Abyssinia-Ethiopia

Abyssinia-Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Abyssinia-Ethiopia, Injibara.

ለአላማህ ዋጋ መክፈል‼️ለፈተና 4.5 ኪሎ ሜትር በከባድ የበረዶ ግርግር ተጓዞ 99 ያመጣው የ8 ዓመቱ ህፃን‼️በቻይና ገጠራማ አካባቢ የሚኖረው የ8 ዓመቱ ህፃን ዋንግ ፉማን (Wang Fuma...
20/08/2026

ለአላማህ ዋጋ መክፈል‼️
ለፈተና 4.5 ኪሎ ሜትር በከባድ የበረዶ ግርግር ተጓዞ 99 ያመጣው የ8 ዓመቱ ህፃን‼️

በቻይና ገጠራማ አካባቢ የሚኖረው የ8 ዓመቱ ህፃን ዋንግ ፉማን (Wang Fuman) ለፈተና ለመድረስ ሲል በከባድ ቅዝቃዜ ውስጥ ያደረገው አስገራሚ ጉዞ የመላውን ዓለም ትኩረት ስቧል። ህፃኑ በዚያ የፈተና ቀን ከዜሮ በታች በሆነ ቅዝቃዜ ውስጥ 4.5 ኪሎ ሜትር ያህል በእግር ተጉዞ ትምህርት ቤት ደርሷል።

ትምህርት ቤት ሲደርስ ፀጉሩ፣ ቅንድቡ እና የዓይን ሽፋሽፍቶቹ ሙሉ በሙሉ በበረዶ የተሸፈኑ የነበረ ሲሆን፣ እጆቹም በከባዱ ቅዝቃዜ ምክንያት አብጠውና ቀልተው ነበር። ዋንግ ይህንን ሁሉ አስቸጋሪ መንገድ ተቋቁሞ በመጨረሻም በፈተናው 99 ከ 100 በማምጣት አስደናቂ ስኬት አስመዝግቧል።

የህፃኑ ታሪክ በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ህፃናት የሚያጋጥማቸውን አስቸጋሪ ሁኔታ ያሳየና የብዙዎችን ልብ የነካ ሲሆን፣ በርካታ ሰዎች ለህፃኑ እና ለትምህርት ቤቱ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

20/08/2026

ሰበር ዜና
********
የኦሮሚያ ክልል ተወካዮች አዲስ አበባ የክልሉ ዋና ከተማ መሆኗ ካልተረጋገጠ በሚል ምክክሩን አፍርሰው ወጡ።
*************************************************
ዛሬ ነሐሴ 14/2018 የምክክር ኮሚሽኑ ስብሰባ የተስማማባቸውን አጀንዳዎች ለባለ 4 ሺ ተመካካሪዎች ለማቅረብ ጫፍ የተደረሰ ቢሆን የኦሮሚያ ተመካካሪዎች ትላንት የተስማሙበትን አፍርሰው አዲስ አበባ የኦሮሚያ ዋና ከተማ መሆኗ እውቅና ካልተሰጠን በሚል ረግጠው ወጥተዋል።

መረጃዎች እየተከታተልን እናደርሳችኋለን።

መቶዎችን የቀጠፈው የመሬት ናዳ❗❗በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የወርቅ ማውጫ ስፍራ በደርመስ ከ100 በላይ ሞቱ።የነፍስ አድን ሠራተኞች በቦታው ተገኝተው ሰዎችን ለማውጣት ጥረት እያደረጉ ቢሆን...
20/08/2026

መቶዎችን የቀጠፈው የመሬት ናዳ❗❗
በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የወርቅ ማውጫ ስፍራ በደርመስ ከ100 በላይ ሞቱ።
የነፍስ አድን ሠራተኞች በቦታው ተገኝተው ሰዎችን ለማውጣት ጥረት እያደረጉ ቢሆንም ወርቅ አውጭዎችን በሕይወት የማትረፉ ዕድል እየተመናመነ ነው ተብሏል፡፡
አደጋው የተባባሰው ወርቅ ቆፋሪዎቹ የደከሙ መሣሪያዎችን ሚጠቀሙ በመሆናቸው እና የአደጋ ምላሽ ስርአቱም በመሳሳቱ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
በካሜሩን ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው ዛምቦዬ አደጋው ከደረሰ 2 ቀን በኋላም አስከሬኖች እየወጡ መሆኑን ኢንዲያን ቱዴይ ዘግቧል፡፡
ይሁን እንጂ የአካባቢው ሰወች የአደጋ ጊዜ ሠራተኞቹ በቂ መሳሪያም ሆነ ሙያው የላቸውም በማለት ተችተዋል፡፡
ከጉዳተኞቹ መካከል የጎረቤት ካሜሩን ዜጎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡
የአካባቢው ቀይ መስቀል ተጎጂዎችን የመፈለግ ሂደቱን እያገዘ ነው የተባለ ሲሆን የሟቾች ብዛት ሊያሻቅብ እንደሚችል ተገምቷል፡፡
በዓመቱ መጀመሪያ አካባቢ አጥኚዎች እና መገናኛ ብዙኃን ደህንነቱ ያልተጠበቀ እና ቁጥጥር የማይደረግበት የማዕድን ቁፋሮ ብዙዎችን እየሳበ ስለመሆኑ ይፋ አድርገው እንደነበር ዘገባው አስታውሷል፡፡

የአገራዊ ምክክሩ አራት አጀንዳዎች ከስምምነት ሳይደረስባቸው ወደ ቀጣይ ዙር ተሻገሩ❗❗በአገራዊ ምክክሩ የመንግሥት አደረጃጀትን ጨምሮ አራት አከራካሪ ጉዳዮች በ120 አባላት ያለው የሐሳብ አዘ...
19/08/2026

የአገራዊ ምክክሩ አራት አጀንዳዎች ከስምምነት ሳይደረስባቸው ወደ ቀጣይ ዙር ተሻገሩ❗❗

በአገራዊ ምክክሩ የመንግሥት አደረጃጀትን ጨምሮ አራት አከራካሪ ጉዳዮች በ120 አባላት ያለው የሐሳብ አዘጋጅ ቡድን ስምምነት ሳይደረስባቸው ወደ ቀጣዩ የምክክር ሂደት መሻገራቸው ተገለጸ።

በአጀንዳው 500 ተሳታፊዎች ባሉበት የሥራ ቡድን 53 ጉዳዮች ቀርበው፣ 50 ላይ ስምምነት ሲደረስ ሦስቱ ግን ሳይስማሙ እንደቀሩ ቀደም ሲል ተገልጿል። የሐሳብ አዘጋጅ ቡድኑ እነዚህን ጉዳዮች በማጣጣም 62 ምክረ ሐሳቦች አድርጎ ሲያቀርብ፣ አራቱ ላይ የጋራ ስምምነት ሊደረስ እንዳልቻለ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

ከእነዚህ መካከል ዋነኛው የመንግሥት አወቃቀር ጉዳይ ሲሆን፣ አንደኛው አማራጭ ፓርላሜንታዊ ሥርዓት እንዲኖርና ፕሬዚዳንቱ ከፓርላማ እንዲመረጥ የሚደግፍ ሲሆን፣ ሌላኛው ፕሬዚዳንታዊ ሥርዓት እንዲኖርና ፕሬዚዳንቱ በሕዝብ ቀጥታ እንዲመረጥ የሚል ነው።

ሌሎቹ ሁለት ጉዳዮች የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት አመራረጥና በምክር ቤቱ የብሔረሰቦች ውክልና አሠራርን የሚመለከቱ ናቸው። በአባላት አመራረጥ ላይ አንዱ ሐሳብ አባላት በክልሎች ምክር ቤቶች እንዲመረጡ ሲደግፍ፣ ሌላው ሕዝቡ በቀጥታ እንዲመርጣቸው የሚል ነው።

በብሔረሰቦች ውክልና ላይም አንድ ሐሳብ በሕዝብ ብዛት መሠረት ተጨማሪ ውክልና እንዲኖር ሲደግፍ፣ ሌላው ሁሉም ብሔረሰቦች በእኩል መልኩ እንዲወከሉ የሚል ሐሳብ ቀርቧል።

አራተኛው አከራካሪ ጉዳይ “ውህድ ማንነት” የሚለው ሐሳብ ሲሆን፣ የሥራ ቡድኑ ቀደም ሲል በስምምነት አልፎ የነበረው ሐሳብ በ120 አባላት ባለው የሐሳብ አዘጋጅ ቡድን ዳግም የአለመስማማት ጉዳይ ሆኗል። በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ መቅረቡንና ከስምምነት ይልቅ አለመስማማት በሚል ወደ ቀጣዩ ዙር መተላለፉን ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

በመሆኑም አራቱ ጉዳዮች በቀጣዩ የምክክር ዙር የበለጠ ውይይትና የመግባባት ሥራ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሆነው መቀጠላቸው ታውቋል።

አሁናዊ መረጃ❗❗ነሐሴ 12/2018❗በደቡብ ወሎ በምዕራብ ቀጠና ከባድ ውጊያ መቀስቀሱ ተገለጸ።በምዕራብ ወሎ ቀጠና በሚገኙ ስትራቴጂካዊ ቦታዎች ከዛሬ ማለዳ 11 ሰዓት ጀምሮ ከባድ ውጊያ እየተ...
18/08/2026

አሁናዊ መረጃ❗❗
ነሐሴ 12/2018❗
በደቡብ ወሎ በምዕራብ ቀጠና ከባድ ውጊያ መቀስቀሱ ተገለጸ።

በምዕራብ ወሎ ቀጠና በሚገኙ ስትራቴጂካዊ ቦታዎች ከዛሬ ማለዳ 11 ሰዓት ጀምሮ ከባድ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑን የመረጃ ምንጮች ገለፁ።

ውጊያው እጅግ ወሳኝ እና ስትራቴጂካዊ በሚባሉት በዋናነት በመቅደላ ወረዳ፣ በተንታ እንዲሁም በደላንታ ቀጠናዎች በሚገኙ ተራራማ አካባቢዎች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ በሰባት የተለያዩ ንኡስ ግንባሮች ተከፍሎ እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ይዘን እንመለሳለን።

10 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሬዝዳንትነት ቦታቸውን ለውድድር ክፍት ሊያደርጉ ነው! ተወዳደሩ!!​ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችን ምልመላ እና ምደባ በተመለከተ አዲስ መመሪያ ...
18/08/2026

10 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሬዝዳንትነት ቦታቸውን ለውድድር ክፍት ሊያደርጉ ነው! ተወዳደሩ!!

​ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችን ምልመላ እና ምደባ በተመለከተ አዲስ መመሪያ አፅድቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል። ባለፉት ሁለት ዓመታት የአመራር ክፍተት እንዳይፈጠር ፕሬዝዳንቶች በተጠባባቂነት ሲሰሩ የቆዩ ሲሆን፤ ከአሁን በኋላ ግን ምደባው ግልፅ፣ ፍትሃዊ እና በውድድር ላይ የተመሰረተ ይሆናል።

​ይህ አዲስ አሰራር ደረጃ በደረጃ የሚተገበር ሲሆን፤ ከሐምሌ 15/2018 ዓ.ም ጀምሮ በመጀመሪያው ዙር የሚከተሉት 10 ዩኒቨርሲቲዎች የፕሬዝዳንትነት ቦታቸውን ለውድድር ክፍት አድርገዋል፦
​1️⃣ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ
2️⃣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
3️⃣ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
4️⃣ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
5️⃣ መቱ ዩኒቨርሲቲ
6️⃣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ
7️⃣ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
8️⃣ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
9️⃣ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ
🔟 ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ

​በአሁኑ ወቅት አብዛኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ከስራ አመራር ቦርዳቸው ጋር በመነጋገር የውድድር ሂደቱን ጀምረዋል። ብቃት ያላቸው አመራሮች ወደ ዩኒቨርሲቲዎቻችን መምጣታቸው የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋፅዖ ይኖረዋል!

"ወለጋ በሰላም ያልኖረ ኦሮሞ እንዴት አዲስ አበባን ይመኛል፤ አዲስ አበባ የኦሮሞ ናት ከሚሉት ውስጥ እኔን ቀንሱኝ'' ፕሮፌሰር ህዝቅኤል ጋቢሳ"ኦሮሞ አዲስ አበባን አልፈለገም፤ ኦሮሞ የሚፈል...
17/08/2026

"ወለጋ በሰላም ያልኖረ ኦሮሞ እንዴት አዲስ አበባን ይመኛል፤ አዲስ አበባ የኦሮሞ ናት ከሚሉት ውስጥ እኔን ቀንሱኝ'' ፕሮፌሰር ህዝቅኤል ጋቢሳ

"ኦሮሞ አዲስ አበባን አልፈለገም፤ ኦሮሞ የሚፈልገው ነቀምትን፣ ጅማን፣ ሻሸመኔን ማስተዳደር ነው። ወለጋ በሰላም ያልኖረ ኦሮሞ እንዴት አዲስ አበባን ይመኛል። አዲስ አበባ የነዋሪዎቿ ናት።"

ሀሳብዎን ያካፍሉን?

''በአበሽጌ የተፈጸመው ግድያ ቀይሽብርን የሚስተካከል ነው! መሰል ግፍን በቃ ለማለትና እንዳይደገም ለአንድ ቀን እናስባቸው ''በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የተሰጠ መግለ...
15/08/2026

''በአበሽጌ የተፈጸመው ግድያ ቀይሽብርን የሚስተካከል ነው! መሰል ግፍን በቃ ለማለትና እንዳይደገም ለአንድ ቀን እናስባቸው ''

በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የተሰጠ መግለጫ

ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጉራጌ ዞን፣ አበሽጌ ወረዳ፣ ናቻ ቁሊት ቀበሌ ሦስት ወጣቶች በማንነታቸው ተመርጠውና ከሕዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ ላይ እንዲወርዱ ተደርገው "ፋኖ ናችሁ" በሚል ሰበብ ታሪክ እንደሚያወሳን በቀይ ሽብር ዘመን ሲደረግ ከነበረውም በላይ እጅግ ኢሰብዓዊ በሆነ ሁኔታ ግድያ መፈጸሙን አረጋግጠናል።

ከአካባቢው ምንጮች ባገኘነው መረጃ መሠረት የጭካኔውን ወደር የለሽነት የሚያረጋግጠው ዘግናኙን ድርጊት ፈጻሚው የፀጥታ አካል ከገደላቸውም በኋላ አስከሬናቸውን የቀብር አፈር እንዳይቀምስ በመከልከሉ በአውሬ እንዲበላ መደረጉንም ሰምተናል።

ከግፍ ሰለባዎቹ አንዱ የሆነው ይታገሱ አሰግደው ከዚህ ቀደም ወንድሙ ከሐዋሳ ተይዞ በተመሳሳይ እንዲረሸን ተደርጓል። ይህም ግድያው ቤተሰብንና ማንነትን ማዕከል ያደረገ ለመሆኑ ማረጋገጫ ነው ይላሉ የአካባቢው ምንጮች።

በተመሳሳይ ከወር በፊት ግዛቸው ግርማ የተባለ ሌላ ወጣት በዚያው በአበሽጌ ወረዳ፣ ዳርጌ ቀበሌ በዘፈቀዳዊ መንገድ ተረሽኗል። ወጣቱ ሥራ ፈጣሪና ለበርካታ ወጣቶች የሥራ እድል የከፈተ ብሎም በአካባቢው እጅግ ምሥጉን ነበር።

የዞኑም ሆነ ወረዳው ማኅበረሰብ በፍቅርና በመከባበር በመኖር የሚታወቅና እንደምሣሌም የሚጠቀስ ነው። አንዳንድ የወረዳ አመራሮችና የፀጥታ አካላት እያመጡት ያለው መግለጫም አደገኛና ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ የሚደረግ ከመሆኑም በተጨማሪ ዜጎች ምክንያት እየተፈጠረላቸው በዘፍቃድ እንዲጨፈጨፉ የሚያበረታታ መሆኑንም በግልፅ የሚያሣይ ነው።

ሰው በወንጀል ተግባር ተሳትፏል ቢባል እንኳን ለፍርድ ወደ ሕግ ቦታ ቀርቦ ፍርዱን በአደባባይ ያገኛል እንጂ ከሕግ ውጭ ዜጎችን የፊጥኝ አሥሮ በጥይት ደብድቦ መግደል የሚያሳየው ሥርዓቱ በዜጎች ላይ እየፈጸመ ያለውን አጠቃላይ የሰብዓባዊ መብት ጥሰት፣ የደቦ ፍርድና ጭካኔ መሆኑን ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት(የሦስቱ ፓርቲዎች ጥምርት) ያምናል፤ የግፍ ግድያውንም በጽኑ ያወገዛል፡፡

ለሞቱት ነፍስ ይማር እያለ ለአካባቢው ማኅበረሰብና ወዳጅ ዘመድ መጽናናትን ይመኛል፡፡ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብም ማክሰኞ ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሦስቱ ወጣቶች ዘፈቀዳዊ ግድያና በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በሚደረጉ ተመሳሳይ ኢሰብዓዊ ድርጊቶችን በማውገዝ የአንድ ቀን የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ “የንጹሓን የግፍ ግድያ ይብቃ//Stop Massacre of Civilians//” በሚል ቃል እንዲያወግዝና ድምጹንም ለዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ እንዲያሰማ ጥሪ እያቀረብን፤

1.ከሕግ ውጭ ምክንያት ፈጥሮ ግድያ የፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎችና ግፉ እንዲፈፀም ትዕዛዝ የሰጡ አካላት ለፍትሕ አደባባይ እስከሚቀርቡ ሕዝቡ ድምጹን እንዲያሰማ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

2.ግፉን ፈጻሚና አስፈጻሚ አካላት እየሰጡ ያሉት የማንአለብኝነት መግለጫ እንዲቆም እያሳሰብን ግድያዎች አፋጣኝ፣ ገለልተኛ፣ ግልጽና አስተማማኝ ምርመራ እንዲደረግባቸው እንጠይቃለን።

ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት - ለኢትዮጵያ
ነሐሴ ፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

 🙏🙏🙏ስንቱ በሙስና ተዘፍቆ እያንዳንዷን ኢንች መሬት ለራሱ ጥቅም እየቸበቸበ  ባለበት ሃገር ውስጥ 1045 ሄክታር መሬት በመከለል ለ20 ሺህ የከተማዋ ነዋሪዎች የቤት ባለቤት ያደረገ ደፋር፣...
13/08/2026

🙏🙏🙏

ስንቱ በሙስና ተዘፍቆ እያንዳንዷን ኢንች መሬት ለራሱ ጥቅም እየቸበቸበ ባለበት ሃገር ውስጥ 1045 ሄክታር መሬት በመከለል ለ20 ሺህ የከተማዋ ነዋሪዎች የቤት ባለቤት ያደረገ ደፋር፣ ጀግና፣ የህዝብ ልጅ የባ/ዳር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ Goshu Endalamaw ክብር ይገባዎታል፥ በሃገሪቱ ያላችሁ የከተማ ከንቲባዎችም ከዚህ ታታሪ ሰው ትምህርት ውሰዱ እንላለን

🙏 እናመሰግናለን 🙏

Address

Injibara

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abyssinia-Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share