08/08/2026
ለሀገር በቀል ዕውቀት(Indigenous Knowledge) ተመራማሪዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ፡፡
==========================
ነሃሴ 2/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ሀገር በቀል እውቀት ዙሪያ ምርምር እየሰሩ ለሚገኙ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በአይነታዊ መረጃ ትንተና (Qualitative Data Analysis) ዙሪያ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርቲው ከትምህርት ሚኒስተር በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በሀገር በቀል ዕውቀት ያተኮሩ ምርምሮችን በመስራት እና ሰነድ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬው ስልጠናም በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ምርምር እየሰሩ የሚገኙ ተመራማሪዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ስልጠናው ተመራማሪዎች ከአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር የተለያዩ አካባቢዎች የሰበሰቡትን የሀገር በቀል ዕውቀት መረጃ የተለያዩ ሶፍትዌሮችን በመጠቀም ለመተንተን እና ሳይንሳዊ የሆነ የምርምር ሰነድ እንዲያዘጋጁ የሚያስችል መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ክንዴ ሰልጣኞች በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት እና ልምድ በአግባቡ ተጠቅመው ምርምሮቻቸውን እንዲያከናውኑ አሳስበዋል ፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምር፣ ህትመት እና ሥነ-ምግባር ስርጸት ዳይሬክተር ተሰራ ቢተው (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርቲው በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ሰፊ ፕሮጀክት ቀርጾ እየሠራ እንደሚገኝ ገልፀው ለተመራማሪዎችም የተለያዩ ምሁራንን በመጋበዝ በአይነታዊ ጥናት (Qualitative research) MAXQDA software እና ሌሎች የመረጃ ትንተና ዘዴዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው በዋናነት መረጃ ትንተና (Qualitative Data Analysis) ማለትም Foundation, መረጃ ማዘጋጀት (Data Preparation) Coding, Codebook, Themes ,Interpretation reporting ላይ በማተኮር የሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ለሚሰሩ 16 ተመራማሪዎች ለሁለት ቀናት የተሰጠ ሲሆን ስልጠናውን የሰጡት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ጤና (Public Health) መምህር የሆኑት ህይወት ተስፋ ናቸው፡፡
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተቀም!