01/04/2023
በ2015 የትም/ዘመን በ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ሀገር አቀፍ የተፈታኞች ምዝገባን አስመልክቶ ከፈጻሚዎች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ።
የምክክር መድረኩን የከፈቱት የምስ/ጐ/ዞብ ትምህርት መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ ደመላሽ ታደሰ እንደገለጹት በዘመኑ ለሚሰጠው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና የDRS ምዝገባን አስመልክቶ ከአስፈታኝ ት/ቤት ር/መምህራን፣ ከየት/ቤቱ ተመርጠው ለመጡ መዝጋቢዎች እና የወረዳ ፈተና ጉዳይ ባለሙያዎች እና ሌሎች ለሚመለከታቸው አካላት ምዝገባውን አስመልክቶ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ አጽንኦት በተሞላበት ሁኔታ ገልጸዋል።
ኃላፊው አያይዘውም ስራውን በትኩረት አለመፈጸምና ተገቢውን ጥንቃቄ አለማድረግ በተማሪዎች ህይወት ላይ የሚያስከትለውን ተጽእኖ አብራርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በምክክር መድረኩ የተገኙ ር/መምህራን፣ ለተማሪዎች አስፈላጊውንና የሚቻለውን ድጋፍ ሁሉ እንዲደረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር (ከወላጆች፣ ከወረዳው አስተዳደርና ከት/ጽ/ቤቶች ጋር በመመካከር መርሀ ግብሮች ተዘጋጅተው ከባለፈው በተሻለ መልኩ ፈተናው እስከሚሰጥበት እለት ድረስ የቀረውን ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም ወደ ተግባር እንዲገባም አቶ ደመላሽ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የምስ/ጐ/ዞን ትምህርት መምሪያ የፈተና ጉዳዮች ባለሙያ የሆኑት አቶ ደሳለኝ አበበ በዚህ አመት ለሚሰጠው አገር አቀፍ ፈተና በምዝገባ ወቅት ባለፈው አመት የተአእተዋሉ ችግሮችን በማንሳትና ለተሳታፊዎች በማሳየት ችግሮቹ እንዳይደገሙ አሳስበዋል።