18/10/2023
ነፃ ትምህርት ዕድል ማስታወቂያ
በሰዎች ለሰዎች ድርጅት ስር የሚተዳደረው የሐረር አግሮ፣ ቴክኒክና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ለ2016 የትምህርት ዘመን ብቁ እና ተወዳዳሪ የሆኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን በማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ እና በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ቴክኖሎጂ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ መርሐግብር ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል ፡፡
የመመዝገቢያ መስፈርቶች :-
1ኛ. በ2012 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሐገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው ከ700 ድምር ውጤት የሚከተለውን ያስመዘገቡ፤
ለመደበኛ እና ማታ ተፈታኞች
ወንዶች 370 እና ከዚያ በላይ
ሴቶች 358 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
ለታዳጊ ክልልና አርብቶ አደር አካባቢዎች መደበኛ ተፈታኞች
ወንዶች 358 እና ከዚያ በላይ
ሴቶች 348 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
ለግል (ድጋሚ ተፈታኞች) በሁለቱም ጾታ
375 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
ለትግራይ ክልል እና መተከል ዞን
ወንዶች 348 እና ከዚያ በላይ
ሴቶች 340 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
2ኛ. በ2013 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሐገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና በመጀመሪያው ዙር ተፈትነው ከ600 ድምር ውጤት የሚከተለውን ያስመዘገቡ፤
ለመደበኛ ተፈታኞች
ወንዶች 348 እና ከዚያ በላይ
ሴቶች 336 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
ለታዳጊ ክልልና አርብቶ አደር አካባቢዎች መደበኛ ተፈታኞች
ወንዶች 336 እና ከዚያ በላይ
ሴቶች 324 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
ለግል (ድጋሚ ተፈታኞች) በሁለቱም ጾታ
365 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
3ኛ. በ2013 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሐገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና በሁለተኛው ዙር ተፈትነው ከ700 ድምር ውጤት የሚከተለውን ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች፤
ለመደበኛ ተፈታኞች
ወንዶች 408 እና ከዚያ በላይ
ሴቶች 394 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
ለታዳጊ ክልልና አርብቶ አደር አከባቢዎች መደበኛ ተፈታኞች
ወንዶች 395 እና ከዚያ በላይ
ሴቶች 381 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
ለግል (ድጋሚ ተፈታኞች) በሁለቱም ጾታ
428 እና ከዚያ በላይ ያገኙ
4ኛ. በ2014 እና 2015 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሐገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው ከ700 ድምር ውጤት 350(50%) እና ከዚያ በላይ ያመጡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች።
5ኛ. በ2015 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የአቅም ማሻሻያ (ሬሚዲያል) ትምህርት ወስደው ማለፊያ ውጤት (50%) እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች።
የመመዝገቢያ ቦታዎች
1ኛ. Online
Google form : https://forms.gle/PRigPH6Tma9HFfPK9
Telegram Bot: https://t.me/MFMATTC_bot
በድረ ገጻችን ፡ http://www.mfmattc.edu.et መመዝገብ ትችላላችሁ ፡፡
2ኛ. በአካል
አዲስ አበባ፡ ቦሌ ቡልቡላ በሚገኘው የሰዎች ለሰዎች ድርጅት
ሐረር፣ በኮሌጁ ቅጥር ግቢ
ሐዋሳ፣ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ
የምዝገባ ቀን
በአካል: ከጥቅምት 12 እስከ 14 ቀን 2016 ዓ/ምባሉት ቀናቶች በስራ ሰዓት ብቻ ይሆናል፡፡
Online ማስታወቂያ ይፋ ከሆነበት እለት እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ/ም
ተመዝጋቢዎች ለምዝገባ ሲመጡ የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን ዋናውን እና ኮፒውን እንዲሁም ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
አመልካቾች ኮሌጁ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና መውሰድ አለባቸው።
የፈተና ቦታ እና ቀን
የፈተና ቀን፡
የኮሌጁን የመግቢያ ፈተና ቀን ከላይ በተገለጹት platform እና በውስጥ ማስታወቂያ ኮሌጁ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል፡፡
የፈተና ቦታ ፡
1ኛ. ሐረር በሚገኘው የኮሌጁ ቅጥር ግቢ እና
2ኛ. አዲስ አበባ በተመረጡ መፈተኛ ጣቢያዎች የሚሰጥ ይሆናል።
ማሳሰቢያ፦
በአቅም ማሻሻያ (ሬሚዲያል) ማለፊያ ውጤት ተመዝጋቢዎች ለመመዝገብ ውጤቱን የሚያሳይ የተረጋገጠ የትምህርት የምስክር ወረቀት ሊኖራቹ ይገባል.
ኮሌጁ የነፃ የትምህርት ፣ ምግብ እና ማረፊያ ይሰጠል፣ እንዲሁም ከወጪ መጋራት (Cost sharing free) ነፃ ነው።
ከተመዘገቡት አመልካቾች ውስጥ ለፈተና የሚቀርቡት ስም ዝርዝራቸው ከፈተና ቦታዎች ጋር የሚገለፅ ይሆናል።
Access Google Forms with a personal Google account or Google Workspace account (for business use).