Dessie special boarding school

Dessie special boarding school

Share

Yehunie Woldu Metasbia Dessie Special Boarding

Photos from Wollo University's post 03/04/2026
Photos from አሚኮ ደሴ AMECO Dessie's post 28/02/2026

ይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት Yihunie woldu metasebiya Dessie Special Boarding School:
https://www.facebook.com/share/1Ho8xDJ2DF/

የትምህርት ቤቱን የተሟላ መረጃ የያዘ ድረ ገፅ ማበልፀግ ችለናል" የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ ተማሪዎች ።

ደሴ፣ የካቲት 20/2018 ዓ.ም (አሚኮ ደሴ) ተማሪ ነብዩ ኑርልኝ እና ሀናን አህመድ የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የ12ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው ። በትምህርት ቤቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ አባል የሆኑት ተማሪዎቹ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን እያዳበሩ ይገኛሉ። ዘመኑ የቴክኖሎጂ በመሆኑ ከቴክኖሎጂ ጋር መተዋወቅ የግድ መሆኑን ተማሪዎቹ ያስረዳሉ።

በትምህርት ቤታቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ አባል በመሆናቸው የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውንና ስለቴክኖሎጂ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ በመቻላቸው በተለይም ከፕሮግራሚንግ እና ከአርዲኖ ባገኙት እውቀትም የትምህርት ቤቱን የተሟላ መረጃ የያዘ ድረ ገፅ ማበልፀግ እንደቻሉ ነው የገለፁት ።

የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበብ ተጠሪና የአይ ሲ ቲ መምህር ጀማል ሁሴን በበኩላቸው በክበቡ በአባልነት እየተሳተፉ የሚገኙ ተማሪዎች የኮምፒዩተር አጠቃቀም ክህሎታቸውን ማሳደግ ችለዋል ነው ያሉት። ተማሪዎቹ በተለያዩ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውድድሮች እየተሳተፉና እያሸነፉ እንደሚገኙም አስረድተዋል ።

የት/ት ቤቱ ተማሪዎች በቴክኖሎጂ የተሻለ ግንዛቤና ክህሎት እንዲያዳብሩ ትምህርት ቤቱ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ደግሞ የት/ት ቤቱ ም/ር መምህር ፍቅር በላይ ናቸው ። ተማሪዎቹ የቁሳቁስ እጥረት ሳይበግራቸው እየሰሩ ነው ያሉት አቶ ፍቅር የተሟላ ግብአት ቢያገኙ የተሻለ መስራት የሚያስችል አቅም ያላቸው መሆናቸውን አንስተዋል። የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክበቡን ለማጠናከር ድጋፍ እንዲደረግም አቶ ፍቅር ጥሪ አቅርበዋል ።

ዘጋቢ፦ ከድር አሊ

የአሚኮ ደሴ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

#ደሴ #አሚኮ #ዜና #ልዩአዳሪትምህርትቤት #ሳይንስናቴክኖሎጂ

ደስ ይላል በርቱ

Photos from Dessie special boarding school's post 30/11/2025

የይሁኔ ወልድ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ተማሪዎች
‎MESOB አንድ ማዕከል አገልግሎት እና የደሴ ከተማ አስተዳደር የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ጎበኙ
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
በደሴ ከተማ አስተዳደር የስጀመረውን የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ያለበትን ሁኔታ እና MESOB አንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ በከተማ አስተዳደሩ አይሲቲ ባለሙያ በአቶ ናትናኤል አማካኝነት የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ገለፃ ልምድ ልውውጡ ተደርጓል።

24/09/2025

ወግዲ ወረዳ 20 ኩንታል ጤፍ ለይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ድጋፍ አደረገ።

ደሴ፣ መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም (ደቡብ ወሎ ኮሙዩኒኬሽን)

በደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ 20 ኩንታል ጤፍ ለይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ድጋፍ አድርጓል።

የተደረገው ድጋፍ ከወረዳው ማኅበረሰብ የተሰባሰበ መሆኑን የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አህመድ ጋሎ ተናግረዋል። ለትምህርት ቤቱ የሚደረገው ድጋፍ በሌሎች ወረዳዎችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ኃላፊው የገለጹት።

Photos from Dessie special boarding school's post 23/09/2025

New entery grade 9 students 2018 E.c

15/09/2025
Photos from Amhara Education Bureau's post 15/09/2025
18/04/2025

" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

ሚኒስትሩ ፥ " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና በተናገሩበት ወቅት 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ብለዋል።

ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ


Want your school to be the top-listed School/college in Dessie?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address


Dessie