24/08/2026
በንብ ማነብና የግብርና ግብአት አቅርቦት ላይ ለተሰማሩ 89 ወጣቶች ሲሰጥ የነበረው አጫጭር ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ......................................
በንብ ማነብና የግብርና ግብአት አቅርቦት ላይ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በኮምቦልቻ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅና ማያ ፕሮግራም (MaYEA Program) የጋራ ትብብር ሲስጥ የሰነበተዉ የአጫጭር ስልጠና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
መጣቶቹ ማያ ፕሮግራም (Mass Youth Employment in Apiculture- MaYEA Program) በተሰኘ ድርጅት ተመልምለው የመጡ ሲሆን በግብርና ዘርፍ ብቃታቸው በተረጋገጠ የኮሌጁ መምህራን ስልጠናውን ወስደዋል። በግብርና ግብአት አቅርቦት ላይ ለተሰማሩ 48 ሰልጣኞች የንግድ ስራ ክህሎት ስልጠና እንዲሁም ለ41 ሰልጣኞች ደግሞ በንብ ማነብና ለንብ ማነብ ስራ በሚሆኑ ግባቶች ማምረት እና መሸጥ ላይ ስልጠናው ተሰጥቷል።
ስልጠናው የተሰጠው ከቃሉ፣ ዳዋ ጨፋ፣ ከባቲ፣ ጭፍራ፣ ከሚሴ፣ አርጎባና ወረባቦ ወረዳዎች ለተውጣጡ 89 ወጣቶች ሲሆን ዓላማውም ስልጣኞቹ የንግድ አስተዳደር ክህሎትን እንዲያደብሩ፣ የንግድ ምርታማነትና የገበያ ጥናት መንገዶችን እንዲረዱ፣ በንግድ ህጎች ላይ ግንዛቤ እንዳዳብሩ፣ በግብርና ስራ ላይ ለተሰማሩ የግብርና ግብአቶችን ማቅረብ፣ ንብ ለሚያንቡ ኢንተርፕራዞች የንብ ግብአትና መሳሪያዎችን ማቅረብ እንዲችሉና የመረጃ ልውውጥና የግንኙነት መረባቸውን ማሳደግ የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው።
በንግድ ስራ ክህሎት ላይ ያተኮረዉን ስልጠና የሰጡት የአግሮፕሮሰሲንግ ሊቁ አቶ ሙሃመድ በላይና የሆርቲካልቸር ምሁሩ አቶ ታደሰ ያሲን ሲሆኑ በንብ ማነብና ግብአት አቅርቦት ላይ ደግሞ በእንሰሳት ሀብት የሙያ ባለቤት የሆኑት አቶ ዋሲሁን መኮነን አስልጥነዋል።
በህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ቡድን
ነሀሴ 17፣ 2018