Kombolcha Polytechnic College

Kombolcha Polytechnic College Welcome to Kombolcha Polytechnic College's page: A College Striding for Quality Training!

በንብ ማነብና የግብርና ግብአት አቅርቦት ላይ ለተሰማሩ 89 ወጣቶች ሲሰጥ የነበረው አጫጭር ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ......................................በንብ ማነብና ...
24/08/2026

በንብ ማነብና የግብርና ግብአት አቅርቦት ላይ ለተሰማሩ 89 ወጣቶች ሲሰጥ የነበረው አጫጭር ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ......................................

በንብ ማነብና የግብርና ግብአት አቅርቦት ላይ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅና ማያ ፕሮግራም (MaYEA Program) የጋራ ትብብር ሲስጥ የሰነበተዉ የአጫጭር ስልጠና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

መጣቶቹ ማያ ፕሮግራም (Mass Youth Employment in Apiculture- MaYEA Program) በተሰኘ ድርጅት ተመልምለው የመጡ ሲሆን በግብርና ዘርፍ ብቃታቸው በተረጋገጠ የኮሌጁ መምህራን ስልጠናውን ወስደዋል። በግብርና ግብአት አቅርቦት ላይ ለተሰማሩ 48 ሰልጣኞች የንግድ ስራ ክህሎት ስልጠና እንዲሁም ለ41 ሰልጣኞች ደግሞ በንብ ማነብና ለንብ ማነብ ስራ በሚሆኑ ግባቶች ማምረት እና መሸጥ ላይ ስልጠናው ተሰጥቷል።

ስልጠናው የተሰጠው ከቃሉ፣ ዳዋ ጨፋ፣ ከባቲ፣ ጭፍራ፣ ከሚሴ፣ አርጎባና ወረባቦ ወረዳዎች ለተውጣጡ 89 ወጣቶች ሲሆን ዓላማውም ስልጣኞቹ የንግድ አስተዳደር ክህሎትን እንዲያደብሩ፣ የንግድ ምርታማነትና የገበያ ጥናት መንገዶችን እንዲረዱ፣ በንግድ ህጎች ላይ ግንዛቤ እንዳዳብሩ፣ በግብርና ስራ ላይ ለተሰማሩ የግብርና ግብአቶችን ማቅረብ፣ ንብ ለሚያንቡ ኢንተርፕራዞች የንብ ግብአትና መሳሪያዎችን ማቅረብ እንዲችሉና የመረጃ ልውውጥና የግንኙነት መረባቸውን ማሳደግ የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው።

በንግድ ስራ ክህሎት ላይ ያተኮረዉን ስልጠና የሰጡት የአግሮፕሮሰሲንግ ሊቁ አቶ ሙሃመድ በላይና የሆርቲካልቸር ምሁሩ አቶ ታደሰ ያሲን ሲሆኑ በንብ ማነብና ግብአት አቅርቦት ላይ ደግሞ በእንሰሳት ሀብት የሙያ ባለቤት የሆኑት አቶ ዋሲሁን መኮነን አስልጥነዋል።

በህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ቡድን
ነሀሴ 17፣ 2018

በአቤቱታና ቅሬታ አቀራረብ፣ አወሳሰንና የዲስፕሊን አፈፃፀም ሥነ ሥርዓት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ************************                        የኮም...
20/08/2026

በአቤቱታና ቅሬታ አቀራረብ፣ አወሳሰንና የዲስፕሊን አፈፃፀም ሥነ ሥርዓት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
************************

የኮምበልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠና ዘርፍ አስተባባሪዎች፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ተሻሽሎ በወጣው የመንግስት ሠራተኞች የቅሬታ አቀራረብ አወሳሰንና የዲስፕሊን አፈፃፀም ሥነ ሥርዓት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ወሰዱ።

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በተሻሻለው የሀዝብ ቅሬታ አቀራረብ፣ ምርመራና አወሳሰን ሥነ-ሥርዓት መወሰኛ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 130/2007 እና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች ዲስፕሊን አፈፃፀምና የቅሬታ አቀራረብ ሥነ ሥርዓትን ለመወሰን በወጣው የክልል መስተዳድር ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 75 /2003 ላይ የኮሌጁ የአቤቱታና ቅሬታ አፈታት ባለሙያ አቶ ሀሰን ኢብራሂም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዉን ሰጥተዋል።

ደንቡን የማዉጣት አስፈላጊነት በተመለከተ አቤቱታና ቅሬታ ሰሚ ባለሙያው አቶ ሀሰን ኢብራሂም ሲያብራሩ የመንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና በተገልጋዩ ሀብረተሰብ ዘንድ ለሚነሱ ጥያቄዎች በወቅቱ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት፤ ቅሬታዎች የሚቀርቡበትን፤ የሚጣሩበትንና ተገቢ ውሳኔ የሚያገኙበትን ሥርዓት ለማበጀት፤ መንግስታዊ ሃላፊነትን ካለመወጣት የተነሳ የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ጉድለት ተፈፅሞ ቢገኝ የባለስልጣናትን ተጠያቄነት ከወዲሁ ለማረጋገጥ የሚስችል አደረጃጀት በየአስተዳደር እርከኑ ለመፍጠር ከፍትኛ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።

የኮሌጁ አቤቱታና ቅሬታ ሰሚ ባለሙያው አቶ ሀሰን ኢብራሂም እንዳሉት በክልሉ ምክር ቤት ተሻሻሎ በወጣው የመንግስት ሠራተኞች የቅሬታ አቀራረብ አወሳሰንና የዲስፕሊን አፈፃፀም ሥነ ሥርዐት ላይ ለሠራተኞች ግንዛቤ ማስጨበጥ ሠራተኞቻችን መብትና ግዴታቸውን አውቀው ሥራቸውን በተገቢው መንገድ እንድከውኑ ያስችላቸዋል።

በህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ቡድን
ነሀሴ 14፣ 2018

Assessments are being conducted under the new holistic competency assessment system!****** ******* ******* ***Kombolcha ...
19/08/2026

Assessments are being conducted under the new holistic competency assessment system!
****** ******* ******* ***

Kombolcha Polytechnic College has been conducting competency assessments in various professions since 2024, when it switched from the previously Level Based Competence Assessment to the new holistic assessment system.

The college has been conducting competency assessments for 167 candidates in Electricity, ICT, Fashion Design, Garment Production, Mechanic, Road Construction, Structural Construction and Beekeeping since August 17, 2026, and the assessment will continue until August 21, 2026, according to information obtained from the assessment coordinators.

By Amanuel Endris
Public Relations and Communication Specialist
August 19/2018

በአዲሱ የአጠቃላይ (holistic) የብቃት ምዘና ስርዐትመሰረት ምዘና እየተሰጠ ነው!************************የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቀደም ሲል ደረጃን መሠረት አድርጎ ሲሰ...
19/08/2026

በአዲሱ የአጠቃላይ (holistic) የብቃት ምዘና ስርዐትመሰረት ምዘና እየተሰጠ ነው!
************************

የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቀደም ሲል ደረጃን መሠረት አድርጎ ሲሰጥ የነበረው የብቃት ማረጋገጫ ምዘና (Level Based Competence Assessment) ቀርቶ በአዲሱ አጠቃላይ (holistic) የምዘና አሰጣጥ ስርዐት ምዘና መስጠት ከጀመረበት ከ2016 ጀምሮ በተለያዩ ሙያዎች የብቃት ማረጋገጫ ምዘና እየሰጠ ይገኛል።

ኮሌጁ ከነሃሴ 11/2018 ጀምሮ በኤሌክትሪሲቲ፣ በICT፣ በፋሽን ዲዛይን፣ በአልባሳት ምርት፣ በመካኒክስ፣ በመንገድ ሥራ፣ በመዋቅራዊ ግንባታና በንብ ማነብ 167 የሚሆኑ ተመዛኞችን የብቃት ማረጋገጫ ምዘና በማስመዘን ላይ ሲሆን ምዘናውም እስከ ነሃሴ 15፣ 2018 እንደሚቆይ ከምዘና አሰተባባሪዎች በተገኘ መረጃ ማዎቅ ችለናል።

በአማኑኤል እንድሪስ
የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ባለሙያ
ነሃሴ 13/2018

በአዳዲስና በተሻሻሉ የመመሪያ ሰነዶች ላይ ስልጠናዊ ውይይት እያካሄዱ ነውበኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት መምሪያ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ቡድን ባለሙያዎችና የኮ...
06/08/2026

በአዳዲስና በተሻሻሉ የመመሪያ ሰነዶች ላይ ስልጠናዊ ውይይት እያካሄዱ ነው

በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት መምሪያ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ቡድን ባለሙያዎችና የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ አስተባባሪዎች በአዳዲስና በተሻሻሉ አራት ሰነዶች ላይ ስልጠናዊ ውይይት እያካሄዱ ነው::

በከተማ አሰተዳደሩ ሥራና ክህሎት መምሪያ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ባለሙያዎችና የኮሌጁ የዘፍ ተጠሪዎች በጥቃቅን አነስተኛና፣ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የሥራ ቡድን አደረጃጀትና ትግበራ አሰራር ማንዋል፣ በጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ሽግግር አፈፃፀም መመሪያና በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት አተገባበር መመሪያ እንዲሁም በሞዴል ፈጠራ፣ ምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስፋት አተገባበር መመሪያ ላይ እያካሄዱ ያለዉ ስልጠናዊ ውይይት ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።

በጧቱ ክፍለ ጊዜ በመድረኩ ተገኝተን እንደተከታተልነው የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት መምሪያ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ቡድን መሪ አቶ ሰይድ አደም የሞዴል ፈጠራ፣ ምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስፋት አተገባበር መመሪያ ሰነዱን አቅርበዋል።

በኮሌጁ ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ቡድን
ሀምሌ 30፣ 2018

ኮሌጁ በብቃት ደረጃዎችና በድግሪ መርሃ ግብር ተቀብሎ ያሰለጠናቸውን 551 ሰልጣኞች እስመረቀየመክፈቻ ስርዐት ንግግር ያደረጉት የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ኤርምያስ ጌትነት እንደተና...
02/08/2026

ኮሌጁ በብቃት ደረጃዎችና በድግሪ መርሃ ግብር ተቀብሎ ያሰለጠናቸውን 551 ሰልጣኞች እስመረቀ

የመክፈቻ ስርዐት ንግግር ያደረጉት የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ኤርምያስ ጌትነት እንደተናገሩት የዛሬው ቀን እንደማንኛው በቀን መቁጠሪያ ላይ እንደለ ተራ ቀን ሳይሆን የረጅም ጊዜ ህልምና ምኞት ወደ ተግባራዊና ተጨባጭ እውነታ፣ የዓመታት ድካም ወደ ድል የተቀየረበት ቀን እንዲሁም የበርካታ እንቅልፍ አልባ ሌሊቶች ፍሬ አፍርተዉ ያያችሁበት ቀን በመሆኑ ተመራቂዎችንና የተመራቂ ወላጆችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ቴክኒክና ሙያ የሀገር ልማት አንቀሳቃስሽ ሞተር ነው ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ኤርምያስ ጌትነት ኮሌጁ ከተለመደው የመደበኛ ስልጠና አሰጣጥ በላይ በመሄድ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለዉ የኢንዱስትሪ ፍላጎት ተወዳዳሪ የሆነና ብቃቱ የተረጋገጠ የሰለጠነ ባለሙያ ለማፍራት የሚያስችለውን ዓለም አቀፍ የስልጠና ጥራት ማስጠበቂያ ስርዐት- ISO 9001:2015 ተግባራዊ በማድረግ ከጥራት ደረጃዎች ማረጋገጫ ድርጅት እውቅና ተሰጥቷል ብለዋዋል። የኮሌጁ ዲን አያይዘው እንደተናገሩት ኮሌጁ በአውቶሞቲቭ ዘርፍ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል ለመሆን ከዓለም ባንክ ባገኘው የፕሮጀክት ገንዘብ ድጋፍ አሰፈላጊውን ሥራ ሁሉ በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

የሥራ ገበያውን መሰረት ባደረገ የስልጠና አሰጣጥ ስርዐት ላይ ተመስርቶ ስልጠና እየሰጠ ያለው የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በICT፣ ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ አውቶሞቲቭና ቴክስታይል-ጋርመንት ስልጠና ዘርፎች በተለያዩ የሙያ አይነቶች ከደረጃ II እስከ ደረጃ V ቀብሎ ያስለጠናቸውን 290 ወንድና 142 ሴት በድምሩ 432 ስልጣኞችን አሰመርቋል።

የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሳተላይት ካምፓስ እንደመሆኑ መጠን በአውቶሞቲቭና በማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ በድግሪ መርሃ ግብሩ ተቀብሎ ያስለጠናቸውን 119 (ወንድ 107፣ ሴት 12) ስልጣኞቹንም አሰመርቋል፤ በአጠቃላይ በብቃት ደረጃዎችና በሳተላይት የድግሪ መርሃ ግብሩ 551 (ወንድ- 307፣ ሴት- 154) ስልጣኞች ሼኽ ሳቢር አካባቢ በሚገኘው የኮሌጁ ዋናው ግቢ በዛሬው እለት በደማቅ ስነ-ስርዐት ተመርቀዋል።

በምረቃ ስነ ስርዐቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባና የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሙሃመድ እሚን ለተመራቂ ሰልጣኞች የሥራ ስምሪት ሲሰጡ እንደተናገሩት የዛሬ ተመራቂዎች አሁን ከደረሳችሁበት ለመድረስ ከልጅነት እስከ እውቀት ከቤተሰባች ጋር ይህ ነው የማይባል ለቁጥር አዳጋች የሆነ ዋጋ ከፍላችኋል፤ ነገር ግን ይህ የመከራ ዋጋ ወደሌላኛው ጣፋጭ የህይወት ምዕራፍ የምትሸጋገሩበት ድልድይ በመሆኑ ልዩ ደስታ ሊሰማችሁ ይገባል ብለዋል።

ክቡር ከንቲባው አቶ ሙሃመድ አሚን እንዳሉት ትምህርት ማቆሚያ የሌለው የህይወት የእድሜ ልክ መሻሻል በመሆኑ በሥራው ዓለም ተሰማርታችሁ ከሰፊው ማህበረስብ ጋር ስትቀላቀሉ ከፊት ለፊታችሁ የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች ሊገጥሟችሁ ይችላሉ፤ እነዚህን ፈተናዎች ማሸነፍ የምትችሉበት ብቸኛው መንገድ በዳበረ መልካም ስነ ምግባር በመሆኑ በተሰማራችሁበት ሙያ ሀገራችሁን የምትወዱ የመልካም ስነ ምግባር ባለቤት መሆን አለባችሁ ሲሉ ለተመራቂዎች በሳል ምክር መክረዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኮሌጁ የቴክስታይል ጋር መንት ስልጠና ዘርፍ ስልጣኞች በራሳቸው የሠሯቸውን የተለያዩ አልባሳት ምርት ውጤቶች ለብሰው የፋሽን ሾው ትርኢት አሳይተዋል።

በዚህ የሰልጣኞች ምረቃ ስርዐት ላይ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የተመራቂ ወላጆች፣ የኢንዱሰትሪ ተዎካዮች፣ የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላትና ሠራተኞች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በመጨረሻም በስልጠና ቆይታቸዉ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ፣ ለታታሪ ሠራተተኞች፣ ኮሌጁ በሚሰጠው የትብብርና የኩባንያ ውስጥ ስልጠና በራቸውን ክፍት በማድረግ በቅርበት በመሥራት ሁለንትናዊና ቀና ትብብር ላዳረጉ አጋር ድርጅቶችና አካላት የሰርትፍኬት፣ ሜዳልያና የዋንጫ ሽልማት ተሰጥቶ ፕሮግራሙ ተፈፅሟል፡፡

ዘጋቢ፦ አማኑኤል እንድሪስ
የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ባለሙያ
ሐምሌ 26፣ 2018

30/07/2026
29/07/2026

የ2026 | የ2018 ዓ.ም. የምረቃ ሥነ ሥርዓት

ኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም. የምረቃ ሥነ ሥርዓት እሁድ፣ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. (Sunday, 1 August 2026) እንደሚካሄድ በደስታ ያስታውቃል።

በዚህ የደስታ ቀን ከተመራቂዎቻችን ጋር በመሆን ስኬታቸውን እንዲያከብሩ ወላጆችን፣ ቤተሰቦችን፣ የኮሌጁ ምሩቃንን፣ የኢንዱስትሪ አጋሮችን፣ ባለድርሻ አካላትን እና መላውን ማኅበረሰብ በክብር እንጋብዛለን።

ለሁሉም ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ! በቀጣይ ሕይወታችሁ የላቀ ስኬት እንመኛለን።

የኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ቡድን

GRADUATION CEREMONY 2026 | የ2018 ዓ.ም. የምረቃ ሥነ ሥርዓትKombolcha Polytechnic College is pleased to announce that its 2026 Gra...
29/07/2026

GRADUATION CEREMONY 2026 | የ2018 ዓ.ም. የምረቃ ሥነ ሥርዓት

Kombolcha Polytechnic College is pleased to announce that its 2026 Graduation Ceremony will take place on Sunday, 2 August 2026.

We warmly invite parents, families, alumni, industry partners, stakeholders, and the public to join us in celebrating the achievements of our graduates.

Congratulations to the Class of 2026! We wish you every success in your future careers.

Kombolcha Polytechnic College Public Relations and Communication Team

Address

Kombolcha
Kombolcha

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:30
Tuesday 08:00 - 17:30
Wednesday 08:00 - 17:30
Thursday 08:00 - 17:30
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Telephone

+251335512510

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kombolcha Polytechnic College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share