03/04/2026
Dessie special boarding school
Yehunie Woldu Metasbia Dessie Special Boarding
03/04/2026
28/02/2026
ይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት Yihunie woldu metasebiya Dessie Special Boarding School:
https://www.facebook.com/share/1Ho8xDJ2DF/
የትምህርት ቤቱን የተሟላ መረጃ የያዘ ድረ ገፅ ማበልፀግ ችለናል" የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ ተማሪዎች ።
ደሴ፣ የካቲት 20/2018 ዓ.ም (አሚኮ ደሴ) ተማሪ ነብዩ ኑርልኝ እና ሀናን አህመድ የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የ12ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው ። በትምህርት ቤቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ አባል የሆኑት ተማሪዎቹ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን እያዳበሩ ይገኛሉ። ዘመኑ የቴክኖሎጂ በመሆኑ ከቴክኖሎጂ ጋር መተዋወቅ የግድ መሆኑን ተማሪዎቹ ያስረዳሉ።
በትምህርት ቤታቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ አባል በመሆናቸው የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውንና ስለቴክኖሎጂ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ በመቻላቸው በተለይም ከፕሮግራሚንግ እና ከአርዲኖ ባገኙት እውቀትም የትምህርት ቤቱን የተሟላ መረጃ የያዘ ድረ ገፅ ማበልፀግ እንደቻሉ ነው የገለፁት ።
የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ ተጠሪና የአይ ሲ ቲ መምህር ጀማል ሁሴን በበኩላቸው በክበቡ በአባልነት እየተሳተፉ የሚገኙ ተማሪዎች የኮምፒዩተር አጠቃቀም ክህሎታቸውን ማሳደግ ችለዋል ነው ያሉት። ተማሪዎቹ በተለያዩ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውድድሮች እየተሳተፉና እያሸነፉ እንደሚገኙም አስረድተዋል ።
የት/ት ቤቱ ተማሪዎች በቴክኖሎጂ የተሻለ ግንዛቤና ክህሎት እንዲያዳብሩ ትምህርት ቤቱ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ደግሞ የት/ት ቤቱ ም/ር መምህር ፍቅር በላይ ናቸው ። ተማሪዎቹ የቁሳቁስ እጥረት ሳይበግራቸው እየሰሩ ነው ያሉት አቶ ፍቅር የተሟላ ግብአት ቢያገኙ የተሻለ መስራት የሚያስችል አቅም ያላቸው መሆናቸውን አንስተዋል። የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበቡን ለማጠናከር ድጋፍ እንዲደረግም አቶ ፍቅር ጥሪ አቅርበዋል ።
ዘጋቢ፦ ከድር አሊ
የአሚኮ ደሴ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
#ደሴ #አሚኮ #ዜና #ልዩአዳሪትምህርትቤት #ሳይንስናቴክኖሎጂ
ደስ ይላል በርቱ
30/11/2025
የይሁኔ ወልድ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ተማሪዎች
MESOB አንድ ማዕከል አገልግሎት እና የደሴ ከተማ አስተዳደር የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ጎበኙ
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
በደሴ ከተማ አስተዳደር የስጀመረውን የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ያለበትን ሁኔታ እና MESOB አንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ በከተማ አስተዳደሩ አይሲቲ ባለሙያ በአቶ ናትናኤል አማካኝነት የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ገለፃ ልምድ ልውውጡ ተደርጓል።
ወግዲ ወረዳ 20 ኩንታል ጤፍ ለይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ድጋፍ አደረገ።
ደሴ፣ መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም (ደቡብ ወሎ ኮሙዩኒኬሽን)
በደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ 20 ኩንታል ጤፍ ለይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ድጋፍ አድርጓል።
የተደረገው ድጋፍ ከወረዳው ማኅበረሰብ የተሰባሰበ መሆኑን የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አህመድ ጋሎ ተናግረዋል። ለትምህርት ቤቱ የሚደረገው ድጋፍ በሌሎች ወረዳዎችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ኃላፊው የገለጹት።
23/09/2025
New entery grade 9 students 2018 E.c
15/09/2025
15/09/2025
" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
ሚኒስትሩ ፥ " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና በተናገሩበት ወቅት 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ብለዋል።
ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Contact the school
Telephone
Website
Address
Dessie