Injibara Poly Technic College

Injibara Poly Technic College "የሚሰሩ እጆች፤ የሚፈጥሩ አዕምሮዎች"

INJIBARA POLY TECHNIC COLLEGE aims to deliver formal, informal and non formal education and training to those who need to acquire a required knowledge and skill according to the need assessment study of the industry. Besides this, this college is giving industry extension service for micro and small enterprises specially for those manufacturing enterprises through technology transfer capability.

24/08/2026
21/08/2026
የእንጅባራ ፖሊ ክላስተር ኮሌጆችየ2018 በጀት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ተካሄደ እንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅህዝብ ግንኘነትና ኮሚኒኬሽን     ነሀሴ 04/ 2018 ዓ...
10/08/2026

የእንጅባራ ፖሊ ክላስተር ኮሌጆች
የ2018 በጀት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ተካሄደ

እንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኘነትና ኮሚኒኬሽን
ነሀሴ 04/ 2018 ዓ.ም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

እንጅባራ ነሐሴ 2018 ዓ.ም የእንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ክላስተር ኮሌጆች የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በማስተዋወቅ የመወያየት መድረክ አካሂደዋል።

በመድረኩ የክላስተሩ ኮሌጆች በ2019 በጀት ዓመት ለማሳካት ያቀዷቸውን ዋና ዋና ተግባራት፣ የአፈጻጸም አቅጣጫዎችና የሚጠበቁ ውጤቶች በዝርዝር ቀርበዋል።

የዕቅድ ትውውቁ ዋና ዓላማ በክላስተሩ ውስጥ ያሉ ኮሌጆች በጋራ አቅጣጫ እንዲመሩ፣ የሚከናወኑ ተግባራትን በቅንጅት እንዲፈጽሙ እና የትብብር ስልጠና የኤግዚቢሽን፣ የጥነትና ምርምር፣ የቴክኖሎጂ ና ክህሎት ውድድር በተመለከተ በሰፊው ውይይት ተደርጎበታል።

በተለይም የሰልጣኞች ቅባለ ቁጥር መሻሻል፣ የስልጠና ጥራትን ማረጋገጥ፣ የኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር፣ የሰልጣኞችን ተቀጣሪነት ፣ የሰው ኃይልና የተቋም አቅምን ማሳደግ እንዲሁም የተቋማትን የስራ አፈጻጸም በተሻለ ደረጃ ማስመዝገብ በዕቅዶቹ ውስጥ ከተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።

ተሳታፊዎችም ዕቅዱ በተግባርና በተቀናጀ መልኩ መስራት፣ የክትትልና የግምገማ ሥርዓትን ማጠናከር እና በኮሌጆች መካከል ያለውን የልምድ ልውውጥ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም የአዊ ብሔረሰብ /አሰ ስራና ክህሎት መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ስንታየሁ መንግስቱ የእንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ክላስተር ኮሌጆች በ2018 በጀት ዓመት የነበሩ ጥንካሬዎች በማስቀጠል የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዳቸውን በተግባር በማከናወን የተሻለ የስራ አፈጻጸምና ውጤት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

"የሚሰሩ እጆች ፤የሚፈጥሩ አዕምሮዎች''

እንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

10/08/2026
የክረምት የበጎ ፈቃድ ስራዎች የሚውል የደብተር እስክሪብቶ እና አልባሳት ድጋፍ ተደረገ።እንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን    ነሀሴ 01/ 2018 ዓ.ም
07/08/2026

የክረምት የበጎ ፈቃድ ስራዎች የሚውል የደብተር እስክሪብቶ እና አልባሳት ድጋፍ ተደረገ።

እንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

ህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን

ነሀሴ 01/ 2018 ዓ.ም

በ2019 በጀት ዓመት በትምህርት ጥራት ስራ ዓመራር ስርዓት ትግበራ መሻሻል በሚገባቸው ዝርዝር ሀሳቦች ላይ የኮሌጁ ሁሉም የአደረጃጀት መሪዎች በተገኙበት ውይይት ተካሄደ።በውይይቱ በ2019 በ...
06/08/2026

በ2019 በጀት ዓመት በትምህርት ጥራት ስራ ዓመራር ስርዓት ትግበራ መሻሻል በሚገባቸው ዝርዝር ሀሳቦች ላይ የኮሌጁ ሁሉም የአደረጃጀት መሪዎች በተገኙበት ውይይት ተካሄደ።

በውይይቱ በ2019 በጀት ዓመት መከናወን በሚገባቸው ክፍተቶችና ስጋቶች እንዲሁም መሟላት ባለባቸው ጉዳዮች በዝግጅት ምዕራፍ እንዲከናወኑ ማሳሰቢያዎች ተሰጥተዋል።

"የሚሰሩ እጆች፤ የሚፈጥሩ አዕምሮዎች"

እንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን
ሐምሌ 30/ 2018 ዓ.ም

31/07/2026

የትብብር ስልጠና ፎርም ምስረታ በአማራ ክልል‼️የክህሎት ልማት መሰረት

Address

Amhara Region Awi Nationality Administration
Injibara
PHONE:0582271212

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Injibara Poly Technic College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Injibara Poly Technic College:

Shortcuts

Share

Category