DIRE Dawa Teacher Association/DDTA

DIRE Dawa Teacher Association/DDTA Let's join together with to create advanced skills and knowledge about education and related information.

የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የአስተዳደር እና የሞዴል ፈተና መርሃ-ግብርለተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም የዝግጅት ጊዜና ስኬትን እንመኛለን።
25/05/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የአስተዳደር እና የሞዴል ፈተና መርሃ-ግብር

ለተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም የዝግጅት ጊዜና ስኬትን እንመኛለን።

የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ ሆኗል።      -------------------------- // -----------------...
15/05/2026

የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ ሆኗል።

-------------------------- // -------------------------

(ግንቦት 07/2018 ዓ.ም) ደጋግሞ መለማመድ የእውቀትን እና የክህሎትን ጉድለት ይሞላል፤ በራስ መተማመንን ያሳድጋል ሲል አገልግሎቱ ገልጿል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በበይነ መረብ (CBT) ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ ይገኛል።

በዚህም ሁሉም ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ባለው ማስፈንጠሪያ በመጠቀም USER Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Pass word በሚለው ላይ 1234 በማስገባት መጠቀም እንደሚችሉ አሳውቋል።

ተማሪዎች ፈተናውን ለመለማመድም በዴስክቶፕ ኮምፕዩተር፣ በላፕቶፕ ኮምፕዩተር፣ በታብሌት፣ በስልክና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሣሪያዎች ማንኛውንም ዓይነት ኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም ከግንቦት 07/2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ እንደሚችሉም ገልጿል።

ተፈታኞች አዲሚሽን ካርድ ከየትምህርት ቤታቸው ማግኘት እንደሚችሉ የተገልጸ ሲሆን በየጊዜው ተማሪዎች የሚለማመዱባቸውን ፈተናዎች በተከታታይ የምንሰጥ መሆኑንም አገልግሎቱ አብራርቷል።
በመሆኑም መምህራን ፣ የትምህርት ቤት አመራርና ወላጆች ተፈታኝ ተማሪዎች እንዲለማመዱ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንዲያደርጉ በአክብሮት ጥሪ እናቀርባለን።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/-of-education-ethiopia
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ

ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም የ5ኛ፣ 7ኛ እና 11ኛ ክፍል ፈተና በትምህርት ቢሮ የሚዘጋጀውን እስታንዳርድ ፈተና በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች የትምህርት ቤት ፋይናል (Final...
11/05/2026

ማስታወቂያ

የ2018 ዓ.ም የ5ኛ፣ 7ኛ እና 11ኛ ክፍል ፈተና በትምህርት ቢሮ የሚዘጋጀውን እስታንዳርድ ፈተና በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች የትምህርት ቤት ፋይናል (Final) ፈተና ሆኖ ለተማሪዎች እንዲያዝ ስለማሳወቅ

የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እና የተማሪዎችን ትክክለኛ የብቃት ደረጃ ለመመዘን የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል።

ከዚህ ቀደም በየዓመቱ ሲሰጥ የነበረው የስታንዳርድ ፈተና ለጥናት እና ለምክረ ሃሳብ ማቅረቢያነት ብቻ ይውል የነበረ ቢሆንም በዚህ ሂደት ውስጥ በተለይም የተማሪዎችን ትክክለኛ የትምህርት ደረጃ ለማወቅ እና በትምህርት ቤቶች በኩል የሚታዩ የምዘና ክፍተቶችን ለመቅረፍ እንዲቻል አዲስ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመሆኑም በ2018 ዓ.ም በሁሉም የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች የሚሰጠው የስታንዳርድ ፈተናን በተመለከተ የሚከተሉት ውሳኔዎች መተላለፋቸውን እናሳውቃለን፡-

1. ፈተናው የሚሰጥባቸው ክፍሎች፡ የስታንዳርድ ፈተናው ለ5ኛ፣ 7ኛ እና 11ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚሰጥ ይሆናል።

2. የውጤት አያያዝ፡ ፈተናው በተጠቀሱት የትምህርት አይነቶች ተማሪዎች የሚፈተኑት ሆኖ፤ ውጤቱም ከ40 (አርባ) ነጥብ ተይዞ እንደ ትምህርት ቤቱ የፋይናል (Final) ፈተና ውጤት የሚቆጠር ይሆናል።

3. የፈተና ዝግጅት፡ ፈተናው በማዕከል በትምህርት ቢሮ የሚዘጋጅ በመሆኑ ትምህርት ቤቶች በእነዚህ የክፍል ደረጃዎች እና የትምህርት አይነቶች የራሳቸውን የፋይናል ፈተና የማያዘጋጁ መሆኑን እናሳውቃለን።

4. ዝግጅትን በተመለከተ፡ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸው ለዚህ በማዕከል ለሚዘጋጀው ፈተና ውጤታማ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እና ክትትል ከወዲሁ እንዲያደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን።

የዚህ ለውጥ ዋነኛ ዓላማ የምዘና ስርዓቱን ወጥ፣ ግልጽ እና ጥራቱን የጠበቀ በማድረግ የተማሪዎችን ትክክለኛ የዕውቀት ደረጃ ለማወቅ እንዲቻል በመሆኑ ሁሉም የትምህርት አመራሮች፣ መምህራን እና ባለድርሻ አካላት ለተግባራዊነቱ የበኩላችሁን እንድትወጡ እናሳውቃለን።

የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ

በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና1. የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ቀድመው የሚፈተኑ ሲሆን በመቀጠል ማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል።2. ፈተናው በተፈጥሮ እና...
02/04/2026

በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና
1. የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ቀድመው የሚፈተኑ ሲሆን በመቀጠል ማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል።

2. ፈተናው በተፈጥሮ እና በማህበራዊ ሳይንስ በእያንዳቸው በሶስት ዙር በድምሩ በ6 ዙር የሚሰጥ ይሆናል።

3. ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች በተፈጥሮ ሳይንስ እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪና ፊዝክስ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።

4. ፈተናው በየትምህርት ዓይነቱ ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን ይሆናል። የዝግጅት አግባቡም 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት (Common Contents) ላይ ያተኩራል። ከ10ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል። የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን ይሆናል።

06/02/2026
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በሀዋሳ ከተማ የምክክር መድረክ አካሄደ  የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ጥር 27/2018 ዓ/ም  በሀዋሳ ከተማ የ6 ወር እቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሂዷል፡፡ በዚህ ...
06/02/2026

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በሀዋሳ ከተማ የምክክር መድረክ አካሄደ
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ጥር 27/2018 ዓ/ም በሀዋሳ ከተማ የ6 ወር እቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሂዷል፡፡ በዚህ የ2018 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መምህራን ማህበር የፕላን ክትትልና ግምገማ ክፍል አባላት የተገኙ ሲሆን የኢመማ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የክፍሎች እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እንዲሁም ክልሎች/ ከተማ አስተዳደሮች እና የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበራት ሪፖርቶች ቀርበው ተመክሮባቸዋል፡፡

በአጠቃላይ የኢመማ እና የኢመማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እቅድ አፈጻጸም በተሻለ ቁመና ላይ እንደሆነ የተገመገመ ሲሆን በተለይ ከአባላት መዋጮ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ክልሎች ከመምህራን ጋር እየተደረገ ያለው ውይይት አበረታች ሆኖ ተገኝቷል። በተለይ የቤ/ጉሙዝ ክልል በኢመማ 23ኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተወሰነውን የአባላት መዋጮ ማሻሻያ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረጉና ለኢመማም በዚሁ በተሻሻለው መዋጮ ፈሰስ ማድረግ መጀመሩ መልካም ተሞክሮ ስለመሆኑ በምክክሩ ተነስቷል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቀጣይ የስድስት ወራት የሁሉም ማህበራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

ማስታወቂያለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻ...
13/11/2025

ማስታወቂያ

ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤

የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ በ3 የተለያዩ ጉዳዮች ማለትም፤

1. ትምህርትን በአደጋ ጊዜ ለማስቀጠልየተዘጋጀ መመሪያ (የመጀመሪያ ረቂቅ) ሊንክ = https://forms.gle/DxVRi8nBuu6HBD7F7
2. የገጠር እና ጠረፋማ አካባቢዎችየትምህርት ድጋፍ አተገባበር መመሪያ (የመጀመሪያ ረቂቅ) ሊንክ = https://forms.gle/uH1tvfKmGrWEwhah6
3. ነፃና የግዴታ ትምህርት አተገባበር መመሪያ (የመጀመሪያ ረቂቅ) ሊንክ= https://forms.gle/F2RHcXKdUUmrCvik6 አዘጋጅቷል።

በመሆኑም ሰነዶቹን በማንበብ አስተያየት እንድትሰጡ እየጠየቅን፤

 ለመጀመር ከእያንዳንዱ ረቂቅ መመሪያ ፊት ለፊት ያሉትን ሊንኮች መጫን፤

 በመቀጠል ማስፈንጠሪያ የሚለውን በመጫን ሰነዱን ማግኘት ትችላላችሁ፣

 ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ (submit) የሚለውን በመጫን መረጃውን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ትምህርት ሚኒስቴር

ማስፈንጠሪያ(Link)

Baaqa Shaqaalaha Rayidka ah ee Wax laga Beddelay 1353/2017 Qodobbo Kala Duwan~~~~~✅ Qaybta Saddexaad Qodobka 9aad Hagaaj...
10/11/2025

Baaqa Shaqaalaha Rayidka ah ee Wax laga Beddelay 1353/2017 Qodobbo Kala Duwan
~~~~~
✅ Qaybta Saddexaad Qodobka 9aad Hagaajinta Miisaanka Mushaharka:

1. Ujeeddada hagaajinta miisaanka mushaharka waa in la go'aamiyo nidaam qaybinta mushaharka oo soo jiidan doona oo hayn doona xirfadlayaal xirfad sare leh isla markaana hagaajin doona waxqabadka shaqaalaha.

2. Guddigu wuxuu si joogto ah u baran doonaa hagaajinta miisaanka mushaharka shaqaalaha rayidka ah, isagoo tixgelinaya awoodda dhaqaale ee dawladda, xaaladaha guud ee nolosha dadka, heerarka qiimaha iyo sicir-bararka iyo arrimo kale, wuxuuna u gudbin doonaa Golaha Wasiirrada, wuxuuna la socon doonaa hirgelintiisa isagoo soo saaraya tilmaamo.

3. Miisaanka mushaharku waa inuu lahaadaa tallaabooyin tilmaamaya mushaharka bilowga iyo kan ugu badan ee heer shaqo kasta, iyo sidoo kale kordhinta mushaharka ee si joogto ah loo sameeyo.

4. Guddigu waa inuu daraaseeyaa mushaharka ugu yar iyo xadka mushaharka ugu badan ee shaqo kasta afartii sanaba mar oo uu u gudbiyo Golaha Wasiirrada, wuxuuna la socon doonaa hirgelintiisa.

✅Marka laga hadlayo Qaybta Saddexaad, Qodobka 11aad, faqrada 2aad:

Mushaharka shaqaale kasta oo dowladeed lama hakin karo ama lama dhimi karo marka laga reebo sababaha soo socda:

a) Marka shaqaaluhu uu qoraal ahaan u sheego heshiiskiisa,

b) Amarka maxkamadda, ama

c) Sida sharcigu dhigayo, lama hakin karo ama lama dhimi karo.

3/ Qaddarka laga jarayo mushaharka shaqaalaha ee ku xusan Qodobka Hoosaadka (2) (b) ama (c) ee Qodobkan waa in uusan dhaafin saddex meelood meel mushaharka.

✅Marka laga hadlayo Qaybta Sagaalaad, Qodobka 72aad, Shuruudaha Shaqada ee Shaqaalaha Dumarka ah:

1/ Xafiis kasta oo dowladeed waa inuu qaadaa tallaabooyin taageero dheeraad ah si loo xoojiyo shaqaalaha dowladda haweenka ah loona hubiyo in lagu meeleeyo jagooyinka go'aan qaadashada.

2/ Haweenku waxay ka faa'iideysan doonaan tallaabooyin taageero dheeraad ah oo ku saabsan shaqaalaysiinta, dallacaadda, wareejinta, dallacaadda, horumarinta shaqada, waxbarashada iyo tababarka.

3/ Waa mamnuuc in shaqaale dawladeed oo uur leh laga wareejiyo booska ay hadda ka shaqeyso ama loo dallacsiiyo boos kale; si kastaba ha ahaatee, haddii caddaynta caafimaadku ay caddeyso inay khatar ku tahay caafimaadkeeda ama tan uurjiifka, waxaa si ku meel gaar ah loogu meeleyn karaa boos ama goob shaqo oo ku habboon.

4/ Xafiis dowladeed ma eryi karo haweeney shaqaale dowladeed ah shaqadeeda inta ay uurka leedahay iyo afar bilood gudahood laga bilaabo taariikhda ay dhalatay, taasoo ka dhalatay hoos u dhac ku yimid tirada shaqaalaha sida ku xusan Qodobka 139 ee Baaqan.

5/ Shaqaale dowladeed kasta oo dumar ah waxaa la siin doonaa fasax lacag ah oo lagu daaweynayo ilmaheeda ka yar hal sano muddo lagu xaqiijiyay caddaynta caafimaadka.

6/ Xafiis kasta oo dowladeed waa inuu dhisaa xarun xannaano carruureed oo ay shaqaalaha dowladda ee haweenka ah ay ku nuujin karaan carruurtooda oo ay daryeeli karaan carruurtooda; faahfaahinta hirgelinteeda waxaa go'aamin doona tilmaamaha ay soo saartay Guddiga.

✅Qodobka 84aad ee ku saabsan daaweynta caafimaad iyo fasaxa la siiyo shaqaalaha sababo la xiriira dhaawacyada shaqada

1/ Kharashaadka looga baahan yahay adeegyada caafimaad ee soo socda ee gudaha lagu siiyo shaqaale dowladeed oo ku dhaawacmay shaqada awgeed waxaa dabooli doona xafiisku:

10/11/2025

Labsii Hojjettoota Mootummaa Fooyya’e 1353/2017 Tumaalee Adda Addaa
~~~~~
✅Kutaa Sadii Keewwata 9 Sirreeffama Iskeelii Mindaa:

1. Kaayyoon sirreeffama iskeelii mindaa sirna raabsa mindaa ogeessota ogummaa olaanaa qaban hawwachuu fi tursiisuu fi raawwii hojii hojjetaa fooyyessuu danda'u murteessuudha.

3. Iskeeliin mindaa sadarkaa hojii tokkoon tokkoon isaatiif mindaa ka’umsaa fi ol’aanaa, akkasumas daballii mindaa yeroo yeroon raawwatamu tarkaanfiiwwan agarsiisan ni qabaata.

4. Komishinichi waggaa afuriin hojii tokkoon tokkoon isaaniif mindaa xiqqaa fi mindaa ol’aanaa qoratee Mana Maree Ministirootaaf ni dhiyeessa, hojiirra oolmaa isaas ni hordofa.

✅Kutaa Sadii Keewwata 11 Keewwata Xiqqaa 2 ilaalchisee:

Mindaan hojjetaa mootummaa kamiyyuu sababoota armaan gadiitiin alatti hin qabamu ykn hir’ifamuu hin danda’u:

a) Hojjetaan waliigaltee isaa barreeffamaan yommuu ibsu, .
b) Ajaja mana murtiitiin, yookiin
c) Akkaataa seeraan tumameen alatti dhorkamuus ta’ee hir’isuun hin danda’amu.


✅Kutaa Sagal Keewwata 72 Haala Hojii Hojjettoota Dubartii ilaalchisee:

1/ Waajjirri mootummaa kamiyyuu hojjattoota mootummaa dubartootaa humneessuu fi gita hojii murtee kennuu irratti ramaddii isaanii mirkaneessuuf tarkaanfiiwwan deeggarsa dabalataa ni fudhata.

2/ Dubartoonni tarkaanfiiwwan deeggarsa dabalataa qacarrii, guddina sadarkaa, jijjiirraa, guddina sadarkaa, guddina hojii, barnootaa fi leenjii irratti fayyadamoo ta’u.

3/ Hojjettuu mootummaa ulfaa gita hojii amma itti qacaramte irraa ykn gara gita hojii biraatti guddifamuun dhorkaadha; haa ta’u malee, ragaan fayyaa fayyaa ishee ykn kan daa’ima gadameessa keessa jiruuf balaa akka qabu yoo mirkaneesse, yeroodhaaf bakka ykn bakka hojii mijaawaa ta’etti ramadamuu dandeessi.

6/ Waajjirri mootummaa kamiyyuu giddugala kunuunsa guyyaa hojjattoonni mootummaa dubartootaa ijoollee isaanii hoosisanii fi ijoollee isaanii kunuunsuu danda’an ni hundeessa; bal’inni raawwii isaa qajeelfama Komishinichi baaseen kan murtaa’u ta’a.

✅Keewwata 84 Wal’aansa fayyaa fi boqonnaa hojjataa tokkoof sababa miidhaan hojiin wal qabateen kennamu ilaalchisee

1/ Hojjetaa mootummaa sababa hojiitiin miidhameef tajaajila yaalaa armaan gadii biyya keessaa kennamuuf baasii barbaachisu mana hojichaatiin raawwatama.

10/11/2025

ተሻሽሎ የወጣው የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ 1353/2017 ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
~~~~~
✅ክፍል ሶስት አንቀፅ 9 የደሞዝ ስኬል ማስተካከያ በተመለከ፦

1. የደሞዝ ስኬል ማስተካከያ ዓላማ ከፍተኛ እውቀትና ችሎታ ያለውን ባለሙያ ለመሳብ፣ ለማቆየትና ሠራተኛውን ለማትጋት የሥራ ውጤቱን ለማሻሻል የሚያስችል የደሞዝ አከፋፈል ሥርዓት ለመወሰን ነው።

2. ኮሚሽኑ የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ሰኬል ማስተካከያ የመንግስትን የፋይናስ አቅም ፣የሕዝቡን አጠቃላይ የኑሮ ሁኔታ፣የዋጋ ደረጃዎችና ግሽበት እና አግብብነት ያለውን ሌሎች ሁኔታዎች ባገናዘበ መንገድ በየጊዜው እያጠና ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ ያስወስናል ፣መመሪያ በማውጣት አፈፃፀሙን ይቆጣጠራል፡፡

3. የደመወዝ ስኬል ለያንዳንዱ የሥራ ደረጃ መነሻ እና ከፍተኛ መድረሻ ደመወዝ እንዲሁም በየጊዜው የሚደረገውን የደመወዝ ጭማሪ የሚያመለክቱ እርከኖች ይኖሩታል፡፡

4. ኮሚሽኑ የሥራ ደረጃ ዝቅተኛ ደመወዝ እና ከፍተኛ ደመወዝ ጣሪያ በየአራት አመቱ አጥንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ ያስወስናል፣አፈፃፀሙን ይቆጣጠራል፡፡

✅ክፍል ሦስት አንቀጽ 11 ተ.ቁጥር 2 በተመለከተ፦

የማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ በሚከተለው ምክንያት ካልሆነ በስተቀር ሊያዝ ወይም ሊቆረጥ አይችልም፡፡

ሀ) ሠራተኛው ስምምነቱን በጽሑፍ ሲገልጽ፣

ለ) በፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ ወይም

ሐ) በሕግ በተደነገገው መሠረት፣ ካልሆነ በስተቀር ሊያዝ ወይም ሊቆረጥ አይችልም፡፡

3/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) (ለ) ወይም (ሐ) መሠረት ከሠራተኛ ደመወዝ በየወሩ የሚቆረጠው ከደመወዙ አንድ ሦስተኛ አይበልጥም፡፡

✅ክፍል ዘጠኝ አንቀጽ 72 ለሴት ሠራተኞች የሚጠበቁ የሥራ ሁኔታዎችን በተመለከተ፦

1/ ማንኛውም የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሴት የመንግሥት ሠራተኞችን ለማብቃትና በውሳኔ ሰጪ የሥራ ቦታዎች ላይ እንዲመደቡ ለማድረግ የሚያስችሉ የተጨማሪ ድጋፍ እርምጃዎችን መውሰድ አለበት፡፡

2/ ሴቶች በቅጥር፣ በደረጃ እድገት፣ በዝውውር፣ በድልድል፣ በሙያ መሰላል እድገት፣ በትምህርትና ሥልጠና አፈጻጸም የተጨማሪ ድጋፍ እርምጃ ተጠቃሚ መሆን አለባቸው፡፡

3/ ነፍሰ ጡር የሆነችን የመንግሥት ሠራተኛ በቅጥር ወይም በደረጃ ዕድገት ከተመደበችበት የሥራ መደብ ወደ ሌላ የሥራ መደብ መድቦ ማሰራት የተከለከለ ነው፤ ሆኖም ለራሷ ጤንነት ወይም ለፅንሱ አደገኛ መሆኑ በሕክምና ማስረጃ ሲረጋገጥ ተስማሚ ወደ ሆነ የሥራ መደብ ወይም የሥራ ቦታ በጊዜያዊነት ተመድባ እንድትሠራ መደረግ አለበት፡፡

4/ ማንኛውም የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሴት የመንግስት ሠራተኛ ነፍሰጡር በሆነችበት ጊዜና ከወለደችበት ቀን ጀምሮ በአራት ወር ጊዜ ውስጥ በዚህ አዋጅ አንቀጽ 139 መሠረት በሚያደርገው የሠራተኛ ቅነሳ ከሥራ ሊያሰናብታት አይችልም፡፡

5/ ማንኛዋም ሴት የመንግሥት ሠራተኛ አንድ ዓመት ያልሞላውን ሕጻን ልጇን ለማሳከም በህክምና ማስረጃ ለተረጋገጠ ጊዜ ደመወዝ የሚከፈልበት ፈቃድ ይሰጣታል፡፡

6/ ማንኛውም የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሴት የመንግስት ሠራተኞች ሕጻናት ልጆቻቸውን የሚያጠቡበትና ሕጻናቱን የሚንከባከቡበት የሕጻናት ማቆያ ማቋቋም አለበት፤ ዝርዝር አፈጻጸሙ ኮሚሽኑ በሚያወጣው መመሪያ ይወሰናል።

✅አንቀፅ 84 ለሠራተኛው ከሥራ በመጣ ጉዳት ምክንት የሚሰጥ ህክምና እና ፈቃድ በተመለከተ

1/ በሥራው ምክንያት ጉዳት ለደረሰበት የመንግሥት ሠራተኛ በሀገር ውስጥ ለሚሰጡ ለሚከተሉት የሕክምና አገልግሎቶች የሚያስፈልገው ወጪ በመሥሪያ ቤቱ ይሸፈናል:-

Address

DIRE Dawa Main Street
Dire Dawa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DIRE Dawa Teacher Association/DDTA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category