Abacus Computer Technology

Abacus Computer Technology አዳዲስ መረጃዎችን እና የቴክኖሎጅ ትምህርቶችን አጠር ባለ አቀራረብ እዚህ ያገኛሉ

13/05/2026

"የሴቶችን ፖለቲካዊ፤ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸው በቀጣይ ዓመታት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሴቶች በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግናን ለመምረጥ
ሊዘጋጁ ይገባል"

ወ/ሮ አክሊለ ዞማነህ
የምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ

በምዕራብ ጎጃም ዞን በተለያዩ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ "የሴቶች ተሳትፎ ለተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል ለ7ኛው አገራዊ ምርጫ የሴቶች ክንፍ አባላትና ደጋፊዎች የምርጫ ቅስቀሳና እጩ ትውውቅ መድረክ በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።

የዞኑ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ አክሊለ ዞማነህ በተለያዩ ወረዳዎች የተካሄዱ የሴቶች ክንፍ አባላትና ደጋፊዎች የምርጫ ቅስቀሳና ምልክት ትውውቅ ሁነቶች ፍሬያማ እንዲሆኑ የሴቶችን ፖለቲካዊ፤ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸው በቀጣይ በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሴቶች በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግናን ለመምረጥ ሊዘጋጁ ይገባል ብለዋል።

መንግስት በተለያዩ ደረጃ የሚገኙ ሴቶች በተለያዩ የፖለቲካ አመራር ሰጭነት ትልቅ ኃላፊነት እንዲያገኙ ተደርጓል።

የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በሌማት ትሩፋትና በከተማ ግብርና የልማት ስራዎች በማሰማራት ሀብት እንዲፈጥሩ መደረጉም ተጠቅሷል።

ብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሰራ ያለ መሆኑን ተገልጿል።

በብልጽግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት በሀገራችን ስር የሰደዱና የቅዩ ችግሮችን በመፍታት ወደ ብልጽግና ማማ ለመሻገር በርካታ እርምጃዎችን እየወሰደ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ እየተጓዘ መሆኑም ገልጸዋል።

ብልጽግና ፓርቲ በማህበራዊ፣በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካው መስኮች የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን በማድረግ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋገር ሴቶች በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ተገጸዋል።

25/07/2024
12/07/2023
https://youtu.be/D56eORgOxsU
06/07/2023

https://youtu.be/D56eORgOxsU

Computer Technology flash Drive usb installerBoot flash drive using universal usb installer for windows operating system iso files ...

04/07/2023

ድረ-ገፆዎን ከጥቃት መከላከል የሚያስችሉ መንገዶች የትኞቹ ናቸው?

የተቋማት ብሎም በግለሰብ ደረጃ የተለያየ ግልጋሎት የሚሰጡ ድረ‐ገጾች ለመረጃ ማዝባሪዎች የጥቃት ሊላማ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህን ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያስችሉ የመከላከያ መንገዶች ጥቂቶቹ፦

 ሶፍትዌሮችን ያዘምኑ (Patch-Update)

የሰርቨር ኦፕሬቲንግ ሲስተም፣ የደህንነት መጠበቂያዎች፣ ዌብሳይቱ ላይ የሚከፈቱ ሌሎች ማናቸውም የሶስተኛ አካል ሶፍትዌሮች፣ የደህንነት ማዘመኛዎች ወይም ጥገናዎች (Patches) በየግዜው ማዘመን ።

 የዶሜይን (Domain) ደህንነትን ያስጠብቁ

o ለሁሉም Domain የ Domain Name System (DNS) ምዝገባን ያረጋግጡ፡፡
o በ DNS እና Domain ምዝገባ በዘፈቀደ (default) የተሰጡ የይለፍ ቃሎችን ይለውጡ፡፡
o ዘርፈ-ብዙ የማንነት ማረጋገጫን (Multi-Factor Authentication) ይጠቀሙ፡፡

 የተጠቃሚ አካውንቶዎን ደህንነት ያስጠብቁ

o ለተጠቃሚዎች የተሰጡ አላስፈላጊ አካውንቶችንና ፍቃዶችን ያጥፉ፡፡
o ሁሉንም ዘፈቀዳዊ (default) የተጠቃሚ ስምና የይለፍ ቃል ያጥፉ (Default User Names and Passwords)

 ክፍተቶችን ይጠግኑ

o ወሳኝና ከፍተኛ ክፍተቶችን በየ15 እና 30 ቀኑ ይሙሉ/ይጠግኑ፤
o የማስተካከያ (Configuration) ክፍተቶችንም ይዳሱ፤ ክፍተቶችን በራሱ እንዲሞላ የሚያስችል ማዘመኛ ይጠቀሙ (Automatic updates)
o ግልጋሎት የማይሰጡ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞችን፣ መተግበሪያዎችን እና መገልገያዎችን (Hardware) በአዲስ ይተኩ፡፡

 በዝውውር ላይ የሚገኝን የመረጃ ደህንነት ያስጠብቁ

o የድረ-ገፅ ተገልጋዮች ግላዊነታቸው እንዲጠበቅ ምስጠራን ይጠቀሙ፡፡
o በተጠቃሚዎችና በድረ-ገፁ መካከል የሚደረጉ ግንኙነቶችን ለመመስጠር ሁሌም HTTPS ይጠቀሙ፤ ከተቻለ ደግሞ HSTS ይጠቀሙ፡፡

 ቅጂ/ቀሪ ይያዙ

o ወሳኝ መረጃዎችንና የስርዓት ማስተካከያዎችን (System Configurations) ሁሌም አውቶማቲክ ቅጂ መያዥያን ይጠቀሙ፡፡
o የቀሪ መያዣ ሚድያዎን ደህንነቱ በተጠበቀ እና የመይገባው አካል እጅ እንዳይገባ አርቆ ማስቀመጥ ፡፡
o የጠፉትን መረጃዎች የማስመለስ ልምምድ ያድርጉ (Disaster Recovery Scenarios)

 የዌብ መተግበሪያዎችን ደህንነት ያስጠብቁ

o የድረ-ገፅ ኮድ እና ሲስተም ላይ መደበኛና ድንገተኛ የደህንነት ፍተሻ ያድርጉ፤
o በመደበኛነት የድረ-ገፁን ጠቅላላ ሁኔታ ኦዲት በማድረግ ያልተፈቀዱ ግንኙነቶችን/ የደህንነት ክስተቶችን ይለዩ፡፡
o በጣም ወሳኝ የዌብ መተግበሪያ የደህንነት ስጋቶችነ በመለየት መፍትሄ ያብጁ፤ ከዚያም ወደ አነስተኛ ወሳኝነት ወዳላቸው ስጋቶች ይቀጥሉ፡፡

 የዌብ ሰርቨሮችን ደህንነት ያስጠብቁ

o የደህንነት ዝርዝር ተግባራተን (Security Checklist) ይጠቀሙ:: መዋቅሮችን (Configurations) ለያንዳንዱ አፕሊኬሽን በተቀመጠው የደህንነት ዝርዝር መሰረት ኦዲት በማድረግ ያጠንክሯቸው፡፡
o የአፕሊኬሽን መፍቀጃን (Application Whitelisting) ይጠቀሙ፤ እንዲሁም ለስራዎ የማይጠቀሙባቸውን የአፕሊኬሽኖች ግልጋሎት (Features) ያጥፉ፡፡
o ኔትወርኮችን ይከፋፍሉ (Network Segmentation and Segregation)
o የመረጃ ሀብትዎን ይወቁ፤ ደህንነቱንም ያስጠብቁ፡፡ ዌብ ሰርቨር ላይ ሊገኝ የማይገባውን ሚስጢራዊ መረጃዎን በማንሳት ለህዝብ እይታ እንዳይጋለጥ ደህንነቱን ያስጠብቁ፡፡

 ደህንነቱ የተጠበቀ የድረ-ገጽ አስተናጋጅ (Host) ይጠቀሙ

ታማኝና ደህንነቱ የተጠበቀ (ቢቻል ቀጣይነት ያለው ቴክኒካል ድጋፍ እንደ ፋየርዎል፣ SSL ሰርቲፊኬቶች፣ የርቀት ቅጂ ማስቀመጫ(back up)፣ ኔትዎርክ ቁጥጥር ወዘተ. የሚሰጥ) የድረ-ገፅ አስተናጋጅ ይጠቀሙ፡፡

https://youtu.be/VOcKHtjr2xw
30/06/2023

https://youtu.be/VOcKHtjr2xw

Computer Technology #ፈቃድ እድሳት License Renewal ፈቃድ እድሳት ሊጀመር ትንሽ ቀናት ቀሩት 2016 ዓ.ም የ 2016 ዓ.ም ፈቃድ እድሳት ሊጀመር ትንሽ ቀናት ቀሩት ማንኛዉም ነጋዴ ከሀምሌ አንድ ጀም...

27/06/2023

✍️ሕንጸተ ቤተ ክርስቲያን

ሰኔ 20 ቀን 2015 ዓ.ም

❤በመጽሐፈ ስንክሳር እንደ ተመዘገበልን ሰኔ ፳ ቀን በኬልቄዶን አውራጃ በቂሣርያ አገር የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ያለ እንጨት፣ ያለ ጭቃና ያለ ውኀ በሦስት ድንጋዮች በተወደደ ልጇ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የታነጸበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት በቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ ከሚከብሩ ከእመቤታችን በዓላት አንደኛው ሲኾን ታሪኩንም በአጭሩ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፤

❤ጌታችን በዐረገ በስምንተኛው ዓመት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ወደ ፊልጵስዩስ ገብተው በክርስቶስ ስም አሳምነው ብዙ አሕዛብን ካጠመቁ በኋላ ቤተ ክርስቲያን ሊሠሩላቸው ወደዱ፡፡ በዚህ ጊዜ ርእሰ ሐዋርያት እያለ እኛ መሥራት አይገባንም ብለው በሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት ላኩበት፡፡ እርሱም ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር መጥቶ ከቅዱስ ጳውሎስ እና ቅዱስ በርናባስ ጋር በኢየሩሳሌም ተገናኙ፡፡

❤በዚያም በአንድነት ሱባዔ ይዘው ከቆዩ በኋላ ጌታችን የሞቱትን አስነሥቶ፣ ያሉትንም ጠርቶ ቅዱሳን ሐዋርያትን በፊልጵስዩስ አገር ሰብስቦ ‹‹በእናቴ በድንግል ማርያም ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚሠራዉን የአብያተ ክርስቲያናት ሥራ ላሳያችሁ፤ ሥርዓቱንም ላስተምራችሁ ሰብስቤአችኋለሁ›› ብሎ ወደ ምሥራቅ ይዟቸው ወጣ፡፡ በዚያ ሥፍራ የነበሩትን ሦስት ድንጋዮችንም የተራራቁትን አቀራርቦ፣ ጥቃቅኑን ታላላቅ አድርጎ ቁመቱን በ፳፬፤ ወርዱን በ፲፪ ክንድ ለክቶ ለቅዱሳን ሐዋርያት ሰጣቸው፡፡

❤ከዚህ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት ሰም እሳት ሲያገኘው እንዲለመልም፣ ድንጋዩ በእጃቸው ላይ እየተሳበላቸው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ሠርተው ፈጽመዉታል፡፡ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ የተሠራዉም ጌታችን በዐረገ በ፲፱ኛው፤ እመቤታችን በዐረገች በ፬ኛው ዓመት ሰኔ ፳ ቀን ሲኾን፣ በ፳፩ኛው ቀን (በማግሥቱ) ኅብስት ሰማያዊ፣ ጽዋዕ ሰማያዊ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ወረደ፡፡ ጌታችንም ከእመቤታችን ጋር ከሰማየ ሰማያት መጥቶ እመቤታችንን ታቦት፤ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ ‹‹እምይእዜሰ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ፤ ከዛሬ ጀምሮ እናንተም እንደዚህ አድርጉ›› ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡

❤ ይህ ታሪክ ብዙ ምሳሌዎች አሉት፡፡ ይኸውም፡- የሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ቁመት በነገሥታት ዘመን የነበሩ የ፳፬ቱ ነቢያት፤ አንድም የ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ አምሳል ሲኾን፣ ወርዱ ደግሞ የ፲፪ቱ ሐዋርያት ምሳሌ ነው፡፡ ሦስቱ ድንጋዮች የሥላሴ አምሳል ሲኾኑ፣ ከታች አቀማመጣቸው ሦስት፤ ከላይ ሕንጻቸው አንድ መኾኑ የሥላሴን ሦስትነትና አንድነት ያመለክታል፡፡ የሠሩትም ሦስት ክፍል አድርገው ሲኾን፣ ይህም የመጀመሪያው የታቦተ አዳም፤ ሁለተኛው የታቦተ ሙሴ፤ ሦስተኛው የታቦተ ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡

❤ዳግመኛም የሦስቱ ዓለማት ማለትም የመጀመሪያው የጽርሐ አርያም፣ ሁለተኛው የኢዮር፣ ሦስተኛው የጠፈር ምሳሌ ነው፡፡
አንድም መጀመሪያው የኤረር፣ ሁለተኛው የራማ፣ ሦስተኛው የኢዮር አምሳል ነው፡፡ በኤረር፡- መላእክት፣ መኳንንት፣ ሊቃናት፤ በራማ፡- ሥልጣናት፣ መናብርት፣ አርባብ፤ በኢዮር፡- ኃይላት፣ ኪሩቤል፣ ሱራፌል ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ዘጠኙ ነገደ መላእክት የዘጠኙ መዓርጋተ ቤተ ክርስቲያን (መዓርጋተ ክህነት) አምሳል ሲኾኑ፣ ይኸውም መላእክት – የመዘምራን፤ መኳንንት – የአናጕንስጢሳውያን፤ ሊቃናት – የንፍቀ ዲያቆናት፤ ሥልጣናት – የዲያቆናት፤ መናብርት – የቀሳውስት፤ አርባብ – የቆሞሳት፤ ኃይላት – የኤጲስ ቆጶሳት፤ ሱራፌል – የጳጳሳት፤ ኪሩቤል – የሊቃነ ጳጳሳት አምሳሎች ናቸው፡፡

❤ይህም በታች (በምድር) የሚኖሩ ደቂቀ አዳም ከቅዱሳን በቀር ወደ ላይ (ወደ ሰማይ) መውጣት እንደማይቻላቸው፣ ከመዘምራን እስከ ጳጳሳት ድረስ ያሉ ካህናትም ከእነርሱ በላይ ያሉትን መዓርግ መሥራት (መፈጸም) እንደማይቻላቸው ያጠይቃል፡፡ እንደዚሁም በላይ የሚኖሩ መላእክት ወደ ታች መውረድ እንደሚቻላቸው ሊቃነ ጳጳሳትም ከእነርሱ በታች ያሉ ካህናትን ተልእኮ መፈጸም (መሥራት) እንደሚቻላቸው ያስረዳል፡፡

❤በጽርሐ አርያም መንበረ ብርሃን (የብርሃን መንበር)፤ ታቦተ ብርሃን (የብርሃን ታቦት)፤ መንጦላዕተ ብርሃን (የብርሃን መጋረጃ)፤ እንደዚሁም ፬ ፀወርተ መንበር (መንበሩን የሚሸከሙ)፤ ፳፬ አጠንተ መንበር (መንበሩን የሚያጥኑ) መላእክት አሉ፡፡ ጽርሐ አርያም – የመቅደስ፤ መንበረ ብርሃን – የመንበር፤ መንጦላዕተ ብርሃን – የቤተ መቅደሱ መጋረጃ፤ ፬ቱ ፀወርተ መንበር – የ፬ቱ ሊቃነ ጳጳሳት ወይም የመንበሩ እግሮች፤ ፳፬ቱ አጠንተ መንበር – የጳጳሳት (የኤጲስ ቆጶሳት) አምሳሎች ናቸው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

https://youtu.be/EGoTiAjObt0
26/06/2023

https://youtu.be/EGoTiAjObt0

Computer Technology Editorhow to use youcut video editor application /Tutorial ላይክ፣ሼር፣ኮሜንት እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቻናሉን ይቀላቀሉ፡፡ስለመጣችሁ እና...

https://youtu.be/1WnRf7r61ec
23/06/2023

https://youtu.be/1WnRf7r61ec

Computer Technology yard to use Stream yard YouTube Live streaming Tutorial ላይክ፣ሼር፣ኮሜንት እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቻናሉን ይቀላቀሉ፡፡ስለመጣችሁ እናመሰግ...

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።ግንቦት 21 አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላ...
29/05/2023

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።
ግንቦት 21 አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ በግልጽ የታየችበት ዕለት ነው፡፡
ደብረ ምጥማቅ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በግልጽ ስለመታየቷና ታላቅ ተአምር ስለማድረጓ፡- ጌታችን ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮጵያ በተሰደደ ጊዜ ከእመቤታችን፣ ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር፡፡ ቦታውን ባርኮ ለድንግል እናቱ ‹‹ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን›› ብሎ ቃልኪዳን ገብቶላት ነበር፡፡ በዚህም መሠረት ደብረ ምጥማቅ ገዳም ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ከሆነ በኋላ እመቤታችን በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን አእላፍ መላእክትን ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት በመሞጣት ለሕዝበ ክርስቲያኑም ለአሕዛብ ጭምር በመገለጥ ለ5 ቀናት በግልጽ ትታያቸው ነበር፡፡ ‹‹በዚህች ቀን በግብፅ አገር ደብረ ምጥማቅ በምትባል በተሰራች ቤተ ክርስቲያን ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ከሰሜን እስከ ደቡብ ያሉ ሰዎች ይሰበሰባሉ ከያገሩም ሁሉ ይመጣሉ፡፡ እነዚህም ሁሉ ሠቀላ ሠርተው ድንኳን ተክለው አጎበር ጥለው ይከትማሉ፡፡ ከ21 ቀን ጀምረው እስከ 25 ቀን ድረስ በፍጹም ደስታ በፍጹም ክብር የድንግልን በዓሏን ማክበር ይጀምራሉ፤ ድንግልም ከግንቦት 21 ቀን ጀምራ እስከ 25 ቀን ድረስ ሳታቋርጥ በነዚህ በ5ቱ ዕለታት ከመላእክት ከጻድቃን ከሰማዕታት ጋር ትገለጽላቸው ነበር፡፡ እነርሱም በፍጹም ክብር በፍጹም ደስታ በዓሏን ያከብራሉ፡፡ ክርስቲያኑም እስላሙም በገሃድ ተገልጻ ያዩዋት ነበር›› ይላል ተአምረ ማርያም፡፡
እመቤታችን በዙሪያዋ የመላእክት ሠራዊት መላእክት አለቆችም በየማዕረጋቸው ክንፋቸውን ዘርግተው ይቆማሉ፣ ይጋርዷታል፡፡ ሱራፌልም ማዕጠንታቸውን ይዘው ለንግሥናዋ ገናናነት ይሰግዳሉ፡፡ በየስግደታቸውም እንዲህ እያሉ ያመሰግኗታል፡- ‹‹አብ በሰማይ ሆኖ ተመለከተ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም አንድ ልጁንም ልኮት እርሱም ከአንቺ ሰው ሆነ፡፡›› ሁለተኛም ሰማዕታት በየማዕረጋቸው ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻው ተቀምጠው እየመጡ መጀመሪያ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአምባላይ ፈረሱ ወርዶ ይሰግድላታል፡፡ እንዲሁም ባልንጀሮቹ ሰማዕታት መጥተው ይሰግዱላታል፡፡ ከእርሱ በኋላ የሚመጣው በዱሪ ፈረስ የሚቀመጥ ቅዱስ መርቆሬዎስ ነው፡፡ ከዚህም በኋላ ሰማዕታት ሁሉ በመከታተል መጥተው ይሰግዱላታል፡፡ ዳግመኛም ደግሞ የጻድቃን አንድነታቸው መጥተው በፊቷ ሰግደው ይመላለሳሉ፡፡ ሄሮድስ ያስገደላቸው 144,000 ሺህ የቤተልሔም ሕጻናት ከዓለቃቸው ከቅዱስ ቂርቆስ ጋር መጥተው ይሰግዱላታል፡፡ በፊቷም እየዘለሉ አንዱ በአንዱ ላይ እየዘለለ በመተቃቀፍም ይጫወታሉ፡፡ በደብረ ምጥማቅ የተሰበሰቡትም ሁሉ ክርስቲያኑም እስላሙም ሁሉ ይህንን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ እጅግ ሐሴት ያደርጋሉ፡፡ እናት አባት የሞቱበት ቢኖር ወይም ከዘመዶቹም ቢሆን ወላዲተ አምላክን ‹‹እመቤቴ ሆይ ዕገሌን… አሳይኝ›› ብሎ በሚለምናት ጊዜ ቀድሞ በነበረበት መልኩ ያንጊዜ ታመጣዋለች፡፡ የብርሃን እናቱ እመቤታችን መሐመድንም ከሲኦል አውጥታ አሳይታቸዋለች፡፡ (መጨረሻ ላይ በደንብ እናየዋለን)
ደግሞም ሕዝቡ ሁሉ መሀረባቸውን ወደላይ ይወረውሩላታል እመቤታችንም የወደደችውን በእጇ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች፤ እነርሱም ለበረከት በየጥቂቱ ይካፈሉታል፡፡ በእንዲህም ዓይነት ሁኔታ 5 ቀን ሙሉ እስላሙም ክርስቲያኑም አረማውያኑም በገሃድ ተመለከቷት፡፡ ወደቤታቸውም ለመሄድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል፤ እመቤታችንም ትባርካቸውና ሄደው እንደገና ይመለሳሉ፡፡ 5ቱ ዕለታትም ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል፡፡ እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ዐርጋለች፡፡
አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ መሐመድንም ከሲኦል አውጥታ እንዳሳየቻቸውና የአሕዛብንም የሐሰት መንፈስ እንዳጋለጠችው ተአምሯ ላይ ተጽፏል፡፡ እመቤታችን በረድኤትና በቸርነት በደብረ ምጥማቅ ተገልጻላቸው ሳለ የሚያምነው ክርስቲያኑም የማያምነው አሕዛቡም ሁሉም በገሃድ ያዩዋት ነበር፡፡ ጥያቄያቸውንም ሁሉ ታሟላላቸው ነበር፡፡ ግማሹ ዳዊትን አሳይን ሲሏት ከነበገናው አምጥታ ታሳያቸዋለች፤ ዕዝራን አሳይን ሲሏት ከነመሰንቆው አምጥታ ታሳያቸዋለች፤ጊዮርጊስን አሳይን ሲሏት ከነፀዓዳ ፈረሱ አምጥታ ታሳያቸዋለች… ሁሉንም እንደየጥያቄዎቻቸው ታስተናግዳቸው ነበር፡፡ ከመካከላቸውም አንዱ ካህን ‹‹እመቤቴ ሆይ! እነዚህ ሙስሊሞች ‹መሐመድ ነቢይ ነው› እያሉ ይዘበዝቡናልና እስቲ እርሱን አሳይን›› ይሏታል፡፡ ያን ጊዜም የብርሃን እናቱ እመቤታችን መሐመድን ከሲኦል አውጥታ አሳይታቸዋለች፡፡ እርሱም እንደከሰል ጠቁሮ በግመል ላይ ተቀምጦ ነበር፡፡ የመሐመድ ብልት ከግመል አንገት ጋር በእሳት ሰንሰለት ታስሮ እርሱም ከሰል መስሎ በግመሏ ላይ ተቀምጦ አጋንንት ከፊት ከኋላ፣ ከቀኝ ከግራ በእሳት አለንጋ እየገረፉትና እያዳፉት ከሲኦል አውጥተው የተሰበሰበው ሕዝብ ሁሉ እንዲመለከተው አደረጉት፡፡ የተሰበሰበው ሕዝበ ክርስቲያንም እመቤታችን ባሳየቻቸው ተአምር እጅግ ተደንቀው ለክብሯ እየሰገዱ በእንባ አመሰገኗት፡፡ በቦታው የነበሩ ሙስሊሞችም ወዲያው በክርስቶስና በድንግል እናቱ እንዳመኑ ተአምረ ማርያም ላይ በሰፊው ተጽፏል፡፡
አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን ለ3 ቀናት ማለትም ከግንቦት 21-23 ድረስ በእንደዚህ ዓይነት መልኩ በደብረ ምጥማቅ በገሃድ ተገልጻ ታላቅ ተአምር ያደረገችበት ዕለት ነው፡፡ ለተሰበሰቡ ምእመናን ሁሉ በግልጽ በመታየት ትነጋገራቸው እንደነበረ ሁሉ ዛሬም በረድኤት በቸርነቷ ልጆቿ ትጎበኘን ዘንድ መልካም ፈቃዷ ይሁንልን። ልጇ አምላካችን በአማላጅነቷ ይማረን፡፡
* ሌሎች በዕለቱ የሚታሰቡ ቅዱሳን
ዳግመኛም በዚኽች ዕለት እንግዶች መጥተውባቸው ሳለ ርግቦችን አብስለው ምግብ ሠርተው ቢያቀረቡላቸው እንግዶቹ እምቢ ቢሏቸው የርግቦቹ ሥጋ ላይ አማትበው እፍ ብለው ርግቦቹን ክንፍ አውጥተው እንዲበሩ ያደረጓቸው ሶርያዊው አቡነ አሮን ዕረፍታቸው ነው፡፡
ገሃነመ እሳት በማሰብ በዝሙትም ላለመውደቅ ብለው ሰውነታቸውን የሚነድ እሳት ውስጥ በመጨመር ዘማዊቷን ሴት ለንስሓ ያበቋት አቡነ መርትያኖስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
* ነቢዩ ቅዱስ አሞጽ መታሰቢያ በዓሉ ነው፡፡
* አቡነ አሮን ሶርያዊ
በዚችም ዕለት ከልጅነቱ ጀምሮ ተጋዳይ የሆነ አባ አሮን ሶርያዊ አረፈ።
ፈውስ የመስጠትና ታላላቅ ተአምራትን የማድረግ ሀብት የተሰጣቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ እንግዶች የሆኑ መነኮሳት ወደ እሳቸው በመጡ ሰዓት ርግቦችን አብስለው ይመግቡ ነበርና አንድ ቀን እንዲሁ አድርገው ርግቦችን አብስለው ለእንግዶቹ መነኮሳት ቢያቀርቡላቸው መነኮሳቱ ግን "ሥጋ አንበላም" አሏቸው፡፡ አቡነ አሮንም አብስለው ሠርተው ባቀረቡት የርግቦቹ ሥጋ ላይ አማትበው እፍ ብለው ርግቦቹን ክንፍ አውጥተው እንዲበሩ አድርገዋቸዋል፡፡
አቡነ አሮን በተራራ ላይ ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ውኃው ከተራራው ይርቅ ነበርና አባታችን በመስቀል ምልክት አማትበው ውኃውን ስበው ከተራራው ላይ አውጥተውታል፡፡ ሰይጣን ወደ በዓታቸው ተመሳስሎ ገብቶ በላያቸው ላይ ‹‹እጅግ ትልቅ ድንጋይ ጥዬ እገድላቸዋለሁ›› ብሎ አስቦ በዓታቸው ውስጥ ገባ፡፡ እርሳቸውም አስቀድመው ዐውቀውት ሳለ ግን እንዳላወቁ ሆነው ‹‹እንግዳ ነህን ና ወደ ውስጥ ግባ›› ብለው ካስገቡት በኋላ በእሳቸው ላይ እጥላዋለሁ ብሎ ያሰበውን እጅግ ትልቅ ድንጋይ በላዩ ላይ ጫኑበትና ዙሪያን ደፍነው እንዳይወጣ በመስቀል አማትበው ዘግተውበት ገድለውታል፡፡ አባታችን አገረ ገዥው መሞቱን ሰምተው ሄደው በጸሎታቸው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ውኃ የሚቀዱባቸው አራት ትላልቅ እንስራዎችን በአንበሳ እየጫኑ 10 ዓመት ገዳማትን አገልግለዋል፡፡ ጻድቁ በመጨረሻ ከጌታችን ታላቅ ቃልኪዳን ተቀብለው ግንቦት 21 በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረች ጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
* ቅዱስ አባ መርትያኖስ
ይህም ታላቅ ጻዲቅ ከልጅነቱ ጀምሮ በቅድስና ሕይወት ያጌጠ ነበር፡፡ መንኩሶ ሐመረ ኖኅ ወደምትባል ገዳም ገብቶ በታላቅ ተጋድሎ እየተጋደለ 67 ዓመት ኖረ፡፡ ምግባር ሃይማኖቱ፣ ገድሉና ትሩፋቱ በቦታው ሁሉ በተሰማ ጊዜ እነሆ አንዲት በክፉ ሥራዋና በዝሙቷ የታወቀች ኃጢአተኛ አመንዝራ ሴት ቅድስናውን ሰማች፡፡ እርሷም መልኳ እጅግ ያማረ ነበር፡፡ ጽድቁንና ቅድስናውን በመናገር የሚያመሰግኑትን ሰዎችም እንዲህ አለቻቸው፡- ‹‹እናንተ ታመሰግኑታላችሁ እርሱ የሚኖረው በዱር ነው የሴት ፊት አይቶ አያውቅም እኔን ቢያይ ግን ድንግልናውን አጥፍቼ ቅድስናውን አረክስበታለሁ›› አለቻቸው፡፡ ቅድስናውን የሚያውቁት ሰዎችም በፍጹም እርሱን በፈተና መጣል እንደማትችል ነገሯት፡፡ በእነርሱና በዚህች ዘማ ሴት መካከል ክርክር በሆነ ጊዜ አባ መርትያኖስን ፈትናው በኃጢአት ከጣለችው ከፍተኛ ገንዘብ ሊሰጧት ተስማሙ፡፡
ከዚህም በኋላ ያች ዘማ ሴት የምንዝር ጌጦቿን ሰብስባ ተጋጊጣ ልብሶቿንና ሽቱዎቿን ይዛ እጅግ የሚያምረውን መልኳን ይበልጥ አስውባ ተከናንባ ወደ አባ መርትያኖስ በዓት አጠገብ ሄዳ ቆየች፡፡ ሲመሽላትም የበዓቱን ደጃፍ አንኳኩታ ‹‹አራዊት እንዲበሉኝ በውጭ አትተወኝ እኔ መጻተኛ ነኝና መንገድንም ተሳስቼ ወደዚህ ደረስኩ›› አለችው፡፡ አባ መርትያኖስም በልቡ አሰበ፡፡ ‹‹በውጭ ብተዋት አራዊት ይበሏታል ባስገባትም ስለእርሷ ጦር በእኔ ላይ ይነሳብኛል›› ብሎ አሰበ፡፡ ‹‹በአውሬ ከምትበላ አስገብቻት ፈተናውን ብቋቋም ይሻላል›› ብሎ አስገብቷት እርሱ ትቷት ፈቀቅ አለ፡፡ ከዚህም በኋላ እርሷ አብሯት እንዲተኛ ለማድረግ ስትል ‹‹ከዚህ ማንም አያየንም›› በማለት የዝሙትን ሀሳብ አቀረበችለት፡፡ አባ መርትያኖስም የሰይጣን ማጥመጃው እንደሆነች ዐውቆ ‹‹ትንሽ ታገሺኝ›› አላትና እንጨት ሰብስቦ ታላቅ እሳት አነደደና እያየችው እግሩን ከእሳቱ ውስጥ ጨመረው፡፡ ነፍሱንም ‹‹የሲኦልን እሳት የምትችይ ከሆንሽ እነሆ ኃጢአትን ሥሪ›› አላት፡፡ ያችም ዘማ ሴት ይህንን በተመለከተች ጊዜ እጅግ ደነገጠች፡፡ አባ መርትያኖስንም ከእሳቱ ውስጥ ጎትታ አወጣችው፡፡ ልቧም ወደ ንስሓ ተመለሰ፡፡ የምንዝር ጌጦቿንና ልብሶቿን ከላይዋ ላይ አውልቃ ጣለችና ለአባ መርትያኖስ ሰግዳ የነፍሷን መንገድ እንዲመራት ለመነችው፡፡ እርሱም የዓለም ፍላጎት ሁሉ ኃላፊ እንደሆነ ሲያስተምራት አደረ፡፡ በቅዱስ ወንጌል ላይ ‹‹ዓለምን መውደድ ለእግዚአብሔር ጥል እንደሆነ አታውቁምን? እንግዲህ የዓለም ወዳጅ ሊሆን የሚፈቅድ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኗል፡፡›› የሚለውን እየጠቀሰ አስተማራት፡፡ ያዕ 2፡4፡፡ የእግዚአብሔር ወዳጅ አለመሆን በሥጋም ሆነ በነፍስ እጅግ ትልቁ የሕይወት ኪሳራ ነው፤ የእግዚአብሔር ጠላት መሆን ግን ምንኛ የሚያስጨንቅ ነገር ነው! ዳግመኛም ጌታችንም ‹‹…ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም፡፡ ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል፡፡›› ያለውን እየጠቀሰ አስተማራት፡፡ ማር 8፡34-36፣ ማቴ 10፡39፣ 1ኛ ዮሐ 2፡16፡፡
ከዚህም በኋላ እርሷም ወደ ዓለም ላለመመለስ በፍጹም ልቡናዋ ቆርጣ ንስሓ ገባችና አባ መርትያኖስ ወደ ሴቶች ገዳም ወሰዳትና ለእመ ምኔቷ አደራ ሰጣት፡፡ ከዚህ በኋላ እርሷ በገድል ተጠምዳ እግዚአብሔርን እያገለገለች ደስ አሰኘችው፡፡ የመፈወስ ሀብትም አድሮባት ብዙ ሕመምተኞችን በጌታችን ስም የምትፈውስ ሆነች፡፡ እስከ ሽምግልናዋም ዕድሜ ድረስ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ስታገለግል ኖረች፡፡
አባ መርትያኖስም ሌላ ሴት እንዳትመጣበት ፈርቶ በባሕር መካከል ወዳለች ደሴት ገብቶ በዚያ ቢኖር በአንድ ወቅት መርከብ ተሰብራ አንዲት ሴት በመርከቧ ስባሪ ተንጠላጥላ ማዕበሉ እያናወጠ አባ መርትያኖስ ያለበት በዓት ድረስ ፈቃደ እግዚአብሔር አደረሳት፡፡ እርሱም እጅግ ደንግጦ እርሷንም እንዲሁ አስተምሮ አመንኩሶ ደሴቲቱን ለእርሷ ጥሎላት ወደ ሌላ ሀገር ሄደ፡፡ ከዚህም በኋላ በአንድ ቦታ እንዳይቀመጥ አስቦ በ108 የተለያዩ ሀገሮች እየዞረ በታላቅ ተጋድሎ የሚኖር ሆነ፡፡ የዕረፍቱም ጊዜ እንደቀረበ ዐውቆ በበዓቱ ውስጥ ራሱን እስረኛ አደረገ፡፡ ኤጲስቆጶሱንም አስጠርቶ ገድሉን ሁሉ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ነገረው፡፡ ኤጲስቆጶሱንም ከጸጋው ገናናነት የተነሣ አደነቀ፡፡ ወደ እርሱ ከመምጣቱ በፊት የታዘዘ መልአክ ለኤጲስቆጶሱ ተገልጦለት ስለ አባ መርትያኖስ ሥጋ እንዲያስብ ነግሮት ነበርና፡፡ ጌታችንም ለአባ መርትያኖስ ቃልኪዳን ከገባለት በኋላ በሰላም ዐርፎ ኤጲስቆጶሱ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ሰብስቦ በክብር ገንዞ ቀበረው፡፡ ከሥጋውም ታላላቅ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረች ጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ቅዱስ አሞጽ ነቢይ
በዚችም ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ አሞጽ ነቢይ መታሰቢያው ነው። አሞጽ ማለት "እግዚአብሔር ጽኑዓ ባሕርይ ነው: አንድም እግዚአብሔር ያጸናል::" ማለት ነው:: "ተወዳጅ ሰው" ተብሎም ይተረጐማል:: የነበረውም ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በስምንት መቶ ዓመት ሲሆን አባቱ ቴና እናቱ ሜስታ ይባላሉ:: ትውልዱም ከነገደ ስምዖን ነው:: በትውፊት ይህ ነቢይ የነቢዩ ኢሳይያስ አባት ነው የሚሉ ቢኖሩም ሁለቱ አሞጾች የተለያዩ መሆናቸውን ሊቃውንት ይናገራሉ::
ይህ ዕውነተኛ ነቢይ በእስራኤል ነገሥታት በኢዮአስና በኦዝያ ዘመን አስተማረ የእስራኤልንም ልጆች የእስራኤልንና የይሁዳንም ነገሥታት ይገሥጻቸው ነበር።
ስለ ክብር ባለቤት ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ ስለመቀበሉ በዚያችም ቀን ስለ ፀሐይ መጨለም ከዚያም በኋላ እስራኤልን ስለሚደርስባቸው መከራ፣ ኀዘን፣ ልቅሶ፣ ረድኤትም እንደሚአጡ፣ የእግዚአብሔርንም ቃል መስማትን ከማጣት የተነሣ እንደሚራቡና እንደሚጠሙ። በሀገሩ ሁሉ በአሕዛብም መካከል እንደሚበተኑ አሕዛብም እንደ አጃ ሸክሽከው እንደሚአጓልቧቸው ትንቢትን ተናገረ ትንቢቱም በላያቸው ተፈጸመ።
ቅዱሱ ነቢይ ወገኖቹን አብዝቶ ይገስጻቸው ነበር፤ ስለኃጢአታቸውና ስለ ክፉ ሥራቸው፣ ስለ ዘለፋቸው እነርሱ እንደ ገደሉት ተነገረ። የትንቢቱም ዘመን ከጌታችን ሥጋዌ በፊት በስምንት መቶ ዓመት ነው ። በረከቱ በሁላችንም ይደር።
ምንጭ፦ የግንቦት ❷❶ ስንክሳር

Address

Finote Selam
6180

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abacus Computer Technology posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Abacus Computer Technology:

Shortcuts

Share