Injibara University

Injibara University Explore your Creative Potentials Explore your creative potentials
(1)

ማስታወቂያለድህረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና  (NGAT EXAM) ተፈታኞች በሙሉ፦====================================በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የ...
24/08/2026

ማስታወቂያ
ለድህረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (NGAT EXAM) ተፈታኞች በሙሉ፦
====================================
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (NGAT EXAM) ለመፈተን የተመዘገባችሁ አመልካቾች ከዚህ በታች በተገለፀላችሁ የፈተና ፕሮግራምና የስም ዝርዝር መሰረት የመግቢያ ትኬት (Entrance ticket) ከግል አካውንታችሁ አውርዳችሁ በመያዝ ከተጠቀሰው ሰዓት ቀድማችሁ በየመፈተኛ ክፍሎች በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን።

ማሳሰቢያ፦ ዝርዝሩን በደንብ ለማየት በቴሌግራም ሊንክ = https://t.me/injiuniversity ገብታችሁ Pdf ላይ ማግኘት ትችላላችሁ።

24/08/2026
ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት!======================================ነሀሴ 17/2018 ዓ/ም እንጅባራ ዩኒቨርሲቲበ2018 የትምህርት ዘመ...
23/08/2026

ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት!
======================================
ነሀሴ 17/2018 ዓ/ም እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 12 ነጥብ 8 በመቶ ወይም 70 ሺህ 544 ተማሪዎች የማለፊያ ወጤት ማስመዝገባቸው የትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወቃል።

በትምህርት ጥራት፣ በአረንጓዴነቱ፣ በውብ እና ማራኪ ግቢው የሚታወቀው ስመ-ጥሩ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወደ ከፍተኛ ትምህርት የማለፊያ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ሲያስተላልፍ ኩራት ይሰማዋል።

እንጅባራ ዩንቨርስቲ የ2ኛ ደረጃ የተማሪዎችን ውጤታማ ለማድረግ በSTEM የበጋ እና የክረምት መርሀግብር ስልጠናዎችን ሲሰጥ የቆዬ ሲሆን እስካሁን ከአዊ ዞን ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ 398 ወንድና 295 ሴት በድምሩ ለ693 ተማሪዎች የSTEM ስልጠና ሰጥቷል።

በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በተፈጥሮ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተማሪ ህዳሴ ዘመኑ በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር በእንጅባራ ከተማ ከሚገኘው ከአገው ምድር ከ/2ኛ ደ/ት/ቤት 583 በማምጣት በተፈጥሮ ሳይንስ 2ኛ እና ከአጠቃላይ ሴቶች አንደኛ በመሆን ታሪክ አስመዝግባለች።

ተማሪ ህዳሴ ዘመኑ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ከ8ኛ ክፍል እስከ 11ኛ ክፍል በእንጅባራ ዩንቨርሲቲ የSTEM ማዕከል በየአመቱ የሚሰጠውን የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምህንድስናና የሂሳብ ስልጠናዎችን በመውሰድ በስኬት ያጠናቀቀች ባለራዕይ ተማሪ ናት።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ህዳሴ ለተማረችበት የአገው ምድር ከ/2ኛ ደ/ት/ቤት ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በማድረግ ደረጃውን የጠበቀ የሳይንስ ላቦራቶሪ ያቋቋመ ሲሆን በት/ቤቱ ለሚገኘው በተማሪ ህዳሴ ዘመኑ ስም ለተሰየመው ህዳሴ ቤተመጻሕፍት አራት መቶ ወንበርና ጠረጴዛ እንዲሁም ሙሉ የመፅሐፍት መደርደሪያ ሼልፍ በመስጠት ለተማሪዎች አገልግሎት እንዲውል ማድርጉን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ እና በምርምር እና ማ/አ ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ዶ/ር ክንዴ ብርሃን ገልጸዋል።

የእንጅባራ ዩንቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) በቀጣይም እንደተማሪ ህዳሴ ዘመኑ አይነት ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በአካባቢው ከሚገኙ ከ/2ኛ ደ/ት/ቤቶች ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ አስታውቀው ለተማሪ ህዳሴ ዘመኑና ቤተሰቦቿ እንዲሁም ለመላው የአገው ምድር ከ/2ኛ ደ/ት/ቤት መምህራንና ሰራተኞች እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ አክለውም ተማሪ ህዳሴ ዘመኑ የ12ኛ መልቀቂያ ፈተናን በእንጅባራ ዩንቨርስቲ የፈተና ማዕከል መፈተኗን አስታውሰው፣ ተማሪ ህዳሴ ዘመኑ የተሻለ የከፍተኛ ትምህርት እድል እንዲመቻችላት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

የአገው ምድር ከ/2ኛ ደ/ት/ቤት ርዕሰ መምህር አቶ አዲሱ አየለ በተማሪ ህዳሴ ዘመኑ ውጤት መላው የት/ቤቱ ማህበረሰብ ከፍተኛ ኩራት እንደተሰማው በመግለፅ እንጅባራ ዩንቨርሲቲ ዘመናዊ የሳይንስ ላብራቶሪና ቤተመፅሐፍት በማደራጀት ካደረገላቸው ድጋፍ በተጨማሪ ለመምህራን የሙያ ማሻሻያ ስልጠናዎችን በመስጠት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችም በSTEM መርሃግብር ተግባር ተኮር ስልጠና በመስጠት ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን በመግለፅ ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡትን ተማሪዎች በሙሉ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እያለ ዩኒቨርሲቲው አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቱን ያጠናቀቀ መሆኑን እየገለጸ ለመማር ማስተማር ምቹ፣ ፍጹም ሠላማዊ፣ አረንጓዴ፣ ውብ እና ማራኪ የሆነውን እንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ቀዳሚ ምርጫችሁ እንድታደርጉ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
እንጅባራ ዩንቨርሲቲ!

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ===============
22/08/2026

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
===============

ለድኅረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተፈታኞች ተቶሪያል ተሰጠ፡፡================================================== ነሀሴ 15/2018 ዓ.ም፤ እንጅ...
21/08/2026

ለድኅረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተፈታኞች ተቶሪያል ተሰጠ፡፡

==================================================



ነሀሴ 15/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ



በ2018 ዓ.ም የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች ከነሀሴ 12-15/2018 ዓ.ም ቲቶሪያል ተሰጥቷል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ዳይሬከቶሬት ዳይሬክተር እሱባለው ስንቴ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በዩኒቨርሲቲው ከ230 በላይ የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የምግቢያ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞች በዩኒቨርሲቲው መምህራን አማካኝነት ቶቶሪያል መሰጠቱን ገልጸው የቲቶሪያል ፕሮግራሙ በእንግሊዝኛ፣ ሂሳብ እና ስታስቲክስ ላይ ያተኮረ እንደነበር ገልጸዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አያይዘውም ነሃሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም ለሚሰጠው የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (NGAT) ከ1ሺህ 135 በላይ ተፈታኞች በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመፈተን መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡



ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

21/08/2026
17/08/2026
ማስታወቂያለ"NGAT" ተፈታኞች በሙሉ፦የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የፈተና ቀን ነሃሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን የፈተናዎች ኤጀንሲ አሳውቋል።ሥለሆነም...
16/08/2026

ማስታወቂያ

ለ"NGAT" ተፈታኞች በሙሉ፦

የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የፈተና ቀን ነሃሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን የፈተናዎች ኤጀንሲ አሳውቋል።

ሥለሆነም እንጅባራ ዩኒቨርሲቲን የፈተና ማዕከል በማድረግ የተመዘገባችሁ ተፈታኞች ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ በተጠቀሰው ቀን በሚወጣው ፕሮግራም መሰረት User Name and Pass Word ይዛችሁ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ድረስ በመምጣት ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ፦ የፕሮግራም ለውጥ ካለ ወደፊት በማስታወቂያ የሚገለፅ ይሆናል።

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ  የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት  መዘራት ተጀመረ።==========================ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲበእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግቢ  ውስጥ የ2...
10/08/2026

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት መዘራት ተጀመረ።
==========================

ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የ2018/19 የመኸር እርሻ የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት መዘራት ተጀምሯል።

በዘር ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊና የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲዉ ከሚሰጣቸው የማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች አንዱ ለምግብነትና ለዘር ብዜት አገልግሎት የሚውል የዳቦ ስንዴ ምርት አምርቶ ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ እንደሆነ ገልፀው በዘንድሮ የ2018/19 የመኸር እርሻ ሰብልም ደንደኣ እና ሰከላ የተባሉ ሁለት አይነት የስንዴ ምርጥ ዘር ዝርያዎችን በግቢ ውስጥ በሚገኘው 20 ሄክታር የእርሻ መሬት ላይ ዘር የመዝራት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ኮሌጅ ዲን የሆኑት ሀብታሙ አድማስ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የስንዴ ምርጥ ዘር መዘራት ከጀመረ ሁለት ሶስት አመታትን ያስቆጠረ መሆኑን አስታውሰው በዘንድሮው የመኸር የስንዴ ዘር የማስጀመር መርሃ ግብር ዩኒቨርሲቲው በግቢው ወስጥ ከግንባታ ሳይት ነፃ የሆኑ የእርሻ መሬቶችን በሳይንሳዊ የአጠቃቀም ዘዴ የአፈር አሲዲማነትን መቋቋም የሚችሉ የስንዴ ዝርያዎችን በ20 ሄክታር መሬት ላይ በመዘራትና ምርምሮችን በማካሄድ በሚቀጥለው ዓመት የተሻለ ምርት አምርቶ ለአርሶ-አደሩ ለማሰራጨት ሰፊ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የዩኒቨርሲቲው የስንዴና ገብስ ምርጥ ዘር ብዜት ተመራማሪና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ የሆኑት አቸነፍ ጥጋቡ (ዶ/ር ) እንደገለፁት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ባለፈ በርካታ ሀላፊነቶችን እየተወጣ የሚገኝ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው በ2018/19 የምርት ዘመን የተሻሉ ግብዓቶችን ተጠቅሞ ልዩ ልዩ ምርምሮችን በማካሄድ ጥራቱን የጠበቀ በቂ የዳቦ ስንዴ ምርጥ ዘር አምርቶ ለአርሶ-አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ ለማድረግ ፕሮጀክቱ ትኩረት አድርጎ አየሰራ ነው ብለዋል።
ፕሮግራሙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የግብርና ኮሌጅ ተመራማሪዎችና የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች በተገኙበት ተጀምሯል።

ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

ለሀገር በቀል ዕውቀት(Indigenous Knowledge) ተመራማሪዎች   የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ፡፡==========================ነሃሴ 2/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲ...
08/08/2026

ለሀገር በቀል ዕውቀት(Indigenous Knowledge) ተመራማሪዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ፡፡
==========================
ነሃሴ 2/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ሀገር በቀል እውቀት ዙሪያ ምርምር እየሰሩ ለሚገኙ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በአይነታዊ መረጃ ትንተና (Qualitative Data Analysis) ዙሪያ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርቲው ከትምህርት ሚኒስተር በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በሀገር በቀል ዕውቀት ያተኮሩ ምርምሮችን በመስራት እና ሰነድ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬው ስልጠናም በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ምርምር እየሰሩ የሚገኙ ተመራማሪዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ስልጠናው ተመራማሪዎች ከአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር የተለያዩ አካባቢዎች የሰበሰቡትን የሀገር በቀል ዕውቀት መረጃ የተለያዩ ሶፍትዌሮችን በመጠቀም ለመተንተን እና ሳይንሳዊ የሆነ የምርምር ሰነድ እንዲያዘጋጁ የሚያስችል መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ክንዴ ሰልጣኞች በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት እና ልምድ በአግባቡ ተጠቅመው ምርምሮቻቸውን እንዲያከናውኑ አሳስበዋል ፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምር፣ ህትመት እና ሥነ-ምግባር ስርጸት ዳይሬክተር ተሰራ ቢተው (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርቲው በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ሰፊ ፕሮጀክት ቀርጾ እየሠራ እንደሚገኝ ገልፀው ለተመራማሪዎችም የተለያዩ ምሁራንን በመጋበዝ በአይነታዊ ጥናት (Qualitative research) MAXQDA software እና ሌሎች የመረጃ ትንተና ዘዴዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡

ስልጠናው በዋናነት መረጃ ትንተና (Qualitative Data Analysis) ማለትም Foundation, መረጃ ማዘጋጀት (Data Preparation) Coding, Codebook, Themes ,Interpretation reporting ላይ በማተኮር የሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ለሚሰሩ 16 ተመራማሪዎች ለሁለት ቀናት የተሰጠ ሲሆን ስልጠናውን የሰጡት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ጤና (Public Health) መምህር የሆኑት ህይወት ተስፋ ናቸው፡፡

ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተቀም!

Address

Injibara
40

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Injibara University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Injibara University:

Shortcuts

Share