15/07/2026
ወርልድ ብራይት አካዳሚ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12 ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ።
ፈተናው በወርልድ ብራይት ኮሌጅ ውስጥ በኦንላይን ቴክኖሎጂ ዘዴ የተሰጠ ሲሆን የሶስቱም ዙሮች ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግም በኮሌጁ ቅጥር ግቢ ውስጥ ችግኝ ተካላ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በተፈጥሮና በማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ 2መቶ 14 ተማሪዎችን በሶስት ዙሮች ማስፈተን ስለመቻሉም ተገልጿል።
ከተፈተኞች መካከል ተማሪ መሳይ ማቴዎስ እና ምንተስኖት ግዛው በሰጡት አስተያየት በዓመቱ የትምህርት ወቅቶች ከመደበኛ ትምህርት በተጨማሪ መምህራን ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠታቸው ለፈተናው እንዳገዛቸው ተናግረዋል።
በዓመቱ የተሰጡ የክፍል ፈተናዎችና ሞዴል ፈተና ከወረቀት ነፃ በሆነ መንገድ መፈተናቸው አሁን በኦንላይን ሲስተም ክህሎት አንዲፈተኑ እንዳገዛቸውም ገልፅዋል።
በተማርንበትና በለመድንበት በራሳችን ት/ቤት መፈተናችን በተረጋጋ ሁኔታ ፈተናውን እንዲናጠናቅቅ አግዞናልም ብለዋል ተማሪዎቹ።
የወርልድ ብራይት ኮሌጅ ፈተና ጣቢያ ኃላፊ መምህር ዘነበ አሰፋ እንደገለጹት በፈተና ጣቢያው በሶስት ዙሮች ማለትም በዙር ሁለት፣ ሶስትና አራት በተፈጥሮና በማህበራዊ ትምህርት ዘርፍ 2መቶ 14 ተማሪዎች የተፈተኑ ሲሆን ከዚህም 76ቱ የማህበራዊ ትምህርት ዘርፍ ተማሪዎች ናቸው።
ለተማሪዎቹ በተማሩበት አካባቢና ት/ቤት ለኦን ላይን ፈተና የሚሆን ግብኣት ተሟልቶ መፈተናቸው ያለምንም መረበሽ ተረጋግተው እንዲፈተኑ እንዳገዛቸው የተናገሩት የፈተና ጣቢያው ኋላፊ አካዳሚው ይህን ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ የሚበረታታ መሆኑንም አክለዋል።
በሶስቱም ዙሮች የተሰጠው ፈተና ሰላማዊ እንደነበር የጠቆሙት ኃላፊው የጣቢያው ፈተና በስኬት ተጠናቋልም ብለዋል።
የወርልድ ብራይት አካዳሚ ስራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ አበራ በበኩላቸው የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለብሔራዊ ፈተና
የማዘጋጀት ስራዎች በትኩረት እየተሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።
የትምህርት ዘመኑ ብሔራዊ ፈተና ከመጀመሩ በፊትም በሞዴል እና በክፍል ፈተናዎችን ከወረቀት ነፃ በሆነ ዘዴ በመስጠት ተማሪዎች የኮምፒውተር ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።
ለኦንላይን ቴክኖሎጂ የሚሆኑ ግብዓቶችን ማሟላት ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ ቢሆንም ጉዳዩ ሀገራዊ ተልዕኮ መሆኑን በመረዳት የተቋሙ ቦርድ እና አመራር ባደረጉት ጥረት ግብዓቶችን ለማሟላት ስለመቻሉም ገልጸዋል።
አካዳሚው የግል ተቋም ሆኖ በራሱ ተቋም ራሱን ችሎ የራሱን ተማሪዎች በኦንላይን ዘዴ ለመፈተን መቻሉ ትልቅ ታሪካዊ ስኬት መሆኑን ያነሱት አቶ ብርሃኑ ይህ ደግሞ ተማሪዎች በተረጋጋ ሁኔታ ፈተና መውሰድ እንድችሉ ያገዘ መሆኑን አብራርተዋል።
ፈተናው ያለምንም ችግር በሰላም መጠናቀቁ ሌላኛው ስኬት መሆኑን ገልፀው ለስኬቱ አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል።
በአካዳሚው ሲሰጥ የነበረው ብሔራዊ ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግም የወርልድ ብራይት ኮሌጅ ፕሬዝደንት ተሰማ አበራ(ዶር)ን ጨምሮ ተፈታኝ ተማሪዎች፣ፈተኝ መምህራን እና በፈተና ጣቢያው የተመደቡ የፀጥታ አካላት ጋራ በመሆን በወርልድ ብራይት ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ችግኝ ተክለዋል።
ዘገባው የወርልድ ብራይት ኮሌጅ ዳይርክቶሬት ነዉ
08/11/2018 ዓ/ም