Muday College

Muday College Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Muday College, Education, Injibara.

Muday College provides high-quality short & long-term professional training, research, and community services at reasonable prices.

🎓 Motto: 'Learn Today for a Better Tomorrow!'

09/07/2026


የሚከተሉትን መስፈርቶች ስታሟሉ ባላችሁበት በ neta.gov.et በመግባት ወረፋ በማስያዝ እንግልት መቀነስ ትችላላችሁ። ቀጠሮው ሲደርስ ባካል ወይም ህጋዊ ውክልና በሰጣችሁት ሰው አማካኝነት ማስጨረስ ይቻላል።

ዝርዝር መስፈርቶች
ከሀገር ውስጥ የተገኙ የትምህርት ማስረጃዎችን ለማረጋገጥ መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች

⚠ የአገልግሎት ክፍያ መጨረሻ ላይ በሚሠጠው የክፍያ አድራሻ (link) በቴሌ ብር (telebirr) ወይም በሲቢኢ ብር (CBE-Birr) አማራጮች ብቻ ይክፈሉ።

(1) በጀርባው ላይ የኮሌጁ ኃላፊና ሬጅስትራር ፊርማና ማህተም ያለበት ኦሪጅናል ዲግሪ፤

(2) በጀርባው ላይ የኮሌጁ ኃላፊና ሬጅስትራር ፊርማና ማህተም ያለበት ኦሪጅናል ትራንስክሪፕት/Student Copy/፤

(3) ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘ ኦሪጅናል ዲፕሎማ ወይም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት፤

(4) ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘው የ12ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት ከሆነ በሀገር አቀፍ የት/ት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ ፤

(5) ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘው ዲፕሎማ ከሆነ ዲፕሎማው በተገኘበት ክልል የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ወይም የዞን/የከተማ መስተዳደር የሥራና ስልጠና ቢሮ ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ እንዲሁም የደረጃ 4 ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት (COC)

(6) የዲግሪ መግቢያው ከውጭ በተገኘ የትምህርት ማስረጃ ከሆነ ከባለስልጣኑ የተገኘ የአቻ ግመታ ደብዳቤ

(7) የማስተርስ ይግሪን ለማረጋገጥ ከሆነ ደግሞ ቅድሚያ የመጀመሪያው ዲግሪ ከላይ በተገለፀው መንገድ መረጋገጥ አለበት፡፡

(8) የስም ለውጥ ካለ የፍርድ ቤት ውሳኔ የተላፈበት ማስረጃ፤

⚠ ከላይ የተጠቀሱትን አስፈላጊ የሆኑ ማስረጃዎች ከፊት እና ከሆላ ስካን (Scan) በማድረግ በ neta.gov.et ማመልከት ይችላሉ

ቀጠሮ ቀን በኢሜል/SMS/ ሲደርሶት፤ በአካል ሲመጡ በባለጉዳዩ ወይም ሕጋዊ የውክልና ሰነድ ባላቸው ተወካዮች ሁሉንም የትምህርት ማስረጃ ዋናውን ይዘው መቅረብ አለባቸው።

ለበለጠ መረጃ:

ነጻ የስልክ ጥሪ ማዕከል: 9799 በስ.ቁ: (+251) 111 23 22 30 ወይም (+251) 111 23 61 30
=======
ወቅታዊ መረጃዎች እንዲደርስዎ ቴሌግራም ገፃችንን https://t.me/mudaycollege ይቀላቀሉ።

 #ለተመራቂዎችበ0 አመት እናት ባንክ አዲስ የስራ ማስታወቂያ♦Deadline: July 14, 2026Enat Bank S.C invites fresh Graduates for the following va...
09/07/2026

#ለተመራቂዎች
በ0 አመት እናት ባንክ አዲስ የስራ ማስታወቂያ

♦Deadline: July 14, 2026

Enat Bank S.C invites fresh Graduates for the following vacant positions.

✅ Position 1: Junior Customer Service Specialist

• Salary & Benefits: As per the Bank’s Salary Scale & Benefits Package

How to Apply Online??
👇👇👇
https://effoysira.com/enat-bank-job-vacancy-fresh-graduates-2026/
:
❗️Telegram:- https://t.me/effoyjobs

Latest Job From Banking Jobs, Enat Bank, Fresh Graduates Jobs

09/07/2026


በዲግሪ መርሃግብር የመውጫ ፈተና በሰኔ 2018 ለተፈተናችሁ እና በዲፕሎማ መርሃግብር ትምህርታችሁን ያጠናቀቃችሁ የኮሌጃችን ተማሪዎች የትምህርት ማስረጃችሁ ተዘጋጅቶ ያለቀና መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

  !ባለሥልጣኑ በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990/2016 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 5 ላይ ብቻ ሀ፣ለ እና ሐ ተብሎ ተጨምሮ በተዘጋጀው ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ከሰኔ 29...
09/07/2026


!
ባለሥልጣኑ በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990/2016 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 5 ላይ ብቻ ሀ፣ለ እና ሐ ተብሎ ተጨምሮ በተዘጋጀው ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ በታች በተቀመጡት አማራጮች አስተያየታችሁን መስጠት የምትችሉ መሆኑን በባለስልጣኑ ቴሌግራም ገፅ በለቀቀው መረጃ ማስታወቂያ ገልጿል፡፡
✔️https://forms.gle/ndRhodE2yoHSn2P5A ሊንኩን ወይም ማስፈንጠሪያውን በመጫን አስተያየት መስጫውን ማግኘት ትችላላችሁ፤ ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ አስተያየታችሁን ሞልታችሁ ስትጨርሱ (submit) የሚለውን በመጫን አስተያየታችሁን መላክ የምትችሉ መሆኑን ተጠቅሷል።
✔️ማሻሻያ የተደረገበትን ረቂቅ አዋጅ በባለሥልጣኑ በዌብሳይት www.neta.gov.et የምታገኙ ይሆናል፡፡
✔️ለሚኖራችሁ ማንኛውም አስተያየት በባለሥልጣኑ ኢ-ሚይል አድራሻ [email protected] ላይ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ መላክ የምትችሉ መሆኑንም ገልጿል።
✔️በአካል ቀርባችሁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን መስጠት ለምትፈልጉ የፊት ለፊት (የገጽ ለገጽ) የመወያያ መድረክ ስለምናዘጋጅ በቀጣይ ቀኑን ፣ሰዓቱን እና ቦታውን የሚያሳውቁ መሆኑን አሳስበዋል።
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

ይህ ቅጽ የተዘጋጀው የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ ማሻሻያ ላይ አስተያየት እንዲሰጥበት ነው።እባክዎን የመመሪያውን ማሻሻያ በጥንቃቄ በማንበብ አስተያየቶችዎ.....

 ።ሙዳይ ኮሌጅ የመማር-ማስተማር ሂደቱን ይበልጥ ዘመናዊ እና ተደራሽ ለማድረግ በትግበራ ላይ ያዋላቸውን የኢ-ለርኒንግ (E-learning) እና የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት መድረኮችን በይፋ አስተ...
07/07/2026



ሙዳይ ኮሌጅ የመማር-ማስተማር ሂደቱን ይበልጥ ዘመናዊ እና ተደራሽ ለማድረግ በትግበራ ላይ ያዋላቸውን የኢ-ለርኒንግ (E-learning) እና የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት መድረኮችን በይፋ አስተዋወቀ።

ሰኔ 28/2018 ዓ.ም በተካሄደው በዚህ ልዩ የማስተዋወቂያ መርሃ-ግብር ላይ፣ በመምህር መሰለ ሞሴ አማካኝነት የዲጂታል መሰረተ-ልማቶቹ ምንነት፣ መገለጫዎች እና ለተማሪዎች የሚሰጡት ዘርፈ-ብዙ ጥቅሞች በተግባራዊ ማሳያ (Demonstration) የታገዘ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

በዕለቱም የተማሪ ወላጆች፣ ተመራቂ ተማሪዎች እና የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ክቡራን እንግዶች ተገኝተው የኮሌጁን የቴክኖሎጂ ሽግግር በአካል ተመልክተዋል። ኮሌጁ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ለማድረስ የሚደረገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተገልጿል።


በቴሌግራም በታች ባለው ሊንክ ያገኙናል።
https://t.me/mudaycollege

06/07/2026
Congratulations to Dean Anteneh F. on the successful completion of the 4th round graduation ceremony!
06/07/2026

Congratulations to Dean Anteneh F. on the successful completion of the 4th round graduation ceremony!

 +_ዳቦ_ቆረሳ
06/07/2026

+_ዳቦ_ቆረሳ

05/07/2026

 !ሙዳይ ኮሌጅ  የ4ኛ ዙር  ተመራቂዎችን÷ የክብር እንግዳው የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ስራና ክህሎት መምሪያ  ም/ሃላፊ አቶ ስንታየሁ መንግስቱ÷ የተማሪ ወላጆች÷ የአካባቢ ሽማግሌዎች÷...
05/07/2026

!

ሙዳይ ኮሌጅ የ4ኛ ዙር ተመራቂዎችን÷ የክብር እንግዳው የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ስራና ክህሎት መምሪያ ም/ሃላፊ አቶ ስንታየሁ መንግስቱ÷ የተማሪ ወላጆች÷ የአካባቢ ሽማግሌዎች÷ የኮሌጁ ስራ ሃላፊዎች÷ መምህራንና ሰራተኞች በተገኙበት በዛሬው እለት በ28/10/2018 ዓ/ም በደማቅ ሁኔታ አሰመርቋል።

በምረቃ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክብር እንግዳው አቶ ስንታየሁ መንግስቱ÷ ምሩቃን ለሀገራችን የሰላም ሁኔታ የበኩላቸውን እንዲወጡ: መንግስት በሚያመቻቸው የብድርና መሬት አቅርቦት ተጠቅመው ስራ ፈጠሪ እንዲሆኑና ሌሎችንም በዙሪያቸው አሰባስበው በትብብር መንፈስ ራስን ከመቻል አልፈው ለሌላው እንዲተርፉ የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። በተጨማሪም የኮሌጁን ኢለርኒግ (ዲጅታል ትምህርት) እና ዲጅታል ቤተመፃህፍት በማድነቅ ምሩቃን ከኮሌጁ ያገኙትን ትምህርትና ስልጠና በመጠቀም ለሀገራችን ዲጂታል ኢኮኖሚ ራዕይ እውን መሆን የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። በማጠቃለያቸውም ምሩቃን በዚህ የታወቀና አንጋፋ መምህራን በሚገኙበት ኮሌጅ ተምረው ያገኙት የምረቃ ሰርተፊኬት በኩራት የሚያሳዩት እንደሆነ ገልፀዋል።

የኮሌጁ ስራ አስፈፃሚ ረ/ፕ ጌታነህ የኔዓለም ተቋሙ አማራጭ ሳይሆን ተመራጭ ተቋም ለመሆን ትምህርት ጥራት ላይ እና የዲጅታል ፕላትፎርሞችን እያስፋፋ እንደሚገኝ እና ምሩቃንም የኮሌጁ አምባሳደሮች እንዲሆኑ አሳስበው ለእንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በተያያዘም የኮሌጁ ዲን አቶ አንተነህ ፈቃድ በተቋሙ ቆይታችሁ ባገኙት ስልጠና ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑና ማህበረሰባችንን በቅንነትና ታታሪነት እንዲያገለግሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በስተመጨረሻም የ4ኛ ዙር ተመራቂዎች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ምሩቃን የሰርተፊኬትና ሜዳሊያ ሽልማት ከክብር እንግዳው በመቀበል የምረቃ መርሃግሩ ተጠናቋል።

Address

Injibara

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Muday College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share