20/05/2026
Woizero Siheen Polytechnic College
Welcome to the Official page of Woizero Siheen Polytechnic College (Dessie). We will keep y
የወ/ሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታሪክ
የወ/ሮ ስኂን ት/ቤት በንጉሥ ሚካኤል ልጅ በወ/ሮ ስኂን ሚካኤል በ1922 ዓ.ም ሳላይሽ በሚገኘው የልጃቸው ጃንጥራር ኃ/ማርያም አስፋው ርስት ላይ በ25,000 ብር ተሠራ፡፡ ይህም በሀገራችን ዘመናዊ የትምህርት ታሪክ ከተመሰረቱት የመጀመሪያ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ ያደርገዋል፡፡ ላለፉት 89 ዓመታት በተለያዩ የዕድገት ደረጃዎች ውስጥ አልፎ አሁን ካለበት የፖሊቴክኒክነት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በነዚህ ጊዜያት በሀገር አቀፍም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በሙዚቃው፣ በፖለቲካው እና ኢኮኖሚው ትልቅ ዝናን ያተረፉ ዜጎች የተገኙበት የትምህርት ተቋም ነው፡፡ ከዚህ ቀጥሎ በዘመን ቅደም ተከተል የ
20/05/2026
19/05/2026
የወይዘሮ ስኅን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጀኔራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ አደረገ
አዲስ አበባ :-ግንቦት 11/2018
የወ/ሮ ስኀን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሥራ ኃላፊዎችና መምህራን ቡድን በጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት ፍሬያማ የሆነ የሥራ ላይ የልምድ ልውውጥና ጉብኝት አካሄደ።
የጉብኝቱ ዋና ዓላማ በሁለቱ አንጋፋ ተቋማት መካከል ያለውን ትስስር ማጠናከርና የተሻሉ አሰራሮችን መጋራት ሲሆን፣ በኮሌጁም ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል። ቡድኑ በቆይታው፦
በዘመናዊ መሣሪያዎች የተደራጁ የተግባር ማሰልጠኛ ወርክሾፖችን፣
የኮሌጁን የቴክኖሎጂ ሽግግርና የፈጠራ ሥራዎችን፣
የአስተዳደርና የዲጂታል አሰራር ሥርዓቶችን በቅርብ ተመልክቷል።
በማጠቃለያውም የሁለቱ ኮሌጆች የሥራ ኃላፊዎች ባደረጉት የጋራ ውይይት፣ ያገኟቸውን መልካም ተሞክሮዎች በኮሌጆቻቸው ውስጥ ተግባራዊ በማድረግ የሥልጠና ጥራትን ይበልጥ ለማሳደግና በቀጣይም አብሮነታቸውን አጠናክረው ለመቀጠል ተስማምተዋል።
19/05/2026
19/05/2026
የወ/ሮ ስሂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ አደረገ
አዲስ አበባ:-ግንቦት 11/2018አ.ም
የወ/ሮ ስሂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአንጋፋውና ስመ ጥር ከሆነው ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር የልምድ ልውውጥ አደረገ። ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ1917 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን የመሰረቱት ደግሞ የቀድሞው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ተፈሪ መኮንን ሲሆኑ ግርማዊ ቀዳማዊ ሀይለ ሥላሴ ነጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተብለው ዘውድ ከመጫናቸው ስድስት ዓመት ቀደም ብለው ነው። ይህ ኮሌጅ 100ኛ ዓመቱን ያከበረው አምና በ2017 ዓ.ም ነው። ወ/ሮ ስሂን እና ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የሚያገናኛቸው የታሪክ ሠንሠለት አላቸው። ይህም 1. ቀድሞ የተሰሩት ህንጻዎች ተመሳሳይ የሆነ የኪነ-ህንፃ ጥበብ ያረፈባቸው መሆኑ። 2.በተቀራረበ ጊዜ /በአምስት ዓመት /የጊዜ ልዩነት የተመሰረቱ ሲሆኑ በዘመናዊ ትምህርት ታሪክ ምስረታ ውስጥ ኢትዮጵያ መጀመሪያ የተመሠረተው ሚኒሊክ ትምህርት ቤት፣ ሁለተኛው ተፈሪ መኮንን ሶስተኛው ወ/ሮ ስሂን ት/ቤቶች ናቸው።
3.ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ያሰሩት ንጉሥ ሀይለ ሥላሴ ሲሆኑ የንጉሡ ባለቤት እቴጌ መነን ደግሞ የወ/ሮ ስሂን ልጅ ናቸው። ወ/ሮ ስሂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን የመሠረቱት የእቴጌ መነን እናትና የንጉሥ ሚካኤል ልጅ ወ/ሮ ስሂን ሚካኤል ናቸው። በተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ/ኮ ግቢ ስንደርስ የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በሞቀ ሁኔታ እንኳን መጣችሁ በማለት አቀባበል አድርገውልናል።
በመጀመሪያም የአርት ሰልጣኞች እና ተመራቂዎች የሰሩትን የአርት ጋለሪ ፣ የተለያዩ ወርክ ሾፖች፣መማሪያ ክፍሎች፣ የቴክኖሎጅና የኢንተርፕረነር ኢንኩቤሽን ሴንተር፣የምድረ-ግቢውን አገልግሎት ታሪካዊነቱን የሚየሳይ ገለጻ በዋና ዲኑ የተደረገልን ሲሆን የየክፍሎቹ ሀላፊዎች ደግሞ በዝርዝር አስጎበኝተውናል። እኛም ብዙ ብዙ ጠቃሚ ትምህርትና ልምድ ያካበትንበትን ጉብኝት አጠናቀን የጨረስን ሲሆን የኮሌጁ ዲኖችና የማኔጅመንት አባላት በሙሉ ላደረጋችሁልን አቀባበልና ላሳያችሁን ወንድማዊ ፍቅር ና ሽኝት እጅግ አድርገን እናመሰግናለን።
12/05/2026
ለኮሌጁ ሰልጣኞች ስልጠና ተሰጠ፡፡
ደሴ፡- ግንቦት4/2018ዓ.ም (ወስፖኮ)
የወ/ሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለጨርቃጨርቅና አልባሳት የትምህርት ዘርፍ ሰልጣኞች በEASE ፕሮጀክት ድጋፍ በgreen skill ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ ፡፡
ስልጠናው በኮሌጁ የስኂን ግቢ አስተባባሪ አቶ ታደሰ እሸቴ አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን
በኮሌጃችን EASE ፕሮጀክት ድጋፍ በሶስቱ የትምህርት ክፍሎች ማለትም በኤሌክትሪክሲቲ፣አይሲቲና ጨርቃጨርቅና አልባሳት በኩል የኮሌጁ የስልጠና ሂደት የሚያግዙ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውንእንደሆነ ገልፀው ይህ የgreen skill ስልጠናም የዚህ አንዱ አካል ነው ብለዋል፡፡
10/05/2026
https://docs.google.com/document/d/1L-vuOFHs9F2Zreo2I6e5zjFWvB-YrXqB0ZureajQoJ0/edit?usp=sharing
ይፋዊ የሥልጠና ጥሪ፡ የለስላሳ ክህሎት (Soft Skills) ድልድይ ሥልጠና ይፋዊ የሥልጠና ጥሪ፡ የለስላሳ ክህሎት (Soft Skills) ድልድይ ሥልጠና የEASE - Skills for Jobs (ቂያስ) ፕሮጀክት እንኳን ደስ አላችሁ! በመካከለኛ ደረጃ የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና (Intermediate Digital Skills Trainin...
07/05/2026
ለሰልጣኞች ኦረንቴሽን ተሰጠ፡፡
ደሴ፡-ሚያዚያ 29/2018ዓ.ም (ወስፖኮ)
በኢፌዴሪ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር (MoLS) እና በኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት (EDI) አማካኝነት በአለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የሚተገበረው የEASE (Education and Skill for Employability) ፕሮጀክት ሰላም ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና ወ/ሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በቅንጅት ለስልጠና ለተመረጡ ሰልጣኞች ኦረንቴሽን ሰጥተዋል።
በዚህ መርሃ-ግብር ሰልጣኞች ስለሚወስዱት የዲጂታል ክህሎት (Intermediate Digital Skills) ማለትም ስለ Graphic Design፣ Web Development፣ UI/UX Design እና Hardware Maintenance ሰፊ ግንዛቤ እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን ከስልጠናው በኋላ ቢያንስ 80% ሰልጣኞች በቋሚ ስራ ወይም በራሳቸው ስራ እንዲሰማሩ የሚደረግ መሆኑም ተብራርቷል፡፡ በተጨማሪም ሰልጣኞች ስራ ከጀመሩ በኋላም ለተከታታይ 3 ወራት የድጋፍ እና ክትትል ስራ እንደሚሰራ ተገልጿል።
በመጨረሻም ይህ ስልጠና ወጣቶችና ሴቶች በገበያ ላይ ተፈላጊ የሆነ የዲጂታል እውቀት ኖሯቸው የራሳቸውንና የሀገራቸውን ኢኮኖሚ እንዲደግፉ ትልቅ በር የሚከፍት በመሆኑ ሰልጣኞች በስልጠናው ወቅት ሊኖራቸው ስለሚገባ ስነ-ምግባር እና ክትትል ዝርዝር ገለጻ ተሰጥቷል።
06/05/2026
የዲጂታል አማራ ኢንሸቲቭን በተመለከተ ግምገማ ተካሄደ፡፡
ደሴ፡-ሚያዚያ 28/2018ዓ.ም (ወስፖኮ)
በአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሮ አማካኝነት በተጀመረው ዲጂታል አማራ ኢንሸቲቭን በተመለከተ በምስራቅ አማራ ከሚገኙ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች፣ የግል ኮሌጆች እና የመምሪያ ትምህርትና ስልጠና ቡድን መሪዎች ጋር በወ/ሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወ/ሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሰለሞን ይመር ለእንግዶቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የአብክመ ስራና ክህሎት ቢሮ የተቋማት ብቃት ማረጋገጫ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሙላው ልመንህ በበኩላቸው በክልሉ ውጤታማ የሆነ የኢንሸቲቩ የስኬት ዘመን እንዲሆን ሁሉም ሊረባረብና የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
በመድረኩ ኢንሸቲቩን በመተመለከተ የተለያዩ ሰነዶች የቀረቡ ሲሆን ጥሩ አፈፃፀም ያላቸው ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ያላቸውን ልምድም አካፍለዋል፡፡
01/05/2026
ለኮሌጁ ሰልጣኞች ስልጠና ተሰጠ፡፡
ደሴ፡-ሚያዚያ 22/2018ዓ.ም (ወስፖኮ)
የወ/ሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአይሲቲ የትምህርት ዘርፍ ሰልጣኞች በEASE ፕሮጀክት ድጋፍ በgreen skill ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ ፡፡
ስልጠናው በኮሌጁ የስኂን ግቢ አስተባባሪ አቶ ታደሰ እሸቴ አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን
በኮሌጃችን EASE ፕሮጀክት ድጋፍ በሶስቱ የትምህርት ክፍሎች ማለትም በኤሌክትሪክሲቲ፣አይሲቲና ጋርመንት በኩል የመማር ማስተማር ሂደቱን የሚያግዙ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውንና እየተከናወነ እንደሆነ ገልፀው ይህ የgreen skill ስልጠናም የዚህ አንዱ አካል ነው ብለዋል፡፡
01/05/2026
የጥራት ስራ አመራር ስርዓትን አስመልክቶ ስልጠና ተሰጠ፡፡
ደሴ፡-ሚያዚያ 22/2018ዓ.ም (ወስፖኮ)
በወይዘሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የጥራት ስራ አመራር ስርዓትን አስመልክቶ Education and Skill for Employment Project (EASE) ባደረገው የገንዘብ ድጋፍ አማካኝነት ለጥበቃና ለፅዳት ሰራተኞች የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠና ተሰጠ ፡፡
ስልጠናዉን የኮሌጁ ምክትል ዲንና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አስተባባሪ አቶ አያሌው መኮነን በመክፈቻ ከፍተዉታል።
ስልጠናው በቀጣይ ለሚደረገዉ ሰርቪላንስ ኦዲት ሰራተኞችን ለማነቃቃት ታስቦ የተሰጠ ሲሆን ሰልጣኞች ከስልጠናው በኃላ ስለ ISO 9001:2015 ከዚህ ቀደሙ በተሻለ በቂ እውቀት ይይዛሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡
ስልጠናዉ በኮሌጁ ኮሊቲ ማናጀር አቶ ጀማል አህመድና በኮሌጁ የላይብረሪ ቡድን መሪ አቶ ቶፊቅ መሀመድ አማካኝነት ተሰጥቷል ።
30/04/2026
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the school
Telephone
Website
Address
Dessie
54