Dire-Dawa University

Dire-Dawa University Dire-Dawa University aspires to be a premium choice in Ethiopia and among the top ten Applied Science Universities in Africa by 2030.

በአርቲስት ኡስማዮ ሙሳ ህይወት ታሪክ ዙሪያ የተፃፈ መፅሐፍ ዛሬ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተመረቀየታዋቂውን አርቲስት ኡስማዮ ሙሳን የህይወት ታሪክ የሚያስቃኝ እና በአርቲስቱ የመጀመሪያ ልጅ አርቲ...
22/08/2026

በአርቲስት ኡስማዮ ሙሳ ህይወት ታሪክ ዙሪያ የተፃፈ መፅሐፍ ዛሬ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተመረቀ

የታዋቂውን አርቲስት ኡስማዮ ሙሳን የህይወት ታሪክ የሚያስቃኝ እና በአርቲስቱ የመጀመሪያ ልጅ አርቲስት ሳርቱ ኡስማዮ የተፃፈ መጽሐፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስት ሀላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራር እና ጥሪ የተደረገላቸው ታዋቂ አርቲስቶች በተገኙበት ተመርቋል፡፡

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ አብዲ ሙክታር በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፣ አርቲስት ኡስማዮ ለኦሮሞ የሙዚቃ እና ስነ ጥበብ እድገት ካበረከተው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ባልተናነሰ መልኩ ለህዝቦች እኩልነት፣ ነፃነት እና አንድነት ታሪክ የሚዘክረው አሻራ ያኖረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለህዝብ እኩለነት ዋጋ የከፈሉ ጀግኖች እንዲታወሱ የሚያደርገውን ጥረት ያደነቁት ክቡር አቶ አብዲ ሙክታር፣ ታላላቅ የማህበረሰቡ መሪዎች እና ፋና ወጊ የነፃነት ታጋዮች እንዲታወሱ ፣ አበርክቷቸው ለትውልድ አንዲተላለፍ ታሪካቸው በመፅሐፍ መልክ ተሰንዶ ለአንባቢወ መድረስ አለበት ብለዋል፡፡

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም በበኩላቸው፣ በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ለትውልድ የሚተላለፉ ታሪኮችን በመፅሐፍ መልክ አዘጋጅቶ የማቅረብ ልምድ ያልዳበረ መሆኑን ገልፀው በአርቲስት ኡስማዮ ታሪክ ዙሪያ የተዘጋጀው መፅሐፍ በብዙ መልኩ አስተማሪ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡ መፅሐፉ በአርቲስቱ ሴት ልጅ መዘጋጀቱ ሴት ፀሐፊያንን ከማበረታታት ባሻገር የህዝብ ታሪክ፣ ባህል እና ቋንቋ እድገት ጉልህ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡

የአርቲስት ኡስማዮ ሙሳ ልጅ እና የመፅሐፉ ፀሐፊ አርቲስት ሳርቱ ኡስማዮ በበኩሏ በመፅሐፉ መመረቅ የተሰማት ደስታ እና የወላጅ አባቷ በህይወት ኖሮ ይህንን የህዝብ ፍቅር ያለማየቱ የተደበላለቀ ስሜት እንደፈጠረባት ገልፃ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በዚህ ልክ ያማረ እና የወላጅ አባቷን ክብር የሚመጥን ታላቅ ዝግጅት በማዘጋጀቱ ምስጋና አቅርባለች፡፡

በመርሃ ግብሩ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ም/አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ከሪማ አሊ፣ የትምህርት ቢሮ ሀላፊ ሱልጣን አሊዩ፣ የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር አብዱሰላም መሀመድ እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በመድረኩ አርቲስት ጂሬኛ ሽፍራው እና ኬኦል ነጋሳ ተወዳጅ የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ለታዳሚው አቅርበዋል፡፡

ድሬዳዋ፣ ነሐሴ 16፣ 2018 (የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት)
ለበለጠ መረጃ
👉 ድረ ገጽ: http://www.ddu.edu.et/
👉 ፌስቡክ: https://www.facebook.com/DDUniv/
👉 ቴሌግራም: https://t.me/DDUniv/
👉 ትዊተር፡ https://twitter.com/DDUniv/”

ለድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች በሙሉየድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይሰጣል። በመሆኑም የመፈተኛ ጣቢያችሁን ድሬዳዋ ዩኒቨርሲ...
22/08/2026

ለድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች በሙሉ

የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ነሐሴ 20 እና 21 ቀን 2018 ዓ.ም ይሰጣል። በመሆኑም የመፈተኛ ጣቢያችሁን ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ያደረጋችሁ ተፈታኞች በሙሉ የተመደባችሁበትን ቀን እና መፈተኛ ክፍል በዩኒቨሪስቲ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ ገጽ እንዲሁም ዋናው ግቢ መግቢያ በር ላይ የሚለጠፍ መሆኑንን እየገለጽን ባመለከታችሁበት ድህረ-ገፅ ወይም e-mail በኩል የሚላክላችሁን የመጠቀሚያ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) ይዛችሁ በዕለቱ በተመደባችሁበት ቀን እና ሰዓት እንድትገኙ እናሳስባለን።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጅስትራር ጽ/ቤት

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጲያ የንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ጋር በትብብር ለመስራት ተስማማ፦ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ነጻ የንግድ ማማከር አገልግሎት የሚሰጥ ማዕከል ያቋቁማል::የድሬዳዋ ዩኒ...
21/08/2026

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጲያ የንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ጋር በትብብር ለመስራት ተስማማ፦ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ነጻ የንግድ ማማከር አገልግሎት የሚሰጥ ማዕከል ያቋቁማል::

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጲያ የንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን ውይይት ከንግድ ምክር ቤቱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር አድርጓል፡፡ ሁለቱ ተቋማት በማማከር እና ስልጠና፣ በምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሁም የተለያዩ ኮንፍረንሶችን በትብብር ማዘጋጀት በሚችሉበት ጉዳይ ዙሪያ መክረዋል፡፡

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተማም አወል በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪዎች ጋር በመቀራረበ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይነትም በተለይ አዲስ የቢዝነስ ሀሳብ ያላቸውን ስራ ፈጣሪዎች እንዲሁም ስራ ነክ ጉዳዮች ላይ ነፃ የቢዝነስ ማማከር አገልግሎት የሚሰጥ ማዕከል እንደሚከፍት ይፋ አድርገዋል፡፡

የኢትዮጲያ የንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክርቤት ዋና ፀኃፊ ዶ/ር ቀነኒሳ ለሚ በበኩላቸው ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ ምርምሮችን የመስራት ልምድ እና እውቀት ያላቸው ምሁራን መገኛ መሆኑን ገልፀው ምክርቤቱ ይህንን አቅም ለመጠቀም ከትምህርት ተቋማቱ ጋር በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ዘርፍን የትኩረት አቅጣጫ በማድረግ እና የሰለጠነ የሰው ሃይል አብቅቶ ለስራ ከማቅረቡም በላይ የንግዱን ማህበረሰብ፣ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪዎችን እንዲሁም አዳዲስ የቢዝነስ ሃሳብ ያላቸውን ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን እና ተማሪዎችን የሚደግፉ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ በመድረከ ተመላክቷል፡፡

ድሬዳዋ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት)
ለበለጠ መረጃ
👉 ድረ ገጽ: http://www.ddu.edu.et/
👉 ፌስቡክ: https://www.facebook.com/DDUniv/
👉 ቴሌግራም: https://t.me/DDUniv/
👉 ትዊተር፡ https://twitter.com/DDUniv/”

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ እና ሪፈራል ሆስፒታል ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የሕክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገለትየድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ እና ሪፈራል ሆስፒታል «ሂዩማን...
21/08/2026

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ እና ሪፈራል ሆስፒታል ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የሕክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገለት

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ እና ሪፈራል ሆስፒታል «ሂዩማን ብሪጅ» (Human Bridge) ከተሰኘው የበጎ አድራጎት ድርጅት የገበያ ግምቱ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎት ምስጫ መሣሪያዎችና ቁሳቁሶች ድጋፍ አገኘ።

በከፊል ሥራ በመጀመር የአካባቢውን ማህበረሰብ በማገልገል ላይ የሚገኘው ሆስፒታሉ፣ የሕክምና አገልግሎቱን በስፋትና በጥራት ለማስቀጠል የሚያስችሉ በርካታ የማስፋፊያ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ሲሆን አሁን የተገኘው ድጋፍም የሆስፒታሉን ተቋማዊ እቅድ ለማሳካትና አገልግሎቱን ለማዘመን ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚኖረው መሆኑ ተገልጿል።

በድጋፉ የተገኙት ዋና ዋና የሕክምና ቁሳቁሶች መካከል፦
👉 42 በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ዘመናዊ የታማሚ አልጋዎች
👉የአልትራሳውንድ ማሽኖች
👉የልብ ሕመም መመርመሪያ (ECG / Electrocardiography) ማሽኖች
👉የኦርቶፔዲክ ሕክምና መሣሪያዎች
👉የቀዶ ሕክምና ማከናወኛ ጠረጴዛዎች (OR Tables)
👉የተለያዩ የሕክምናና የላቦራቶሪ መመርመሪያ ማሽኖች ይገኙበታል።

በድጋፍ ርክክብ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም ባስተላለፉት መልዕክት፣ «ሂዩማን ብሪጅ» ሆስፒታሉ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር ሲያደርግ ለቆየው አጋርነት ምስጋና አቅርበዋል። አክለውም ዩኒቨርሲቲው የማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ፍላጎት ለማሟላት በሚያደርገው ጥረት ድርጅቱ የሚያደርገውን ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

የሂዩማን ብሪጅ ካንትሪ ዳይሬክተር ዶ/ር አዳሙ አንለይ በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው ቀደም ሲል የተደረጉለትን ድጋፎች በአግባቡ በመጠቀም የማህበረሰቡን አገልግሎት ማሻሻል መቻሉ በቀጣይም ተቋሙን ለማገዝ ከፍተኛ መነሳሳት መፍጠሩን ገልጸዋል። ድርጅታቸው የሆስፒታሉን አገልግሎት የሚያዘምኑ እንዲሁም የአገልግሎት ሽፋኑን እንዲያሰፋ የሚያስችሉ ድጋፎችን ማድርጉን ይቀጥላል ብለዋል።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ እና ሪፈራል ሆስፒታል የማህበረሰቡን የጤና ፍላጎት ለማሟላት እያደረገ ባለው በርካታ ጥረትና በሚሰጣቸው የክረምት የጤና በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት ከጤና ሚኒስቴር እውቅና ማግኘት የቻለ ተቋም መሆኑ በወቅቱ ተመላክቷል።

ድሬዳዋ፣ ነሐሴ 15፣ 2018 (የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት)
ለበለጠ መረጃ
👉 ድረ ገጽ: http://www.ddu.edu.et/
?Dire-Dawa University/DDUniv/
?? ቴሌግራም: https://t.me/DDUniv/
👉 ትዊተር፡ https://twitter.com/DDUniv/”

  የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በታች በተመለከቱት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ህጋዊ ማስረጃዎቻችሁን ይዛችሁ ማስታወቂያው...
20/08/2026



የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በታች በተመለከቱት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ህጋዊ ማስረጃዎቻችሁን ይዛችሁ ማስታወቂያው ላይ በተጠቀሱት አድርሻዎች በመቅረብ እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን፡፡

ዝርዝር መስፈርት እና ተያያዥ መረጃዎችን ከታች ይመልከቱ!!

የሐዘን መግለጫ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ጤና ሳይንስ  ኮሌጅ በህክምና ት/ርት ቤት ረዳት ፕሮፌሰር አና የአይን ስፔሻሊስት ሀኪም የነበሩት  ዶ/ር  ያቆብ ጨመረ ባደረባቸው ህመም ምክንያት...
17/08/2026

የሐዘን መግለጫ

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህክምና ት/ርት ቤት ረዳት ፕሮፌሰር አና የአይን ስፔሻሊስት ሀኪም የነበሩት ዶ/ር ያቆብ ጨመረ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ነሀሴ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ በ ዶ/ር ያቆብ ጨመረ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ መፅናናትን ይመኛል፡፡

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ

የውሃ ስርጭት እና ተደራሽነትን ማሻሻል የሚያስችል የስራ ውል ከአስተዳደሩ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ጋር ተደረገበድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የውሃ ስርጭት ችግር በቋሚነት መፍታት የሚ...
15/08/2026

የውሃ ስርጭት እና ተደራሽነትን ማሻሻል የሚያስችል የስራ ውል ከአስተዳደሩ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ጋር ተደረገ

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የውሃ ስርጭት ችግር በቋሚነት መፍታት የሚያስችል የስራ ስምምነት ከድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ጋር ተፈርሟል።

ዩኒቨርሲቲው የውሃ እጥረት ችግርን መቅረፍ የሚያስችሉ የከርሰ ምድር ውሃ ቢያስቆፍርም የስርጭት ክፍተት በመኖሩ ምክንያት በተማሪዎች መኖሪያ፣ በቢሮዎች እና የመምህራን መኖሪያ ቤቶች አካባቢ የውሃ ስርጭት እጥረት ተከስቷል። ከአስተዳደሩ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጥን ጋር የተደረገው ስምምነት ይህንኑ የውሃ ስርጭት ችግር በዘላቂነት የሚቀርፍ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡

በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ፕሮጀክት፣ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ እና በመምህራን መኖሪያ አካባቢዎች የሚስተዋለውን የአቅርቦት ችግር እንደሚያቃልል ተገልጿል።

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም እንደገለጹት ‘’የድሬዳዋ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ፕሮጀክቱን በወቅቱ በማጠናቀቅ በተቋም ደረጃ የሚስተዋለውን የውሃ ስርጭት ተግዳሮት ለማቃለል የተለመደ ድጋፉን እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አክለውም ባለስልጣኑ በቀጣይም ግቢውን የማስዋብ እና የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ረገድ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በትብብር እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡።

የድሬዳዋ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ ሙሴ በበኩላቸው ‘’ዩኒቨርሲቲው በራሱ ጥረት እያከናወናቸው ያሉትን የልማት ስራዎችን አድንቀዋል። አቶ መሀመድ አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተጀመረውን የውሃ ስርጭት ፕሮጀክት ከተያዘለት ጊዜ ቀድሞ ለማጠናቀቅ ተገቢውን አመራር እንደሚሰጡ ገልጸዋል።

ድሬዳዋ፣ ነሐሴ 8፣ 2018 (የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት)
ለበለጠ መረጃ
👉 ድረ ገጽ: http://www.ddu.edu.et/
👉 ፌስቡክ: https://www.facebook.com/DDUniv/
👉 ቴሌግራም: https://t.me/DDUniv/
👉 ትዊተር፡ https://twitter.com/DDUniv/”

📢𝐂𝐀𝐋𝐋 𝐅𝐎𝐑 𝐏𝐀𝐏𝐄𝐑𝐒 | 𝐇𝐚𝐫𝐥𝐚 𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐚𝐥 𝐨𝐟 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐢𝐞𝐝 𝐒𝐜𝐢𝐞𝐧𝐜𝐞𝐬 𝐚𝐧𝐝 𝐌𝐚𝐭𝐞𝐫𝐢𝐚𝐥𝐬We are cordially inviting researchers, scholars, and a...
14/08/2026

📢𝐂𝐀𝐋𝐋 𝐅𝐎𝐑 𝐏𝐀𝐏𝐄𝐑𝐒 | 𝐇𝐚𝐫𝐥𝐚 𝐉𝐨𝐮𝐫𝐧𝐚𝐥 𝐨𝐟 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐢𝐞𝐝 𝐒𝐜𝐢𝐞𝐧𝐜𝐞𝐬 𝐚𝐧𝐝 𝐌𝐚𝐭𝐞𝐫𝐢𝐚𝐥𝐬

We are cordially inviting researchers, scholars, and academics to submit their original research for publication in the upcoming issue!

🔹 Volume: 4, Issue 2

🔹 Accreditation: Nationally Accredited Journal in Ethiopia 🇪🇹

🔹 Scope: Applied Sciences, Materials Science, and Engineering

📩 Submit Your Manuscript Today!

For submission guidelines, editorial policies, and inquiries, please visit our website or contact the editorial team.

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል እየተከናወኑ ያሉ የክረምት በጎ አድራጎት ሥራዎችበድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ አድራጎት ...
12/08/2026

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል እየተከናወኑ ያሉ የክረምት በጎ አድራጎት ሥራዎች

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብሮች በተለያዩ የድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢዎች በሰፊው እየተከናወኑ ይገኛሉ። በዛሬው እለት የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በአሸዋ አላይ-በዴ አካባቢ የተካሄደውን የበጎ አድራጎትና የሕክምና አገልግሎት መርሃ ግብር ጎብኝተዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ወቅትም ለማህበረሰቡ ነጻ የህክምና ምርመራ፣ የጤና ምክር አገልግሎት እንዲሁም የማህበረሰቡን ግንዛቤ ለመጨመር የጤና ትምህርት ተሰጥቷል። በጉብኝቱ ላይም መልዕክት ያስተላለፉት የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዮቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሁሴን መሀመድ መርሀ ግብሮቹ በቀጣይ በአስተዳደሩ የገጠር አካባቢዎች እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ድሬዳዋ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት)
ለበለጠ መረጃ
👉 ድረ ገጽ: http://www.ddu.edu.et/
👉 ፌስቡክDire-Dawa Universityv/
👉 ቴሌግራም: https://t.me/DDUniv/
👉 ትዊተር፡ https://twitter.com/DDUniv/

𝐃𝐢𝐫𝐞 𝐃𝐚𝐰𝐚 𝐔𝐧𝐢𝐯𝐞𝐫𝐬𝐢𝐭𝐲 𝐇𝐨𝐬𝐭𝐬 𝐄𝐔-𝐒𝐮𝐩𝐩𝐨𝐫𝐭𝐞𝐝 𝐕𝐢𝐫𝐭𝐮𝐚𝐥 𝐑𝐞𝐚𝐥𝐢𝐭𝐲 𝐓𝐫𝐚𝐢𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐭𝐨 𝐄𝐦𝐩𝐨𝐰𝐞𝐫 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐢𝐞𝐝 𝐒𝐜𝐢𝐞𝐧𝐜𝐞 𝐄𝐝𝐮𝐜𝐚𝐭𝐨𝐫𝐬Dire Dawa Universit...
06/08/2026

𝐃𝐢𝐫𝐞 𝐃𝐚𝐰𝐚 𝐔𝐧𝐢𝐯𝐞𝐫𝐬𝐢𝐭𝐲 𝐇𝐨𝐬𝐭𝐬 𝐄𝐔-𝐒𝐮𝐩𝐩𝐨𝐫𝐭𝐞𝐝 𝐕𝐢𝐫𝐭𝐮𝐚𝐥 𝐑𝐞𝐚𝐥𝐢𝐭𝐲 𝐓𝐫𝐚𝐢𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐭𝐨 𝐄𝐦𝐩𝐨𝐰𝐞𝐫 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐢𝐞𝐝 𝐒𝐜𝐢𝐞𝐧𝐜𝐞 𝐄𝐝𝐮𝐜𝐚𝐭𝐨𝐫𝐬

Dire Dawa University has officially launched a four-day practical Virtual Reality (VR) training workshop aimed at strengthening the instructional capacity of University of Applied Sciences (UAS) educators. Organized in collaboration with the European Union and the MaDE for UASs Project, the initiative focuses on integrating cutting-edge technologies into higher education to enhance practical, industry-aligned learning across Ethiopian universities.

The landmark workshop brings together trainers, educators, international partners, and academic leaders to explore immersive learning methodologies, conduct interactive simulations, and examine how VR can be practically embedded across various academic disciplines.

Addressing distinguished guests, Dr. Ubah Adam, President of Dire Dawa University and Chairperson of the Universities of Applied Sciences Consortium, highlighted the transformative role of emerging technologies in modern education. She further said ''Virtual Reality is one of the most promising technologies for modern education; it enables educators to create immersive, interactive, and safe learning environments where students can practice complex procedures, conduct simulations, and gain hands-on experience.

The four-day program will focus on hands-on technical sessions, collaborative experience sharing, and developing actionable strategies to adopt VR technologies in university classrooms and laboratories, marking a significant step forward for applied education in the region.

August 6, 2026 (Public and International Relation, DDU)
For more information, please use the links below
👉 Website: http://www.ddu.edu.et/
👉 Facebook: https://www.facebook.com/DDUniv/
👉 Telegram: https://t.me/DDUniv/

Address

Dire-Dawa University
Dire Dawa
1362

Opening Hours

Monday 07:30 - 17:00
Tuesday 07:30 - 17:00
Wednesday 07:30 - 17:00
Thursday 07:30 - 17:00
Friday 07:30 - 17:00

Telephone

+251251111501

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire-Dawa University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Dire-Dawa University:

Shortcuts

Share