Wollo University Kiot Ict Club

Wollo University Kiot Ict Club wollo university kombolcha institute of technology ICT CLUB

11/07/2025

የሐዘን መግለጫ

በዩኒቨርሲቲያችን የሂውማኒቲስ ፋኩልቲ በእንግሊዘኛ ቋንቋና ስነ-ጽሑፍ ት/ክፍል በመምህርነትና በተመራማሪነት ሲያገለግሉ የነበሩት ዶ/ር ደረጀ ነገደ ባጋጠማቸው ድንገተኛ የጤና እክል ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ለህክምና ቢገቡም ሊሻላቸው ባለመቻሉ ዛሬ ሃምሌ 04/2017 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ዶ/ር ደረጀ ነገደ የዩኒቨርሲቲያችን አንጋፋ መምህርና ተመራማሪ፣ በባልደረቦቻቸውና በተማሪዎቻቸው የሚወደዱና የሚከበሩ አንጋፋ መምህራችን የነበሩ ሲሆን ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም በማረፋቸው ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እጅግ አዝኗል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለባልደረቦቹ ልባዊ መጽናናትን እየተመኘ ፈጣሪ አንጋፋ መምህርና ተመራማሪያችን የነበሩትን ዶ/ር ደረጀ ነገደ ነፍስ በአፀደ ገነት እንዲያሳርፍልን ልባዊ ምኞታችንን እንገልጻለን!

ነፍስ ይማር!
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
ሃምሌ 04/2017 ዓ/ም

Office Boy Job in Canada👉  Salary: CA$1,400.00 - CA$1,650.00 / Monthly👉  Experience: Fresh👉  Gender: Both👉  Career level...
26/02/2022

Office Boy Job in Canada
👉 Salary: CA$1,400.00 - CA$1,650.00 / Monthly
👉 Experience: Fresh
👉 Gender: Both
👉 Career level: Office Boy
👉 Qualification: Any Degree
👉 Number of Vacancy: 215
👉 Relocation: Yes
👉 VISA : Provided by the company
👉 Accommodation : Provided by the company
👉 Transportation : Provided by the company
Contact
Other vacancy

10/04/2020

ለኮሮና በሽታ ታማሚዎች የሚሰጠው ህክምና ምንድነው ?
====================================

1) የህክምናው ዓላማ
----------------
የኮሮና ቫይረስ በህዋሳት ላይ የሚያደርሰውን ቀጥተኛ ጉዳት ለማስቆም የሚያስችል ፍቱን መድሃኒት ባለመኖሩ የህክምና ድጋፉ ዋና አላማ ለተፈጠረው የጤና ችግር የሕክምና ድጋፍ በማድረግ የጎንዮሽ ጉዳትንና የህመም ስቃይን በመቀነስ ቶሎ እንዲያገግሙ ማገዝ ነው::

2) የህክምና ድጋፍ አይነቶች
---------------------
እንደ ህመሙ ክብደትና ተጓዳኝ ችግሮች የሚለያይ ቢሆንም በህክምና መስጫ ተቋማት የሚደረጉ ዋና ዋና የህክምና ድጋፍ አይነቶች የሚከተሉት ናቸው፡-

1. በቂ እረፍት እንዲያደርጉ ማስቻል፣
2. ህመምና ትኩሳት የሚቀንሱ መድሃኒቶች መስጠት፣
3. ለህክምና አገልግሎት የሚውል ኦክስጅን (Medical Oxygen) መስጠት፣
4. ሰውነት በቂ ፈሳሽ፣ ምግብና ንጥረ ነገር እንዲኖረው ማድረግ፣
5. በፅኑ ለታመሙና በራሳቸው መተንፈስ ለማይችሉ በመሳሪያ (Mechanical Ventilator) ታግዘው እንዲተነፍሱ ማስቻል፣
6. በባክቴሪያዎች አማክኝነት የተከሰተ ተደራቢ የሳንባ ምች፣ የደም መመርቀዝ ላለባቸው ተገቢውን ፀረ-ባክቴሪያ መድሃኒት/መድሃኒቶች (antibiotics) መስጠት፣
7. በፅኑ ለታመሙና በከፍተኛ ደረጃ ስራቸውን መስራት ለማይችሉ የዉስጥ ክፍለ አካላት (ለምሳሌ ኩላሊት፣ ወዘተ) ችግር፣ ተገቢውን የህክምና ድጋፍ ማድረግ፣
8. ሌላ ተጨማሪ የጤና ችግር (የደም ግፊት፣ የስኳር ህመም፣ አስም፣ ወዘተ) ካለ ተገቢውን ህክምና ማድረግ፣
9. በሐኪሞች ምክር ሙከራ/ጥናት ላይ ያሉ ለሌላ በሽታ ተብለው የተሰሩ ፀረ-ቫይረስነት ባህሪ ያላቸውን ተስፋ ሰጪ መድሃኒቶች (ለምሳሌ ክሎሮኩዊን (Chloroquine/ hydroxychloroquine) ከባድ ህመም ላለባቸው ታማሚዎች መስጠት::

3) ማጠቃለያ
-----------
በኮሮና በሽታ የተያዘ ሰው ተገቢውን የህክምና ድጋፍና እንክብካቤ ለማግኘት ለዚህ አላማ ተብለው ወደ ተዘጋጁ የህክምና ተቋማት መሄድ ይኖርበታል:: የሚደረገው የህክምና ድጋፍና እንክብካቤም በሽታው የሚያመጣውን ጉዳት ለመቀነስና ታማማዊ ቶሎ እንዲያገግም በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው:: ተገቢውን የህክምና ድጋፍ አለማግኘት ከፍተኛ የህመም ስቃይ ከማስከተሉም ባሻገር ሳምባና ኩላሊት ስራቸውን እንዲያቆሙ በማድረግ ለሞት ሊዳርግ ይችላል::

የህክምና ድጋፉ ታማሚዎች ከኮሮና በሽታ እንዲድኑ ከማገዙም በላይ ከበድ ያለ ህመም የገጠማቸው ታማሚዎች ላይ ሊከሰት የሚችለውን ዘላቂ የጤና ችግር (ለምሳሌ በሳንባ ጠባሳ ምክንያት የሚመጣ ዘላቂ የአተነፋፈስ ችግር፣ የኩላሊት ድክመት፣ ወዘተ) ለመቀነስ ጉልህ ድርሻ አለው።

ስለሆነም የኮሮና በሽታ ምልክቶች የታየበት ማንኛውም ሰው እራሱን/እራሷን በቤት ዉስጥ ለይቶ ከማቆየት ባሻገር ወደ ጤና ተቋም በመሄድ በጤና ባለሙያዎች በሚሰጠው የውሳኔ ሃሳብ መሰረት ተገቢውን የኮሮና ምርመራ በማድረግ ለዚህ አላማ ተብለው በተዘጋጁ የለይቶ ማከሚያ ክፍሎች ገብቶ ሕክምና ማድረግ የግድ ይላል:: ኮሮናን ለመከላከልና ስርጭቱን ለመቆጣጠርም አንዱና ወሳኙ መንገድ ነውና::

4) ትኩረት !
--------
· እጃችንን በሳሙና ደጋግመን እንታጠብ

· አካላዊ ርቀትን እንጠብቅ

· በተቻለ መጠን ከቤት አንዉጣ

· ሰባዊነትን በማስቀደም እንተሳሰብ፤ እንረዳዳ

· ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን እናጠናክር

· በመንግስትና በሃይማኖት ተቋማት የሚተላለፉ ምክሮችንና
ዉሳኔዎችን እንተግብር

· ጤና ተቋማትን እንደግፍ

· ፈጣሪ በምህረቱ እንዲጎበኘን እንፀልይ
====================
በፕሮፌሰር የሺጌታ ገላው
ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ

የኮሮናቫይረስ መረጃዎቹን በቴሌግራም ማቅረብ ጀምረናል ይቀላቀሉን
👉 https://t.me/covid_ethiopia
👉 https://t.me/covid_ethiopia

19/12/2019
08/11/2013

WELL-COME TO WOLLO UNIVERSITY KIOT INFORMATICS COLLEGE IS,IT,CS STUDENT ....

Address

Wollo University
Kombolcha

Telephone

+251927422032

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo University Kiot Ict Club posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Wollo University Kiot Ict Club:

Shortcuts

Share

Category