20/04/2023
ዘካተል ፊጥር በገንዘብ
ነቢዩ ﷺ ዘካተል ፊጥርን አንድ ቁና ተምር ወይም ገብስ ይሰጡ ነበር።
(ቡኻሪይ 1503)
ዘካተል ፊጥርን በገንዘብ መስጠት ይቻላል? የሚለውን በተመለከተ 3 ዓይነት አስተያየቶች አሉ።
♦️ አብዛኛው ዑለማዎች ነቢዩ ﷺ በእህል ስለሰጡ በእህል እንጅ በገንዘብ መሰጠት አይፈቀድም። መከተል ያለብን የነቢዩን ﷺ ተግባር እንጅ የሰዎችን አስተያየት አይደለም ይላሉ።
ከእነሱም መካከል ኢማም ማሊክ፣ ኢማም አሽ-ሻፊዒይ፣ ኢማም አህመድና ኢብን ሐዝም ይጠቀሳሉ።
♦️ ታላላቅ የታቢዒይ ዑለማዎች ደግሞ በገንዘብ ለውጦ መስጠት ይቻላል ብለዋል።
ከእነሱም መካከል ሐሰን አል-በስሪ፣ አጣዕ ኢብን አቢ-ረባህ፣ ዑመር ኢብን አብዱልአዚዝ፣ ኢማም ሱፍያን አስ-ሰውሪ፣ ኢማም አቡ-ሐኒፋ እና ኢማም ቡኻሪይ ይጠቀሳሉ።
(ሙስነፍ 4/37)
♦️ ሶስተኛው ለተቀባዩ ሰው በሚጠቅመው ሁኔታ በእህል ወይም በገንዘብ መስጠት ይቻላል የሚለው ነው።
ኢብን ተይሚያህ ስለዚህ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦
«ዘካተል ፊጥርን ተቀባዩ በገንዘብ ቢሰጠው የሚፈልግና የሚጠቅመው ከሆነ በገንዘብ ተምኖ መስጠት ይቻላል። ለምሳሌ 5 ግመሎች ያሉት ሰው አንድ በግ ዘካ እንዲያወጣ ተጥሎበታል። ነገርግን በአካባቢው በግ ከሌለ በገንዘብ ተምኖ መስጠት ይችላል። ሙዓዝ ኢብን ጀበል የየመን ሰዎችን ዘካ ሲቀበል ‹ከእህል ይልቅ በልብስ ቀይራችሁ ብትሰጡኝ ትችላላችሁ። ይሄ በመዲና ለሚገኙ ሙሐጅሮችና አንሷሮች የበለጠ ጠቃሚ ነው።› ብሏቸዋል። ይህም ዘካተል ፊጥርንም የበለጠ ጠቃሚ በሆነው መስጠት እንደሚቻል ያሳያል።»
(ፈታዋ ኢብን ተይሚያህ 25/82)
ይህንን ሃሳብ የደገፉ ዑለማዎች ነቢዩ ﷺ ዘሃተል ፊጥርን በእህል የሰጡበት ምክንያት አንደኛ በወቅቱ በአረቦች ዘንድ የገንዘብ ዝውውር አነስተኛ በመሆኑ፤ ሁለተኛ የገንዘብ አቅም በየጊዜው ስለሚለዋወጥ ዘካውን በስፍር ተምኖ ለማስቀመጥ እንዲረዳ ነው ይላሉ።
(አል-ሙግኒ 3/60)
♦️ ከዘመናችን ዑለማዎች መካከል ሸይኽ ሸልቱት እና አል-ቀርዷዊ በገንዘብ መስጠቱ የደገፉ ሲሆን፡-
👉 የዘካተል ፊጥር ዋና ዓላማው ሰዎች በዓሉን ተደስተው እንዲውሉ ለማድረግ በመሆኑ ሰውየው የበለጠ በሚደሰትበት መንገድ መስጠቱ እንደሚበልጥ
👉 በዘመናችን የገንዘብ ዝውውር የበዛበትና በገንዘብ ቢከፈል ለሰጭውም ለተቀባዩም ስለሚቀል
👉 እንዲሁም እህል ቢሰጣቸው እንኳን እነሱ መልሰው ሽጠው ወደ ገንዘብ መቀየራቸው ስለማይቀር ቀጥታ በገንዘብ ቢሰጥ ይበልጣል ይላሉ።
(ፊቅህ ወ ሂሳብ ዘካት አል-ፊጥር 15)
አላህ የበለጠ ያውቃል!
©ሰል ማን
07/09/2022
ጀነት ስንገባ የመጀመርያዎቹ ቅፅበቶች
______________________________
ልክ ጀነት ስንገባ ጅረቶች ከህንፃዎቹ ስር ሲፈሱ፣ በየ ርቀቱ የተተከሉ ከወርቅ እና ከሀር የተሰሩ ድንኳኖችን እና የበሰሉ ፍራፍሬዎችን ስንመለከት ስሜቱ ይለያል።
ከረጅም ዘመን በፊት ሙተው ከአይኖቻችን የተሰወሩ ወዳጆቻችንን ስንገናኝ፣ ልጅ ሲንከባከባት ቆይቶ በሞት ያጣትን እናቱን ድንገት ሲመለከት፣ ወላጆች በህፃንነቱ ሞቶባቸው ናፍቆቱ የግር እሳት የሆነባቸውን ልጃቸውን ከጀነት ሲገናኙት፣
ሙቶ የተለየን እና ለዘመናት መልኩ ከአይናችን አልጠፋ ያለው አባታችንን ድንገት ከጀነት ህንፃዎች ስር ከንግስናው ዙፋን በድሎት ተከብሮ ስናገኘው፣
ለዘመናት የአልጋ ቁራኛ ሁኖ ልባችንን የሰበረው በሽተኛው ወዳጃችን፣ ቤተሰባችን በጀነት ጎዳናዎች ከነሙሉ ጤንነቱ ሲደሰት ስንመለከት፣
ሁሌም በህይወት ውጣ ውረድ ፊታቸው በሀዘን የተሞሉ ወላጆቻችን በደስታ ፈክተው ጀነት ውስጥ በመላዕክት የክብር አጀብ ተከበው ስንመለከታቸው፣
ሽማግሌው አባታችን እና አያታችን ፈርጣማ ወጣት ሁነው፣ ዛሬ የምናያቸው አሮጊቶች እሚገራርሙ ማራኪ እና ፈታኝ ልጃ ገረድ ሁነው ከጀነት እልፍኞች ሲዘዋወሩ ስናይ፣
አርብ እለት የረሕማንን ዝያራ ለመታደም ስንሄድ እዝያው የናፈቁን ነቢያትቶችን፣ ሰሐባዎችን፣ ዑለማኦችን፣ በተለይ ደግሞ ነቢን ሰዐወ ተገናኝተን ስንዘይራቸው፣
ያን ሁሉ ቅጥፈቶቻችንን ይቅር ብሎ ጀነትን ያወረሰንን ጌታችንን አላህ ያለ ምንም ግርጆ ከፊታችን ስንመለከተው፣ ያለው የማይታመን የደስታ ስሜት ልዩ ነው።
ዒባዳ የለም ተጠናቅቋል፤ ጭንቀት የለም ሒሳብ አልቋል፤ ያ የጨለማ፣ የመጠላላት፣ የማስመሰል፣ የጦርነት፣ የመሸምገል፣ የድካም፣ የበሽታ፣ የመርፌ፣ የመድሃኒት....አለም አልቋል።
«ባሮቼ ሆይ! እኔ ስለናንተ ወድጃለሁ፤ መቼም አልጠላችሁም።» እያለ አላህ ሲያበስረን የደስታችን ድባብ ያኔ እንዴት ይሆን!?
Sefwan Sheik Ahmedin
01/09/2022
Allah is unique, and there is nothing like Allah - the sole Creator and Master of all things in the universe. Allah describes Himself in the Quran as being the First and Last, meaning there was nothing before Him and He will remain when everything else perishes. Allah is the Ascendant, the Supreme, and nothing is above Him. Allah is the Intimate and Knowing, who knows everything that happens, has happened, and ever will happen, and His knowledge is absolute.
27/08/2022
ሰውዬው ሌት ተ ቀን ዒባዳ እያደረገ ከጌታው ጋር ቅርበት ለመፍጠር ይጥራል። ከእለታት አንድ ቀን በሌሊት ተነስቶ ጌታውን ሲማፀን ኢብሊስ ይመጣ ና እንዲህ ሲል ሹክ ይለዋል፦‹‹እስከመቼ ነው አላህን ስትማፀን ከርመህ አንዲትም ምላሽ እማይመጣልህ? መቼ ነው ያንተ ዱዓህ ተቀባይነት አግኝቶ ውጥንህ ሚሰምረው?››
ባርያ ቅስሙ ተሰበረ፣ ሀሞቱ ፈሰሰ፣ ሞራሉ ተነካ፣ ከአምልኮውም ተዘናግቶ በብስጭት ጥላ ስር ተጠለለ።
ከእለታት አንድ ሌሊት በእንቅልፍ ተውጦ ሳለ የህልም ተጣሪ እንዲህ ሲልም ተጣራ፦‹‹ባርያ ሆይ! ስለምን ከአምልኮ ተቋረጥክ? ስለመቋረጥህ ምክንያት ይኖርህ?! ››
ባርያውም በህልም ሰመመን እየዋለለ እንዲህ ሲል ምላሽ ሰጠ፦‹‹አላህ ተማፅኖዬን አልሰማህ አለኝ፤ ምናልባትም እኔ ከደጃፉ የተባረርኩ እና የተጠላሁ መስሎ ታየኝ፤ ጠፋሁም››
ተጣሪውም እንዲህ ሲል ምላሽ ይሰጠው ጀመር፦‹‹በፍፁም ከደጃፉ አልተባረርክም። አላህን ማወደስህ እና መማፅንህ አላህ ዘንድ ተፈላጊነትህን እና ቅቡልነትህን ማመላከቻ ነው። ያ ባይሆንማ ምትሻውን ሰጥቶ ከደጃፉ ባባረረህ!
አላህም እንዲህ ይልኃል "እኔ ነኝ እኮ ወደ እኔ መዋደቅን እና እኔን ማውሳትን በልብህ ያስዋብኩልህ። ወደ እኛ መዋደቅህ እና እኛን ማውሳትህ በኛ ዘንድ በፍቅር የመሳብህ ውጤት እንጂ ሌላ አይደለም።
የዝንጉዎችን ልቦችማ! ወደኛ እንዳያስቡ እና ከደጃፋችን እንዳይዋደቁ ግርጆ አድርገንባቸዋል። በችግሮቻቸውም ግዜ ከደጃፋችን መዋደቅን አንለግሳቸውም"››
ያ ረብ ከደጃፍህ አዋድቀን!
Sefwan sheik ahmedin