርዮ አካደሚ Aryo Academy

አርዮ አካደሚ Aryo Academy በመልካም ሥነምግባርና በዕውቀት የታነፀ፣ ብቁ፣ ተወዳዳሪና ?

08/09/2025
የ2017 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ማጠናቀቅያ ፣የተማሪዎች ዉጤት መግለጫና የወላጆች  በዓል በሸካ ዞን ማሻ ከተማ የሚገኘዉ አሪዮ አካዳሚ ትምህርት ቤት ማክበሩ ተገለፀ።ማሻ ፣ የሰኔ 26፣ 20...
03/07/2025

የ2017 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ማጠናቀቅያ ፣የተማሪዎች ዉጤት መግለጫና የወላጆች በዓል በሸካ ዞን ማሻ ከተማ የሚገኘዉ አሪዮ አካዳሚ ትምህርት ቤት ማክበሩ ተገለፀ።

ማሻ ፣ የሰኔ 26፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ቅድመ መደበኛ ትምህርት ያጠናቀቁ ተማሪዎችንም አስመርቋል።
በሰኔ ወር የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ዓመቱን ሙሉ ሲደክሙበት የቆዩትን ዉጤት የሚያዩበት ወር እንደሆነ ይታወቃል።

አሪዮ አካዳሚ ትምህርት ቤት በተደራጁ ግለሰቦች የተከፈተ ሆኖ ከቅድመ መደበኛ እስከ አምስተኛ ክፍል የሀገሪቱን ትምህርት ፖሊሲ መሰረት አድርጎ በስነ ምግባር ታንፀዉ በእዉቀት የተካኑ ተማሪዎችን ለማፍራት እያስተማረ ቆይቷል።

ትምህርት ቤቱ በቅድመ መደበኛ ትምህርታቸዉን ያጠናቀቁ 28 ተማሪዎችን ያስመረቄ ሲሆን በመደበኛ ያስተማራቸዉንም በጥሩ ዉጤት ወደ ቀጣይ ክፍል አዛዉሯቸዋል ።

የአሪዮ አካዳሚ ት/ቤት ር/መ/ር ነገሱ ዱጉማ ትምህርት ቤቱ ተማሪዎቹን ዉጤታማ እንድሆኑ በትኩረት መሰራቱን ገልፀዉ የግባት እጥረትን ለመቅረፍ በቅንጂት መሰራት እንዳለበት አንስተዋሉ ።

በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙ ወላጆችም ልጆቻቸዉ በስነ ምግባርም ሆነ በእዉቀት እየተለወጡ መምጣታቸዉን ተናግረዉ የግብዓት እጥረትን ለሟሟላት የድርሻቸዉን እንደሚወጡ ሀሳብ ሰጥተዋል።

ከማሻ ከተማ ት/ፅ/ቤት በክበረ በዓሉ የተገኙት የምህርት ቤት መሻሻል ባለሙያ ወ/ሮ እመኙሻል አምበሎ ት/ቤቱ ጥሩ ተግባራትን እያከናወነ ያለዉ ስራ አመስግነዉ ቀጣይ የበለጠ ዉጤት ለማስመዝገብ የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ያስፈልጋል ብለዋል ።

ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ማፍራት አለብን ያሉት የአሪዮ አካዳሚ ትምህርት ቤት ቦርድ ሰብሳቢ ዶክቴር ጀመሬ ቆጭቶ ልጆች በጥሩ ስነምግባር የተሻለ ዉጤት እንድያስመዘግቡ ትምህርት ቤቱ እያደረገ ያለዉን ጥረት ወላጆች ሊያግዙ እንደሚገባዉ አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም ደረጃ ላገኙ ተማሪዎች የተለያዩ ሽልማቶች ተሰጥቶላቸዉ የተማሪ ወላጅ ክብረ በዓል ፕሮግራም ቋጭቷል።

ዘጋቢ ግርማ ጮሪቶ

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉትን ትክክለኛ አድራሻዎቻችንን ይከታተሉ።
◆ፌስቡክ https://www.facebook.com/
◆ ቴሌግራም
https://t.me/Mashafmofficial
◆ ዩቲዩብ https://www.youtube.com/
◆ ዩቲዩብ የቀጥታ ስርጭት
https://www.youtube.com/
◆ ቲክቶክ
https://www.tiktok.com/
◆ ኢንስታግራም
https://instagram.com/mashafm2023?igshid
◆ ቲውተር
https://twitter.com/masha_fm98
◆ ዋትሳፕ
https://whatsapp.com/dl/
◆ ድረገጽ
www.mashafm.gov.et

አርዮ አካዳሚ በተሻለ ርምጃ ላይ ነውት/ቤቱ አርብ መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓም የተማሪ ወላጆችና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት የ2017 ት/ዘመን የግማሽ ዓመት  ዕቅድ አፈፃፀምና የተማሪዎች ...
30/03/2025

አርዮ አካዳሚ በተሻለ ርምጃ ላይ ነው
ት/ቤቱ አርብ መጋቢት 18 ቀን 2017 ዓም የተማሪ ወላጆችና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት የ2017 ት/ዘመን የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምና የተማሪዎች ውጤት ሪፖርት አቅርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በግማሽ ዓመት ትምህርት ውጤት ከየክፍልና ከአጠቃላይ ብልጫ በማምጣት ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለወጡ ተማሪዎች ማበረታቻ ምስክር ወረቀት ተሠጥቷቸዋል። እንድሁም በህፃናት ክትትል፣ ድጋፍና፣ የወላጅ ግዴታ በመፈፀም ግምባር ቀደም ለሆኑ ወላጆች የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሠጥቷቸዋል። በዕለቱ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በሚባል ሁኔታ የተማሪዎች ወላጆች በመገኘታቸው የትምህርት ቤቱ ሥራ አመራር ቦርድ ከፍ ያለ ምስጋና አቅርቧል።
በዕለቱ የተገኙት ተጋባዥ እንግዳ የነበሩት የማሻ ከተማ ት/ጽ/ቤት ተወካይ አቶ ግርማ አቾሞ በት/ቤቱ አሠራርና ውጤታማ ተማሪ ለመፍጠር እየተደረገ ባለው ትጋት ተደንቀው ሰፊ የማበረታቻ አሰተያየት በመስጠት አሁን ት/ቤቱ የደረሰበት ደረጃ ከሌሎች አንፃር የተሻለ ስለሆነ የበለጠ በማሻሻል ከደረጃ 2 ወደ ደረጃ 3 ለመሸጋገር ተግቶ እንዲሠራ የሥራ መመሪያ ሠጥቷል። አቶ ግርማ አቾሞ ከተደነቁባቸው ሥራዎች
1ኛ) ት/ቤቱ የቤት ኪራይና የመ/ራን ደመወዝ ለመክፈል ከፍተኛ የገንዘብ እጥረትና የዕዳ ጫና እያለበት ለመክፈል አቅም የሌላቸው የደሃ ቤተሰብ ልጆች የሆኑ 3 በላይ ተማሪዎችን በየዓመቱ በነፃ እያስተማረ መቆየቱን በማየታቸው ለትርፍ ንግድ ሳይሆን አከባቢውን ለማገዝ ያለመ ት/ቤት ነው ብለዋል። ሌሎች ት/ቤቶችም መልካም አርአያነቱን ማስፋት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
2ኛ) ት/ቤቱ የገንዘብና የግብኣት(የመጽሐፍ) እጥረት እያለበት በተማሪ ውጤትና ትምህርት ጥራት ላይ በየዓመቱ ጎልቶ የሚታይ ዕድገት ማስመዝገብ ላይ መሆኑ በሱፔርቪዥንና እንስፔክሽን የተረጋገጠ ቢሆንም ዛሬ ተግባራዊ ሁኔታ ያሳዩ ተማሪዎች ድንቅ ብቃት ስመለከት ት/ቤቱ በገንዘብና በግብኣቶች ቢደገፍ ለአከባቢው ድንቅ ብቃት ያላቸው ተማሪዎችን እንደሚፈጥር እምነት ይጣልበታል ብለዋል። ለዚህም የተማሪው ወላጆችና የአከባቢው መንግሥት ድርሻ የጎላ መሆኑን አስገንዝበዋል።
3ኛ) የመምህራኑን ብቃት ለማሻሻልና ተነሳሽነት ለመጨመር ተከታታይነት ያለው ስልጠና ለሁሉም መ/ራን ከመሠጠቱ በላይ ለኬጂ(ቅድመ መደበኛ ተማሪዎች) ልዩ ስልጠና መሠጠቱ የሙያ ክፍተት በመሙላት ለተሻለ አፈፃፀም ይረዳል
4ኛ) የተማሪዎች ውጤት በብቃት ደረጃቸው የተተነተነበት (ትወራ) አሳማኝና ተማሪዎችን ብቃት ለይቶ ለመደገፍ ምቹ መሆኑ
5ኛ) የተማሪዎች ውጤት በየትምህርት ዓይነት ተለይቶ የየክፍሉ አማካይ መለየቱ ለወደፊቱ ጉድለቶችን ለይቶ ለመደገፍ ጠቃሚ በመሆኑ ይህ ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል በአቶ ግርማ አቾሞ አጽንኦት ተሰጥቶበታል።

በዕለቱ የተገኙ የተማሪ ወላጆችም ከ2012 ዓም ጀምሮ በኪራይ ቤት ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለ፣ ትርፍ ሳይሆን ወጪውን ሳይሸፍን በከፍተኛ ኪሳራ ውስጥ ሆኖ እየሠራ በየጊዜው በተማሪዎች ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ያለ ት/ቤት መሆኑን መስክረው ት/ቤቱ ለወደፊቱ የራሱ ግቢና መማሪያ ክፍሎች እንዲኖሩት አሳስበዋል። ባጠቃላይ ወላጆች ት/ቤቱ የልጆቻችን የወደፊት ተስፋ መሆኑን ዛሬ ከቀረበው በዓይን የሚታይ ተጨባጭ ሪፖርት፣ ግልጽ ውይይትና ከተማሪዎች ተግባራዊ ብቃት ስለተረዳንና በትምህርት ቤቱ ቀጣይነት ላይ ስላመንንበት በሚንችለው መልኩ ት/ቤቱን እንደግፋለን ብለዋል። አንዳንድ ወላጆችም ከወራዊ ክፍያ በተጨማሪ በግል ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል።

የት/ቤቱ ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ጀመረ ቆጭቶ ከመጋቢት 16 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ የት/ቤቱን አጠቃላይ ሁኔታና የሪፖርቱን ተዓማኒነት በመገምገም በግልፀኝነት ለወላጆችና ባለድረሻ አካላት እንዲቀርብ አድርገዋል። የቦርድ ሰብሳቢው በሠጡት ማጠቃለያ ሀሳብ መጨረሻ ላይ ከወላጆችና ከባለድርሻ አካላት ከተነሱ ሀሳቦችን የተገነዘብነው በአወንታዊነት በጋራ ት/ቤቱን ወደፊት እናሸጋግራለን፣ የሚያስፈልገውን መስዋዕትነት በጋራ እንከፍላለን የሚል ቃል ኪዳን ሲሆን ከ2012 ዓም እስካሁን የመጣንበት ሁኔታ እጅግ ፈታኝና ት/ቤቱን የሚያስዘጉ ቢሆንም በይሉኝታ ተሸብበን መከራችንን በውስጣችን ይዘን መልካም ውጤት ብቻ አሳይተን ዞር ለማለት ያሰብን ሲሆን ዛሬ ግን ድንገት ወላጆች የገቡት ቃል ኪዳን ሳናስበው ያንን ሁሉ የመከራና የኪሳራ ጊዜ ረስተን ከሕዝቡ ጋር የወደፊቱን ተስፋ አሻግሬን እንዲናይ ያደረገ ነው ካሉ በኋላ አርዮ አካዳሚ በትውልዶች ቅብብሎሽ ለዘላለም ይቀጥላል በማለት ቃል በመግባት ይህንን ተረድተው በዋናነት የማሻ ከተማ አስተዳደር ኬንቲባና ማዘጋጃ ቤት ፈጣን መልስ በተግባር እንደሚሠጡ እምነታችን የፀና ነው ብለዋል።

በዕውቀትና በመልካም ሥነምግባር የታነፀ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ የመቅረጽ ራዕያችን በጋራ ጥረት ይሳካል።

አርዮ አካዳሚ
መጋቢት 19 ቀን 2017 ዓም
ማሻ

18/07/2024
ለተሻለ ለውጥ ሁል ጊዜ ሥራ ላይ ነን!በ2016 ዓም ያደረግነውን የአሠራርና የአመራር ለውጥን ተከትሎ በተፈጠረው የሥራ ትጋት አርዮ አካዳሚ ወደማይቀለበስበት ደረጃ ተሸጋግሯል። ይህንንም በ20...
18/07/2024

ለተሻለ ለውጥ ሁል ጊዜ ሥራ ላይ ነን!
በ2016 ዓም ያደረግነውን የአሠራርና የአመራር ለውጥን ተከትሎ በተፈጠረው የሥራ ትጋት አርዮ አካዳሚ ወደማይቀለበስበት ደረጃ ተሸጋግሯል። ይህንንም በ2016 ትምህርት ዘመን ማጠቃልያና የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች ምረቃ በዓል ላይ የተገኙ ወላጆች አርዮ አካዳሚ ወደ ተሻለ ደረጃ እየተሸጋገረ ያለ ምርጫቸው መሆኑን በደስታ አረጋግጠዋል። ከዚህ በተጨማሪ
1) የትምህርት ቤቶችን ደረጃና ምቹነትን ለማረጋገጥ በተለያዩ የግልና የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ተዘዋውሮ በአካል በመገኘት የገመገመው የዞኑ እንስፔክሽን ቡድን ትምህርት ቤቱ የደረጃ 2 መስፈርት ከበቂ በላይ ያሟላ ሲሆን ወደተፈላጊው ደረጃ 3 ለመሸጋገር አስፈላጊ መስፈርቶችን ማሟላት እንዳለበት ገንቢ ምክረ ሀሳብ ሠጥቷል። በዚሁ መሠረት የተሠጠውን ምክረ ሀሳብ በመቀበል ለማሟላት ሰፊ ጥረት ማድረግ ጀምረናል።
2) ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች መማር ማስተማርና ጤና ምቹ መሆናቸውን ክትትልና ቁጥጥር ሲያደርግ የነበረው የማሻ ከተማ አስተዳደር ጤና እንስፔክሽን ቡድንም አርዮ አካዳሚ በ2016 ዓም በሠራው ሥራ ለመማር ማስተማርና ለህፃናት ጤና ምቹ መሆኑን በማረጋገጥ የጤና ሞዴልነት ምስክር ወረቀት ከመስጠቱም በላይ የቁሳቁስ ሽልማት በማበርከት የህፃናት ማረፍያ ክፍል እንዲደራጅ አድርጓል።
3) ቀደም ባሉ ዓመታት በአርዮ አካዳሚ ትምህርታቸውን ስከታተሉ ቆይተው በቤተሰብ ዝውውር ምክንያት ወደ ሌሎች ከተሞች የሄዱትና እዚሁ ማሻ ከተማም እኛ ዘንድ ያለውን ደረጃ በማጠናቀቅ ወደ ሌሎች ት/ቤቶች የተዛወሩ ተማሪዎች እያስመዘገቡ ያሉት የብልጫ ውጤትና የስኬታቸው ዜና በስፋት እየሰማን ስለሆነ እጀግም በጣም ደስ እያለን ነው።

ስለዚህ እኛም ራዕያችንን ተረድተው የሙያ ድጋፍና አስፈላጊ ቁሳቁስ እየሠጡ ያሉትን የሸካ ዞን ት/መምሪያ፣ የማሻ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት፣ ማሻ ከተማ ጤና ጽ/ቤት፣ ወላጆችና ግለሰቦችን ሁሉ ከልብ እያመሰገንን በተፈጠረው ለውጥ በመነቃቃት በ2017 የትምህርት ዘመን የተሻለ ሥራ ለመሥራት ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆናችን እናሳውቃለን።

አርዮ አካዳሚ አማራጭ ሳይሆን ትክክለኛው ምርጫ እየሆነ ነው!

የትጋትና የመልካም አርአያነት ውጤት!
08/07/2024

የትጋትና የመልካም አርአያነት ውጤት!

🎓🎓
ፕሮፌሰር ባዬ ይማም (አባት) እና ፕሮፌሰር ቃለአብ ባዬ ይማም (ልጅ)

👉ሁለቱም የከፍተኛ ትምህርት ህይወታቸውን በአንጋፋው ዩኒቨርሲቲያችን ጀምረው በሞያቸው ዩኒቨርሲቲያችንን እያገለገሉና ተተኪ ምሁራንን እያፈሩ የሚገኙ ፕሮፌሰሮች ናቸው።

👉ፕሮፌሰር ባዬ ይማም 44 ዓመታትን እንዲሁም ፕሮፌሰር ቃለዓብ ባዬ 15 ዓመታትን በመምህርነት፣ በተመራማሪነት፣ እንዲሁም በተለያዩ የስራ ሀላፊነቶች ያገለገሉ እና እያገለገሉ የሚገኙ ምሁራን ናቸው።

👉ሁለቱም የፒኤችዲ ዲግሪያቸውን በሰሩ ልክ በ10ኛው አመት የሙሉ የፕሮፌሰርነት ማዕረግን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያገኙ ናቸው።

👉ፕሮፌሰር ቃለዓብ ባዬ በዘንድሮው ዓመት የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ከሰጣቸው ምሁራን መካከል ናቸው። ማዕረጉ የተሰጣቸው በማስተማር ውጤታማነት፤ ባሳተሟቸው ጥናታዊ ጹሁፎች፤ ለማህበረሰብ ላበረከቱት አካዳሚያዊ አገልግሎትና በዩኒቨርሲቲው በነበራቸው የተቋም አስተዳደር ድምር ውጤት ነው።

አርዮ አካዳሚ በብርታቱ ቀጥሏል!የ2016 ዓም የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች ምረቃና የወላጆች በዓል ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓም በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። በበዓሉ የተሳተፉ ወላጆች ትምህርት ቤቱ በየ...
08/07/2024

አርዮ አካዳሚ በብርታቱ ቀጥሏል!

የ2016 ዓም የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች ምረቃና የወላጆች በዓል ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓም በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። በበዓሉ የተሳተፉ ወላጆች ትምህርት ቤቱ በየጊዜው በመሻሻልና በዕድገት ጎዳና ላይ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልፀዋል።
የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ከሐምሌ 1ቀን 2016 ዓም ጀምሮ ይሠጣል!!!

የካቲት 11 ቀን 2016 ዓም የት/ቤቱ ቦርድ አባላት፣ ወመህ፣ ወላጆችና ተማሪዎች በተገኙበት የግማሽ ዓመት የመማር ማስተማር ሥራ አፈፃፀም ተገምግሟል። አብላጫ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ማበ...
18/03/2024

የካቲት 11 ቀን 2016 ዓም የት/ቤቱ ቦርድ አባላት፣ ወመህ፣ ወላጆችና ተማሪዎች በተገኙበት የግማሽ ዓመት የመማር ማስተማር ሥራ አፈፃፀም ተገምግሟል። አብላጫ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ማበረታቻ ሽልማት ተስጥቷቸዋል። ወላጆችም ትምህርት ቤቱን በመልካም አፈፃፀሙ አመስግነው መስተካከል የሚገባቸው ደካማ ጎኖችን በግልፀኝነት አስቀምጠዋል። ት/ቤቱም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በወላጆች አስተያየት መሠረት በርካታ ማሻሻያዎችን አድርጓል።
አርዮ አካዳሚ በማህበረሰቡ ጥረትና ድጋፍ እየተሻሻለ የሚቀጥል ት/ቤት!!!

23/11/2023

የትምህርት ጥራት ጉዳይ የአንድ ሰሞን ሞቅታ መሆን የለበትም። ተከታታይነት ይኑረው። የትምህርት ሥራው ከሥር ከቅድመ መደበኛ (ከኬጂ) ጀምሮ በጥንቃቄ መመራት አለበት።
የ12 ክፍል ተማሪ ይህንን ያህል ብቻ አለፈ ብሎ ተንጫጭቶ ዝም ማለት ዋጋ የለውም።
እንደዞናችን ከዛሬዋ ቀን ጀምሮ ቀጣይ ምን መሠራት አለበት? እስቲ ራስዎንም ተሳታፊ የሚያደርጉ ሀሳቦችን ያቅርቡ!
የመጽሐፍት ሕትመት ጉዳይስ ከምን ደረሰ???

Address

Masha

Telephone

+251912202360

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አርዮ አካደሚ Aryo Academy posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to አርዮ አካደሚ Aryo Academy:

Shortcuts

Share