09/09/2022
ዜና ኦርቶዶክስ
ዲማና ደብረወርቅን አንድ ለማድረግ የተጠራ ሴራ ለበስ ጉባኤ ይበልጥ የሚያለያይ ሆኖ ተጠናቀቀ ።
ማህበረ ቅዱሳንና ዲማ ካህናት የመከፋፈል ሴራ ጠንስሰው ከመነሳታቸው በፊት የምስራቅ ጎጃም ኦርቶዶክሳውያን ካህናቱ ክህነት ከአንድ ጳጳስ ተሹመው፤ በአንድ ቤተ ክርስቲያን ቀድሰው፤ ሰው ሲሞትባቸው አብረው ፍትሐት ፈተው ፤ ሃይማኖታዊ በዓላትን አብረው አክብረው፤
ምእመናኑም በሃይማኖትም በሌላውም ማህበራዊ ኑሮ አብረው ኖረዋል ለነዚህ አባባሎች ትቂት ምስሌዎች እንጥቀስ
1ክህነት ከአንድ ጳጳስ መቀበል
አቡነ ዘካርያስ የምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነበሩጊዜ ህዳር 7 ቀን 1996 ዓ.ም በሞጣ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዲቁና የሚሾሙ ወጣቶች ተሰባስበው ጳጳሱ ሹመቱን ሊሰጧቸው ሲሉ የተሰበሰቡትን ወጣቶች እስኪ ቅባት የሆናችሁ እጃችሁን አውጡ አሏቸው ወጣቶችም እጃቸውን ሲያወጡ ቅባት ነን ብለው እጃቸውን ያወጡት ካላወጡት በእጅጉ በለጡ ጳጳሱም ከዚህ በኋላ ምንም ተጨማሪ ቃል ሳይናገሩ ወጣቶችን ሾሟቸው።
አቡነ ዘካርያስ በኋላ ነው አቋማቸውን ቀይረው የከፋፋዩ ቡድን ፊት አውራሪ የሆኑ።
ወልደ አብ የተባለውን መጽሐፍ ራሳቸው ፈቅደው የገንዘብ ድጋፍ አድርገው ማሳተማቸው በተደጋጋሚ ተገልጿል መጽሐፉን ቀድመው ያወገዙም እርሳቸው ናቸው ።
2 በሀዘን እና በደስታ አንድ መሆን
የምስራቅ ጎዳም ኦርቶዶክሳውያን በሀዘን በደስታ አንተ ቅባት ነህ አንተ ካራ ነህ ተባብለው አይለያዩም በኀዘን በደስታ አብረው ይካፈላሉ። በዚህ ግንኙነታቸው ሊቃውንቱ በቅኔ እየተቀላለዱ የጥበብ ችሎታቸውን የሚያሳዩበት አጋጣሚም ብዙ ነው አንድ ምሳሌ እናንሳ
ቅባት ከሚባሉት ኦርቶዶክሳውያን የደብረ ወርቅ ሊቅ የተበሩ አለቃ ተሰማ የተባሉ ሊቅ ሞተው ካራ የሚባሉት የዲማ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንትም በፍትሐቱ ላይ ይገኛሉ በዚህን ጊዜ አንዱ የዲማ ሊቅ ቅኔ ሲቀኙ
እምልባ ኃዘነት ምድረ ደብረ ወርቅ ዘማ
አኮኑ ተሰብረ የቅቤ ቅሏ ተሰማ ።
አሉ የቅኔው ጥቅል ሀሳብ
"የቅቤ ቅሏ ተሰማ ስለተሰበረባት አመንዝራይቱ የደብረ ወርቅ ምድር ከልብ አዘነች" ማለት ነው።
የደብረ ወርቁ ሊቅ ሲመልሱ ደግሞ
ሐመደ እቶን ይመስል ገፀ ዘማዊት ዲማ፣
እስመ ኢረከበት ቅብዐ እምነ ባእል ተሰማ።
ብለው መለሱ ። የመልሱ ቅኔ ሀሳብ
"ከባለፀጋው ተሰማ ቅቤ ስላላገኘች ዘማዊት ዲማ ፊቷ አመድ ይመስላል" ማለት ነው።
በደስታም በሀዘንም አብሮነታቸውን የሚያሳይ አንድ ሌላ ምሳሌ እንጨምር በሞጣ ከተማ አቅራቢያ በሚገኝ ቦታ ሁለቱም ወገኖች ማለትም ቅባት ኦርቶዶክሶች እና ካራ ኦርቶዶክሶች
(ተዋህዶ ያላልናቸው ተዋህዶ የሚለው ጥንት ጸጋዎች የሚጠሩበት እንጅ የነርሱ ስም ስላልሆነ ነው)
አብረው የሚገለገሉበት አንድ ቤተክርስቲያን ነበር ከጊዜ በኋላ ግን የቅባት ተዋህዶ ወገኖች የብቻችን መስራት አለብን ብለው ሌላ ቤተ ክርስቲያን ይሰራሉ በኋላ የጥምቀት በዐል ሲያከብሩ ግን ሕዝቡ የመጀመሪያውን ቤተክርስቲያን ታቦት ተከትሎ ስለሄደ የአዲሱ ይቀዘቅዛል ይህ የሆነባቸው የአዲሱ ቤተክርስቲያን ሽማግሎች የመጀመሪያው ቤተክርስቲያን ታቦት እንደገባ ሕዝቡ ተመልሶ የአዲሱን ቤተክርስቲያን ታቦት እንዲያጅብ ሲለምኑት ሕዝቡ ተመልሶ አጅቦ አስገባው።
እነዚህን በመሰሉ እና ሌሎችም ጉዳዮች በአንዲት ቤተክርስቲያን ውስጥ አብሮ የሮረ ህዝብ ነው ሊቁ መላከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬም ሁለቱ ወገኖች እንደወንድማማች አብረው የሚኖሩ መሆናቸውን እንደሚከተለው ገልጸዋል ።
"ወንድማማቾች ከእናት ከአባታቸው ቤት ሲያድጉ ለጊዜው መምኑም በምኑም ቢጋጩ መልሰው ወንድሜ ወንድሜ ተባብለው እንደሚሳሳሙት …ያለ ነው እንጂ ከአያት ከቅድመ አያት የወረደ ጥንተ ባላጋራ ምክንያት አድርጎ ሊገባበትና ሊጠቀምበት የሚችል የበረታ ጠብ አይደለም የበረታ የሚያለያይ ጠብ ካለመሆኑም የተነሳ ሁሉም ወገኖች በእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ስር ይኖራሉ።
ሰው ሆይ(መድሎተ አሚን ) ገፅ 73-74
እንዲህ በክህነት ፣ በማህሌት በደስታ በሐዘን አብረው የኖሩ የምስራቅ ጎጃም ኦርቶዶክሳውያን ማህበረ ቅዱሳን እና የዲማ ካህናት ቅባቶች ከሆናችሁ ያላመናችሁ ስለሆናችሁ መጠመቅ አለባችሁ በማለት ይዘውት በተነሱ ከፋፋይ ተልኮ አንድ ሆነው የኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ከሁለት እንደተከፈሉ ይታወሳል
ይህ በእንዲህ እንዳለ በሲኖዶስ ደረጃ በተደጋጋሚ ተሞክሮ ያልተሳካውን የአንድነት ሙከራ አንድ እናደርጋለን የሚሉ ወገኖች አንድ እናደርጋለን በማለት አጋጣሚውን በመጠቀም የገንዘብ መዝረፊያ አድርገውታል።
ለዚህ ከተጠቀሙባቸው የተወሰኑትን እንጥቀስ ባለፈው መጋቢት ወር ላይ አቡነ አብርሃም የደብረ ማርቆስ ከተማ ጳጳስ አቡነ ያሬድን ጋልበው ደብረወርቅ ከተማ መጥተው የደብረ ወርቅን ህዝብ ጥያቄ ለሲኖዶስ አቅርቤ ጥያቄው እንዲመለስ አድርጌ አንድነት እንዲፈጠር አደርጋለሁ ብለው ጥያቄዎችን የያዘውን ሰነድ ተረክበው ሄደው ራሳቸው እንዳይቀርብ አደረጉ ። በዚህም የደብረወርቅን ህዝብ አታለሉት ።
የደብረ ወርቅ ህዝብ ለሲኖዶስ ያቀረበውን ጥያቄ መረጃ ዘቤተክህነት በተሰኘው የዩቲብ ቻናላችን ያገኛሉ ።
ከዚያ በኋላ ደግሞ በማህበረ ቅዱሳን ቁጥጥር ስር ያለው የደብረ ማርቆስ ከተማ ሀገረ ስብከት ሰራተኞች ወደ መርጡለ ማርያም ሄደው የመርጡለ ማርያም ህዝብ በቆጋ አባቶች ላይ በጥላቻ እንዲነሳ ቅስቀሳ አድርገው አልሳካላቸው ሲል አንድ እንሁን በሚል ከመርጡለ ማርያም ከተማ ሽማግሌ መርጠው ወደ ጉንደወይን ህዝብ ላኩ የጉንደ ወይን ከተማ ህዝብና ካህናትም የሚመለከታቸውን ወገኖች ጠርተው ከተመካከሩ በኋላ የተላኩ ሽማግሎችን አክብረው ተቀብለው አንድነቱን አንጠላውም መጀመሪያም ተገፍተን ነው የተለየን አሁን ግን ጉዳዩ በሲኖዶስ ደረጃ የደረሶ እና ሲኖዶሱም ስላወገዘን ንግግረ ካስፈለገን በሲኖዶስ ደረጃ ነው መሆን ያለበት ብሎ መለሳቸው ።
አሁን ደግሞ የዲማና ደብረወርቅን ልዩነት እንፈታለን በሚል ስብሰባ ጠርተው ስብሰባው ይበልጥ በሚያለያይ ውሳኔ ተጠናቋል ።
ስብሰባው የተደረገው ፦ በ27/ 12 /2014
የስብሰባ ቦታ፦ ጠልማ ማርያም
ተሰብሳቢዎች፦
ከደብረቀርቅ
1, ደብረወርቅ ማርያም ገዳምን ወክለው የሔዱት የሰበካ ጉባኤ አባላት ፣ ካህናት ፣ ወጣቶችና የሀገር ሽማግሌዎች፣
2 የእናርጅ እናውጋ ወረዳ ቤተክህነት
ከዲማ
1, ዲማ ገዳም
ከቢቸና አጥቢያዎች የተውጣጡ ተወካዮች
2 እነማይ ወረዳ ቤተክህነት እና ስብሰባውን ያዘጋጀው ሀገረ ስብከቱ ናቸው
በዚህ ስብሰባ የተያዘው አጀንዳ
, የሁለቱ ገዳማትን ልዩነት መፍታት የሚል ሲሆን ልዩነቱን በማባባስ ተጠናቋል እንዲት ከተባለ ደግሞ
ከደብረ ወርቅ ተሰብሳቢዎች ዳግም ጥምቀት እያጠመቃችሁ ስለሆነ ይሔም በሲኖዶስ የተወገዘ ስለሆነ ይህ እንዲቆም ጠይቀዋል። ///////
ዲማዎች ነገሩን ሸፋፍነው ለማለፍ ሞክረዋል። " እኛ ከእስልምናና ከሌላ ሀይማኖት የመጣን አጥምቀናል እንጂ ሁለተኛ አላጠመቅንም" የሚል የማያዘልቅ መልስ ሰጡ የተሰጠው መልስ የመሸፋፈን መሆኑን የተረዱት ደብረ ወርቆች
ይሔንን ጉዳይ ግልጽ ሆኖ መነጋገር ስላስፈለገ እውነቱ መውጣት አለበት ከደብረወርቆች "አንገቱ ላይ ማተብ እያያችሁበት ያረገውን አየበጠሳችሁ ሌላ አላሰራችሁም ወይ? ለዚህ ራሳችን ምስክር ነንና አትክዱም" መካድ አትችሉም ብለው አፋጠዋቸዋል ። የዲማወችን ውሸት በማያፈናፍን ሁኔታ ያጋለጠባቸው እና ያልጠበቁት ሀፍረት ላይ የጣላቸው ደግሞ ራሳቸው ያሳተሙት መጽሐፍ ነበር መጽሐፉ ብርሃነ ሊቃውንት ዘዲማ የሚል ርእስ ያለው ሲሆን ሐምሌ 2014 ዐ . ም የታተመ ነው በዚህ መጽሐፍ ላይ የቅባት ትምህርት ተከታዮችን እና ደብረ ወርቅ ገዳምን የሚያክፋፉ እና ዲማዎች ቅባቶችን ማጥመቃቸውን የሚያረጋገጡ ጽሁፎች ይገኙበታል ከነዚህ ቃላት ።"በገጽ 25 ላይ የሚከተለው ሰፍሯል
" ብዙ የቅባትና ትቂት ደግሞ የእስልምና እምነት ተከታዮችን አስተምረው አጥምቀው መልሰዋል ካጠመቋቸው መካከል እግዚእኃረያ የተባለችው በዲማ ጊዮርጊስ ዘንድ ትታወቃለች "
እናም ዲማዎች ዳግም አላጠመቅንም ብለው ለማጭበርበር ሲሞክሩ ደብረ ወርቆች መጽሐፉን አውጥተው አንብበው አሳፍረዋቸዋል ።
ይህ መሸፋፈን የማያዋጣ መሆኑን የተረዱት የሚማው መምህር ግን
"ይሔንን ጥምቀት እኛ አልጀመርነውም ድሮ የአባቶቻችንን ፈለግ ተከትለን ነው እየፈጸምን ያለነው ጥፋት ነው የሚለኝ ካለ ቀኖና እወስድበታለሁ ብለው ፍርጥ አድርገውታል ።
እኚሁ መምህር እማሳረጊያ ጸሎት ላይም ሲናገሩ " በቅብዐተ መንፈስ ቅዱስ ከበረ የሚለው ተወግዟል። የተወገዘ ደግሞ መጥፋት አለበት። ተዋህዶ ነን ካላችሁ አናጠምቃችሁም" በሚል ሀሳብ ደምድመውታል
የደብረ ወርቆች መልስ
ዳግም ጥምቀትን የማታቆሙ ከሆነ እኛም በገዳማችን ደብረ ወርቅ ህዝብ ፊት ቆመን ዲማ ሄዶ የቆረበ ፣ ክርስትና ያስነሳ ፣ የመነኮሰ ከቤተክርስቲያኗ ምንም አይነት መንፈሳዊ አገልግሎት እንደማያገኝና እንደምናወግዝ እወቁልን የሚል ሀሳብ ተናግረው ተለያይተዋል ። አንድ ለማድረግ የተጠራ ጉባኤ ይበልጥ በሚያለያይ ውሳኔ ተጠናቀቀ ። ማለት ይህ ነው ።
ይሄን ጉባኤ የተጠራ ዲማዎችም ደብረወርቆችም ፈልገውት አይደለም ማህበረ ቅዱሳን በተቆጣጠረው የደብረ ማርቆስ ከተማ ሀገረ ስብከት ስር አቡነ ያሬድ የሰላም ኮሚቴ ብለው በማህበረ ቅዱሳን አባላት ያቋቋሙት ቡድን የሚያደርገው የገንዘብ መዝረፊያ ስልት ነው ። ይህ ቡድን አንድ ለማድረግ ፣ ልዩነቶችን ለመፍታት እያለበየወረዳው እንደዚህ አይነት ስብሰባዎችን እየጠራ ገንዘብ ይዘርፋል ለዚህ ዘረፋው መሳሪያ ሆነው በወረዳዎች ለሚያስተባብሩለትም ገንዘብ ይከፍላል።
ለምሳሌ ደብረ ወርቅ ከተማ ውስጥ የዚህ ቡድን መሳሪያ ሆኖ የሚያገለግለው አለምነው አዘነ የተባለ ቄስ ነው ። ይህ የዘረፋ ስልት በሌሎች ወረዳዎችም እንደሚቀጥል ውስጥ አዋቲዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋ የደብረ ማርቆስ ካህናትና ህዝብ ይሄን ዘራፊ ቡድን በቃህ በማለት ዘረፋውን ሊያስቆም ይገባል ሰንሰለቱ ከወረዳ ቤተክህነት እስከ ጠቅላይ ቤተክህነት የተሳሰረ ነው።
በዩቲብ እንገኛለን መረጃ ዘቤተክህነት ብለው ይፈልጉን