Gambella Region Education Bureau Page

Gambella Region Education Bureau Page የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ወቅታዊና ታማኝ ትምህርታዊ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ ለማድረስ የተዘጋጀ የመረጃ ገጽ ነው

የክልላዊ እና ብሔራዊ ፈተናዎች ዝግጅት ተጠናቀቀ፤ የተማሪዎች መረጃ እና የፈተና ጣቢያዎች ይፋ መሆን​ጋምቤላ — በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የሚሰጡትን የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እና የ8ኛ ...
22/05/2026

የክልላዊ እና ብሔራዊ ፈተናዎች ዝግጅት ተጠናቀቀ፤ የተማሪዎች መረጃ እና የፈተና ጣቢያዎች ይፋ መሆን
​ጋምቤላ — በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የሚሰጡትን የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እና የ8ኛ ብሄራዊ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ-ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ከፈተናው የጊዜ ሰሌዳ፣ ከተማሪዎች ምዝገባ እና ከፈተና ጣቢያዎች ጋር የተያያዙ ዝርዝር መረጃዎችም ይፋ ሆነዋል።
​1. የፈተና ጊዜ ሰሌዳ (Schedule)
​ፈተናዎቹ በአገር አቀፍ እና በክልል ደረጃ በተቀመጠው ወጥ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የሚሰጡ ሲሆን፣ ተማሪዎች ካሁኑ ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ጥሪ ቀርቧል።
​የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና: ከሰኔ 08 እስከ ሰኔ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት 2 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ይሰጣል።
​የ8ኛ ክፍል ፈተና: ከሰኔ 11 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ የሚሰጥ ይሆናል።
​ማሳሰቢያ: ተማሪዎች በፈተናው እለት ጠዋት በ2:30 ሰዓት ላይ በየፈተና ክፍሎቻቸው መገኘት እንዳለባቸውና ፈተናው በ3:00 ሰዓት በይፋ እንደሚጀምር ተገልጿል።

​2. የተማሪዎች መረጃ እና ዲጂታል ምዝገባ
​በዘንድሮው የፈተና ዝግጅት ላይ የተማሪዎችን መረጃ ጥራት ለመጠበቅ እና ማጭበርበሮችን ለመከላከል ዘመናዊ የዲጂታል የመረጃ ሥርዓት ጥቅም ላይ ውሏል።
​የተማሪዎች ብዛት: ተፈታኝ የ6ኛ ክፍል ወንድ: 9,351
ሴት: 7,473 ድምር: 16,824 ሲሆኑ
የ8ኛ ክፍል ፈተናውን ለመውሰድ ወንድ: 11,093
ሴት: 8,327 ድምር: 19,420 የሚቆጠሩ ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል።
​የመለያ ቁጥር (Admission Card): እያንዳንዱ ተማሪ ፎቶግራፉን እና ሙሉ መረጃውን የያዘ ዲጂታል የፈተና መግቢያ ካርድ ለሁሉም ወረዳዎች በሲስተም መተግበሪያው ለተማሪዎች እንዲደርስ ተደርጓል።
​የመረጃ ማጣራት: የተማሪዎች ስም፣ እድሜ እና የትምህርት ክፍል ስህተቶች እንዳይኖሩ የወረዳ ፈተና ክፍል ከትምህርት ቤቶች ጋር በመቀናጀት አስቀድሞ የማጣራት ስራ ተከናውኗል።
​3. የፈተና ጣቢያዎች
​ፈተናው ሙሉ በሙሉ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ታማኝ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ የ6ኛ ክፍል 270 እና የ8ኛ ክፍል
217 የፈተና ጣቢያዎች ተዘጋጅተዋል
​መልዕክት
​ክልል ትምህርት ቢሮም በስተመጨረሻ ባስተላለፈው መልዕክት፣ ወላጆች ለልጆቻቸው ምቹ የንባብ አካባቢ እንዲፈጥሩላቸው፣ ተማሪዎችም በተረበሸ ስሜት ሳይሆን በራስ መተማመን ለፈተናው እንዲዘጋጁ እና ከማንኛውም የፈተና ኩረጃ ድርጊት እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
ለሁሉም ተማሪዎች መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆን እንመኛለን!

22/05/2026

የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ የፈተና ሰሌዳን ይፋ አደረገ።

ከጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት(ግንቦት 14/2018 ዓ.ም)

​የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ኡኩኝ ኡኬሎ በሰጡት መግለጫ፣ በዘንድሮው የ2018 ዓ.ም ክልላዊ ፈተና ላይ በአጠቃላይ 36 ሺህ 244 ተማሪዎች እንደሚቀመጡና ለዚህም አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል።

​እንደ ቢሮ ሃላፊው ማብራሪያ፣ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 9/2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ በ270 የፈተና ጣቢያዎች ላይ ይሰጣል ብለዋል።

ለዚህ ፈተና ከሚቀመጡት 16 ሺህ 824 አጠቃላይ ተማሪዎች መካከል 9 ሺህ 351 ያህሉ ወንዶች ሲሆኑ፣ 7 ሺህ 473ቱ ደግሞ ሴት ተማሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

​በተመሳሳይ መልኩ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከሰኔ 11 እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ እንዲሰጥ የተወሰነ ሲሆን፣ ፈተናውን ለማስተናገድም 217 የፈተና ጣቢያዎች ተዘጋጅተዋል።

በዚህ የክፍል ደረጃ ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 19 ሺህ 420 ተማሪዎች ውስጥ 11 ሺህ 93ቱ ወንዶች ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 8 ሺህ 327ቱ ደግሞ ሴት ተማሪዎች መሆናቸውን ገልፀዋል።

​ፈተናው በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ መላው የማህበረሰብ ክፍል፣ ወላጆች እና መምህራን ለተማሪዎቹ አስፈላጊውን እገዛ እና ክትትል እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

የ2018 የተማሪዎች አድሚሽን ካርድ ተዘጋጅቶ የተለቀቀ መሆኑን እየገለጽን ለ6ኛ ክፍልhttps://gambella6.ministry.etለ8ኛ ክፍልhttps://gambella.ministry.etበመ...
20/05/2026

የ2018 የተማሪዎች አድሚሽን ካርድ ተዘጋጅቶ የተለቀቀ መሆኑን እየገለጽን
ለ6ኛ ክፍል
https://gambella6.ministry.et
ለ8ኛ ክፍል
https://gambella.ministry.et
በመጠቀም download በማድረግ ተማሪዎች እንዲያረጋግጡ በማድረግ የስም፣የጾታ፣የስትሪም፣ የፎቶ እና ሌሎች ስህተቶች ካሉ በአንድ ሳምንት ውስጥ እንድታስተካክሉ እናሳስባለን።

አድሚሽን ካርድና አቴንዳንስ download ለማድረግ ተከታዩን ቪዲዮ ማየት ይቻላል
👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/5Lzb5BBb7G0?si=MPO0sy2y2cAorGKQ

ማስታወቂያ ለ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ መጪ ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋ...
14/05/2026

ማስታወቂያ ለ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ

መጪ ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Card) በፈተና አስተዳደር ሲስተም (https://exam.eaes.et/) ከ03/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለክልል ትምህርት ቢሮ፣ ለዞን ትምህርት መምሪያዎች እና ለትምህርት ቤት ተወካዮች ተለቋል።
ስለሆነም፡-
1.እያንዳንዱ ተፈታኝ ተማሪ በአድሚሽን ካርዱ ጀርባ ላይ የተፈታኝ ተማሪው ትምህርት ቤት ወይም የወረዳው አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበትን አድሚሽን ካርድ ከትምህርት ቤቱ ወስዶ በእጁ መያዝ ይጠበቅበታል።

2.በምዝገባ ወቅት በተፈታኙ ወይም በመዝጋቢው የተከሰተ የትምህርት መስክ፣ የጾታ፣ የፎቶ እና መሰል ማስተካከያዎች ካሉ ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በፊት ለትምህርት ቤቱ ማሳወቅና ሂደቱን ጠብቆ መስተካከሉንም ከትምህርት ቤቱ ማረጋገጥ ይጠበቅበታል።

3.እያንዳንዱ ተፈታኝ አድሚሽን ካርዱን ወደ መፈተኛ ማዕከልም ሆነ መፈተኛ ክፍል ለመግባት የሚጠቀምበት በመሆኑ በአግባቡና በጥንቃቄ መያስ ይገበዋል።

4.ተፈታኞች በፈተና ወቅት ከአድሚሽን ካርድ በተጨማሪ የፋይዳ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን በጋራ እንከላከል
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ከትምህርት ለውጥ ትግበራ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል (ETOL, Education Transformation Operation for Learning) ፕሮጀክት ጋር በመተባ...
08/05/2026

የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ከትምህርት ለውጥ ትግበራ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል (ETOL, Education Transformation Operation for Learning) ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በተመረጡ ወረዳዎች ለሚገነቡ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግንባታ መመሪያ ሰነድ እና የአካባቢና ማህበረሰብ ጥበቃ ሰነድ አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አደረገ።

ክልል ትምህርት ቢሮ ከETOL ፕሮጀክት እና ከተመረጡ ወረዳዎች ጋር በመተባበር 10 ስታንዳርዱን መሠረት በማድረግ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት አቅዷል።

ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም (የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ)

አቶ ኡኩኝ ኡኬሎ(ቢሮ ኃላፊ) በተዘጋጀ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ መክፍቻ ላይ እንዳብራሩት እንደሀገር በተያዘው ዕቅድ ደረጃቸው የጠበቁ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት አስፈላጊነት እና የባለድርሻ አካላትን አበርክቶ ገልጸዉ የግንባታ ሂደቱ የተመረጠው ወረዳ አንድ ቅድመ አንደኛ ሲገነባ በትምህርት ሚኒስቴር አንድ የሚገነባ ሲሆን በዚህ ሂደት እንደክልል 10 ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚገነቡ መሆናቸውን አብራርተዋል።

ከትምህርት ለውጥ ትግበራ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል (ETOL) ፕሮጀክት የክትትል እና ግምገማ ባለሙያ የሆኑት አቶ አስቻለው ታዬ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግንባታ ዓላማ እና አስፈላጊነትን ገለጻ አድርገዋል።

የETOL የአካባቢ እና ማህበረሰብ ጥበቃ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጌታቸው ሙሉ ለሚገነቡት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ጋር በተያያዘ የአካባቢው እና ማህበረሰብ ጥበቃን ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

በመጨረሻም የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊና ም/ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም የቢሮው ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ የአኝዋሃ እና የኑዌር ብሄረሰብ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊዎች፣ የጆር፣ የጋምቤላ፣ የጂካዎና የማኮይ ወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና የወረዳ ት/ጽ/ቤት መረጃና ዕቅድ ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ የዕለቱ ውይይት መድረክ በስኬት ተጠናቋል።

የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ዘንድሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል የበይነመረብ ፈተና አስፈጻሚ ግብረ ሀይል አባላት፣ ተግባር እና ኃላፊነት ዙሪያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት አደረገ። ሚያዝያ 17/2018...
25/04/2026

የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ዘንድሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል የበይነመረብ ፈተና አስፈጻሚ ግብረ ሀይል አባላት፣ ተግባር እና ኃላፊነት ዙሪያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት አደረገ።

ሚያዝያ 17/2018 ዓ.ም(የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ)

በቀረበው ሰነድ የግብረሀይሉን አስፈላጊነትና ዓላማ እንዲሁም እስከ ወረዳ ድረስ የሚቋቋመው ስትሪንግ ኮሚቴ አባላትን፣ ተግባር እና ኃላፊነታቸውን ገለጻ ተደርጓል።

በመሠረታዊነት ግብረሀይሉ በየደረጃው ያለውን ኮምፒውተሮችን፣ መሠረተ ልማቶችን፣ የኤሌክትሪክ ኃይልን፣ የቴሌኮም አገልግሎቶችን ለስራው በሚያስፈልግ መጠን ዝግጁ ማድረግና አስቻይ ሁኔታዎችን የሚፈጥርና በተዋረድ ስራውን በበላይነት ይዞ የቅርብ ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ እንዲሁም የበይነመረብ ፈተናው ስኬት ዕቅድ የማዘጋጀት፣ የማስተባበርና አፈጻጸሙን የመከታተል ከፍተኛውን ሚና የሚጫወት መሆኑን በሰነዱ ተብራርቷል።

ውይይቱን የመሩት አቶ ኡኩኝ ኡኬሎ(ቢሮ ኃላፊ) ከዚህ በፊት የነበሩ ተሞክሮዎችን በማንሳት የዲጅታል ኢትዮጵያ አንዱ አካል የሆነውን የበይነመረብ ፈተና በስኬት ለመምራት ግብረሀይሉ ከሚመለከታቸው ጋር በትብብር ይሰራል ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎችም በቀረበው ሰነድ ዙሪያ የተሳካ ውይይት በማድረግ በሀገር አቀፍ ለሚሰጠው የበይነመረብ ፈተና ከተማሪዎች ልምምድ ጀምሮ ፈተናው እስከሚጠናቀቅ ድረስ በመተባበር የበኩላቸውን እንደሚወጡ በመግለጽ ውይይቱ በስኬት ተጠናቋል።

24/04/2026
የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የበይነመረብ ምዝገባ(Online Registration) መጋቢት 15/2018 እንደሚጠናቀቅ መግለፃችን ይታወሳል። ሆኖም ግን መዝጋቢዎችና የመመ...
29/03/2026

የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የበይነመረብ ምዝገባ(Online Registration) መጋቢት 15/2018 እንደሚጠናቀቅ መግለፃችን ይታወሳል።

ሆኖም ግን መዝጋቢዎችና የመመዝገቢያ ኮምፒውተር በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ቢዚ በመሆን እና በተለያዩ ምክንያቶች የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ምዝገባ የተጓተተ መሆኑን የተረዳን ስለሆነ ምዝገባው እስከ መጋቢት 25/2018 የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን ሲስተሙ ለሌላ ስራ ዝግ ስለሚሆን ከተባለው ጊዜ ውጭ ለሚፈጠር ችግር የወረዳው ፈተና ክፍል ኃላፊነት የምትወስዱ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።

ያልተመዘገበ ተማሪ አይፈተንም!
ክልል ትምህርት ቢሮ
መጋቢት 20/2018

23/03/2026

Address

Gambella
Gambela
35

Opening Hours

Monday 07:45 - 05:30
Tuesday 07:45 - 05:30
Wednesday 07:45 - 05:30
Thursday 07:45 - 05:30
Friday 07:45 - 05:30

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gambella Region Education Bureau Page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share