Amhara North Shewa Zone Communication

Amhara North Shewa Zone  Communication ሰሜን ሸዋ ዞን በግምት 8 degree 38’ --- 10 degree 42’ ሰሜን ላቲቲዩድ 38 degree 40’ – 40 degree 43’ ሎጊትዩድ

ደብረብርሃን የተቆረቆረችውና የተሰየመችው ከ5ዐዐ ዓመት በፊት በ1446 ገደማ በአፄ ዘርዓያዕቆብ /1426 – 146ዐ/ ነበር፡፡
ከተማዋ ቀድሞ ደብረ ኢባ በመባል የምትታወቅ ሲሆን የንጉሱ የግራ በአልቲሐት ርስት ነበረች፡፡
በ144ዐ ዎቹ መጀመሪያ ንጉሱ ጐበኟትና ደስ ስለተሰኙባት የድንኳን ከተማቸውን ከተሙባት፡፡ አሁንም የስላሴ ቤ/ክርስቲያን በሚገኝበት ቦታ ላይ ሶስት አብያተ ክርስቲያናት ነበሩ፡፡
ከተማዋ ስያሜዋን ያገኘችው ለስዕልና ለመስቀል አንሰግድም የሚሉ የእስጢፋኖስ ተከታዮች በ1446 ከንጉሱና ከካህናቱ ጋር በጉባኤ ክርክር ላይ አቋማቸውን አንለውጥም በማለታቸው ምላሣቸው ተቆርጦ እንዲገደሉ ተፈረደባቸው ፍርዱ በተፈፀመ በ

38ኛው ቀን በስላሴ ቤ/ክርስቲያን “ ብርሃን “ ታዬ ይባላል፡፡ ንጉሱም በመዋዕለ ዜናቸው ይህንኑ ማየታቸውን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡ እስጢፋኖሳውያኑ ላይ ለተፈረደው ቅጣት ለትክክለኛነቱ የታየው ብርሃን አምላካዊ ማረጋገጫ ነው በማለት ንጉሱ ከተማዋን ደብረብርሃን ብለው መሠየም ለ14 ዓመት በከተማዋ ኖረውባታል፡፡

ለሚዲያ እና ህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወራና ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ከየተቋማቱ ለተው...
21/08/2026

ለሚዲያ እና ህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወራና ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ከየተቋማቱ ለተውጣጡ የህዝብ ግንኙነት ፎካል ፐርሰን አባላት በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወ/ሪት ኤፍራታ ሸንቁጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዙሪያ ያለብንን የቴክኖሎጂ እውቀት በማዳበር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን ይጠበቅብናል፤በተቋማችን የሚሰጠውን ስልጠና በተገቢው መከታተል ያስፈልጋል ብለዋል።

ስልጠናው በጽህፈት ቤቱ የአይ ሲቲ ባለሙያ አቶ ዘላለም ተስፋዬ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)ዙሪያ በተግባር የተደገፈ ስልጠና ሰጥቷል።

የስልጠናው ተሳታፊዎችም በበኩላቸው የሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) ግንዛቤ ማስጨበጡና ከዘመኑ ጋር አብሮ እንድንዘምን ከማድረጉ ባለፈ ስራን የማቅለል ትልቅ አስተዋፅኦ ያለው ነዉ፤ አጠቃቀማችንን በማስተካከል የተሻለ ስራ ለመስራት የሚጠቅም ቢሆንም ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እንዳያመዝን መጠንቀቅ ይገባል ብለዋል።

ተቋማት በክላስተር ተደራጅተዉ  አፈፃፀማቸዉ በቅርብ ክትትል መመራታቸዉ  ዉጤታማ  ለመሆን ያስችላል  ሲሉ የወረዳዉ  ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታዉ በላይግዛዉ ተናገሩ ።   ደብረ ብርሃን፤ ነሃሴ...
21/08/2026

ተቋማት በክላስተር ተደራጅተዉ አፈፃፀማቸዉ በቅርብ ክትትል መመራታቸዉ ዉጤታማ ለመሆን ያስችላል ሲሉ የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታዉ በላይግዛዉ ተናገሩ ።

ደብረ ብርሃን፤ ነሃሴ15 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) በሰሜን ሸዋ ዞን የመርሐቤቴ ወረዳ አስተባባሪና ጠቅላላ አመራሮች በተገኙበት በክላስተር የተለዩ ተቋማት የተግባራት አፈፃፀም ተገምግሟል።

በክላስተር ተለይተው ድጋፍና ክትትል የሚደረግላቸው ተግባራት በቀጣይነት ከወረዳ ተቋም እስከ ገጠር ቀበሌ መዋቅር ድረስ ድጋፉን አጠናክሮ የሚያስቀጥል ውይይት ተካሒዷል።

በግምገማዉ ከግብዓት ስርጭት፣የኢሊኖ ስጋትን ቅድመና መከላከል ስራ፣ገቢ አሰባሰብ ሂደትም፣የመንገድ ትራንስፖርት አገልግሎት አሠጣጥ፣የመንግስት ሰራተኞችን የቆጠራ አፈፃፀም፣የተማሪዎች ምዝገባ ሂደት፣ የኑሮ ዉድነትን ገበያ ለማረጋጋት የተሠሩ ሰራዎች፣የበጎ ፈቃድ ስራዎችና የወጣቶችና ሴቶችን በማንኛዉም ዘርፍ ተጠቃሚ ለማድረግ የተሠሩ መልካም ስራዎች ላይ ያሉ ዉጤቶችን ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሔዎች በክላስተር አሰተባባሪ አመራሮችና በተቋም ኋላፊዎች በተገቢዉ ቀርበዋል።

የየክላስተሩ ተግባራት አፈፃፀም ሁኔታን በተጨባጭ እስከ ተቋማት ባለሙያዎች ድረስ ማረጋገጥ እንደሚገባ በመድረኩ የተገለፀ ሲሆን የገጠር ፣ የከተማ፣ የማህበራዊ፣ የመሠረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር ተቋማትን ለይቶ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ መጀመሩ ውጤት እያመጣ መሆኑም በውይይቱ ተመላክቷል።

የወረዳዉ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኋላፊ አቶ በቂነዉ ስለሺ እንደገለፁት ተቋማቶች የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደርና የአሰራር ጥያቄዎችና የህዝብን ጥያቄ የምንመልሰው ላስቀመጥናቸው ግቦች ተገዢ ሆነን በቅንጅትና በትብብር ስንሰራና የምናስተዳድረውን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ስናውል ነው ብለዋል።

የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታዉ በላይግዛዉ ሴክተሮች እንደየስራ ዘርፋቸዉ በክላስተር መደራጀታቸዉ ተቋማቶች የሚሰሯቸዉን ስራዎች በቅርበት ከመከታተል በተጨማሪ ማህበረሰብ ጠቃሚ የሆነ ተሞክሮአዊ አፈፃፀሞች ጎልተዉ እንዲወጡ ያስችላል ብለዉ፤ በየተቋማቶች ያጋጠሙ የግብዓት፣የአሰራርና የክህሎት ችግሮችን በቅንጅት እየፈታን ሁሉም ተቋሞች ተቀራራቢ አፈፃፀም እንዲኖራቸዉ እናደርጋለን ብለዋል።

በየክላስተሩ የሚሰሩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የልማት፣ የሰላምና የመልካም አሰተዳደር ወቅታዊ ስራዎች በቀጣይ በትኩረት እንዲሠሩ የቀጣይ አቅጣጫ በዋና አስተዳዳሪዉ ተሰጥቶ ግምገማዉ ተጠናቋል።

መረጃው የወረዳው ኮሙንኬሽን ነው።

የዝናብ እጥረቱ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡****************/////////////*****************መኮይ ፣ ነሐሴ 15/20...
21/08/2026

የዝናብ እጥረቱ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡
****************/////////////*****************
መኮይ ፣ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም. (አንፆኪያ ኮሙኒኬሽን) በያዝነው የክረምት ወቅት ዓለም አቀፍ የሆነ የዝናብ እጥረት /ኤሊኖ/መከሰቱ ይታወቃል፡፡ክስተቱ ክረምቱ ዘግይቶ መግባትና ቀድሞ መውጣት በመሆኑ ከሚያስከትለው ጉዳት ለመውጣት መደረግ ያለበት ቅድመ ዝግጅትና ትግበራዎችን አስመልክቶ ለ8ሺ 847 አርሶ አደሮች ባለሙያዎችና ለሚመለከታቸው አካላት ግንዝቤ የተፈጠረ መሆኑን የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ አቶ ፋንታሁን አስቻለው ገልፀዋል፡፡

እንደ ወረዳ 7ሺ 751 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ የነበረ ሲሆን 7ሺ 313 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡
በዘር የተሸፈነው ማሳ ምርት እንዲሰጥ ለማድረግ መሬቱ እርጥበት እንደያዘ እንዲቆይ ማድረግ የሚገባ በመሆኑ የጎርፍ ውሀ ወደ ማሳ ማስገባት፣ታይሬጅንግ የማሳ አናት ትሬንች፣ውሀ ማሰባሰቢያ ትሬንች፣ጥልቅ ውሀ ማስረጊያ ትሬንች፣ግማሽ ጨረቃ እርከን ስራዎች የተከናወነና እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በ62 የውሀ ሞተሮች አማካንነት ደግሞ 129 ደጋፊ መስኖ ወደስራ በማስገባት 722 ሄክታር በላይ መሬት የለማ መሆኑንና 3ሺ 366 አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

የከተማ ክላስተር ተቋማት የ2019 በጀት ዓመት የሃምሌ ወር እቅድ አፈፃፀማቸዉን ገመገሙ።በሰሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ የከተማ ክላስተር ተቋማት የ2019 በጀት ዓመት የሃምሌ ወር እቅድ አፈፃ...
21/08/2026

የከተማ ክላስተር ተቋማት የ2019 በጀት ዓመት የሃምሌ ወር እቅድ አፈፃፀማቸዉን ገመገሙ።

በሰሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ የከተማ ክላስተር ተቋማት የ2019 በጀት ዓመት የሃምሌ ወር እቅድ አፈፃፀም ግምገማ የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የከተማ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሽፈራው ሀይሉ፣ የክላስተሩ የፅ/ቤት ሃላፊዎችና ቡድን መሪዎች በተገኙበት ነሃሴ 15/2018 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡

በመረሃግብሩ ላይ የክላስተሩ ተቋማቶች ኢ/ኢንቨስትመንት፣ ከ/መ/ልማት፣ መ/ከ/መ/ማዘጋጃ ቤት፣ በኸራ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት፣ ንግድ ገበያ ልማት፣ ባ/ቱ/ስፖርት እና ስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ከእቅዳቸዉ የተቀዳ ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ተግባራት ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል ፡፡

የወረዳው ኢ/ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በጋሻው ጸጉ እንደገፁት ተግባሮችን በአደረጃጀት በመምራት የኢ/ኢንቨስትመንት ስራዎች እንዲነቃቃ በዕቅድ እየተሰራ ነው ብለዋል። አክለውም በሀምሌ ወር አድስ ፈቃድ እና የኢንቨስትመንት የፈቃድ እድሳት ስራ ተሠርተዋል ብለዋል። እንዲሁም በዘርፉ ለተሠማሩ ባለ ሀብቶች የማበረታቻ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የወረዳው ንግድ ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ለገሰ ትርፊ ባቀረቡት ሪፖርት ቀልጣፋ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የግብይት ስርዓት ለመዘርጋት ህጋዊ እና ዘመኑን የሚመጥን ነጋዴ ለመፍጠር ተቋሙ በዕቅድ እየሰራ ስለመሆኑ አስገንዝበዋል። አያይዘውም ወቅታዊ ሰው ወለድ የኑሮ ውድነት ለመቅረፍ ከአጋር አካላት ጋር የገበያ ማረጋጋት ስራ እየተሰሩ ስለመሆናቸው አስረድተዋል።

በ2019 በጀት ዓመት በሀምሌ ወር ለ3 መቶ 13 ዜጎች ቋሚ ስራ ዕድል መፈጠሩን የገለፁት የወረዳው ስ/ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጋለ ሹምየ ለ65 ወጣቶች ከተለያዮ ፕሮጀክቶች ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በማሰራጨት ተጠቃሚ የማድረግ ስራ እንደተሰራ ገልፀዋል። አክለውም በሀምሌ ወር ከ5 መቶ ስራ ፈላጊ ዜጎችን በኦላይን ሲስተም መመዝገባቸውን ጭምር አስረድተዋል።

የሀገር ውስጥ የቱሪስት ፍሰትን ለማሳደግ በዓመቱ በሰው ዕቅድ 45ሺህ 180 ተይዞ ከ18% እና በብር 45 ሚሊዮን 180 የዕቅዱን 18.6% መፈፀም መቻላቸውን የገለፁት የወረዳው ባ/ቱ/ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ላቀ ጋሻው በባህልና የሰላም እሴቶችን በማበረታታት የኪነ-ጥበብ ስራዎችን ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል ማቅረብ መቻሉን አስረድተዋል። የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎችን በባለቤትነት መፈፀም ተችሏል ብለዋል።

የአገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን የህዝቡን ተጠቃሚ የሚያረጋግጡ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያሉት የመራኛ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ስ/አስኪያጅ ወይዘሮ ብርቅነሽ ዘውገ በሀምሌ ወር የዕንግዳ ማረፊያ እና የንብረት ክፍል ግንባታዎች መገንባት እንደቻሉ በሪፖርታቸው አመላክተዋል። አክለውም የውስጥ ለውስጥ የመብራት የመሠረተ ልማት ዝርጋት ስራ መሠራቱ፣ ለተለያዮ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ቦታ የማስተላለፍ ስራዎችን ጨምሮ የኢንቨስትመንት ቦታ ተረክበው ያለሙ ቦታዎችን መሬት ገቢ ማድረጋቸውን ጭምር አስረድተዋል።

የተቋማት እቅድ አፈፃፀም እንደየ ባህሪያቸው በየጊዜዉ መገምገሙ የተገኘዉን ውጤት ለማስቀጠልና ክፍተቶችን ለማረም ያግዛል ያሉት የወረዳዉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሽፈራው ሀይሉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመፍታት ዕቅዶችን በትጋት በመፈፀም የህዝብን ተጠቃሚነት በተግባር ማረጋገጥ አለብን ብለዋል። አክለውም ተቋማቶች በመደጋገፍ ክፍተቶችን በመሙላት ከተሞችን ለነዋሪው ማህበረሰብ ምቹ አድርጎ መሥራት ተገቢ ነው ብለዋል።

መረጃው የወረዳው ኮሙንኬሽን ነው።

በሞጃና ወደራ ወረዳ 13ሺ5መቶ ሄክታር መሬት በክላስተር ስንዴ ሰብል የተሸፈነ መሆኑ ተገለፀ።በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሞጃና ወደራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት በምግብ ራስን ለመቻልና የምግብ...
21/08/2026

በሞጃና ወደራ ወረዳ 13ሺ5መቶ ሄክታር መሬት በክላስተር ስንዴ ሰብል የተሸፈነ መሆኑ ተገለፀ።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሞጃና ወደራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት በምግብ ራስን ለመቻልና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በተያዘው አቅጣጫ መሰረት፣ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች 13ሺ500 ሄክታር መሬት በክላስተር አሰራር በስንዴ ሰብል የተሸፈነ መሆኑን የወረዳዉ ም/አስተዳዳሪ ና ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኛቸዉ አዝብጤ ገልፀዋል ።

ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነዉ ።

በክላስተር የለማው የስንዴ ሰብል በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በሙያተኞች የቅርብ ክትትልና እንክብካቤ እየተደረገለት ይገኛል።

በወረዳው በኩታ ገጠም የተዘራው ይህ ሰብል ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር በተሻለ እና ምርታትና ምርታማነት ከማሳደግ አኳያ ሚናዉ የጎላ መሆኑን አቶ ዳኛቸዉ ገልፀዋል።

ሞጃና ወደራ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

በበየዳ ወረዳ ታጣቂ ሃይሎች መንግስት ያደረገላቸዉን የሰላም ጥሪ ተቀብለዉ ገቡ።​በሰሜን ጎንደር ዞን በበየዳ ወረዳ በተከዜ፣ በበስቂያ፣ በጠዘን፣ በሰገነት እና በአበርገሌ አካባቢዎች ታጥቀዉ ...
21/08/2026

በበየዳ ወረዳ ታጣቂ ሃይሎች መንግስት ያደረገላቸዉን የሰላም ጥሪ ተቀብለዉ ገቡ።

​በሰሜን ጎንደር ዞን በበየዳ ወረዳ በተከዜ፣ በበስቂያ፣ በጠዘን፣ በሰገነት እና በአበርገሌ አካባቢዎች ታጥቀዉ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ በመቀበል በሰላማዊ መንገድ ገብተዋል።

​በዚህም የተከዜ ብርጌድ አዛዥ ሻለቃ እንዳልክ ፍቃዱ ከ10 አባሎቻቸው ጋር በመሆን 1 ብሬን፣ 4 ክላሽንኮቭ፣ 1 እስኬስ፣ 1 ምንሽር እና 1 አብራራው የተሰኙ የጦር መሳሪያዎችን በማስረከብ በዛሬው ዕለት ወደ በየዳ ወረዳ ገብተዋል።

​በአቀባበል ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የበየዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሸጋው ብርሃን ጥሪውን ተቀብለው በሰላም በመመለሳቸው ምስጋና አቅርበዋል። ከግጭት የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን በመረዳት ወደ ሰላም መመለሳችሁ ትክክለኛ ውሳኔ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪዉ ከዚህ በኋላም ለአካባቢው ሰላም ዘብ ልትቆሙ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

​የሀገር መከላከያ ሰራዊት የ70ኛ ክፍለ ጦር 3ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ተስፋሁን ቤኬ በበኩላቸው፣ እርስ በእርስ መጋጨት ሰላምንና ልማትን ወደኋላ ከማስቀረት ውጭ ምንም ጥቅም እንደሌለው ጠቁመዋል። አሁንም በጫካ የሚገኙ ሌሎች የታጠቁ ኃይሎች ይህን የሰላም አማራጭ ተከተለው ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉም አዛዡ ጥሪ አቅርበዋል።

​ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው የተቀላቀሉት መካከል የራስ አሞራው ውብነህ 3ኛ ኮር ሰሜን ብርቅዬ ክፍለጦር የተከዜ ብርጌድ አዛዥ ሻለቃ እንዳልክ ፍቃዱ በበኩላቸዉ ቀደም ሲል የነበራቸው አካሄድ የተሳሳተ እንደነበር ገልጸዋል።

አሁንም የሰላም ጥሪውን በመቀበላቸው ደስተኛ መሆናቸውን በመግለጽ፣ ከዚህ በኋላ በልማት እና በሰላም ግንባታ ላይ በንቃት በመሳተፍ ህዝባቸውን ለመካስ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

​ከበየዳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን

"የወጣቶችን እውቀትና ተሳትፎ ለሰላምና ልማት እንዲውል ጥሪ ቀረበ"ደብረ ብርሃን፦ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) "የወጣቶችን እውቀት፣ አቅምና ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም ማኅበራዊ ትስስ...
21/08/2026

"የወጣቶችን እውቀትና ተሳትፎ ለሰላምና ልማት እንዲውል ጥሪ ቀረበ"

ደብረ ብርሃን፦ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) "የወጣቶችን እውቀት፣ አቅምና ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም ማኅበራዊ ትስስርና ልማት በማዋል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ንቁና ተጨባጭ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

ጥሪውን ያቀረቡት የሰሜን ሸዋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዓይነኩሉ አበበ ሲሆኑ "ብዝኀ የወጣቶች እውቀት ለጋራ ትልም" በሚል መሪ ቃል የዓለም ወጣቶች ቀንን አስመልክቶ ዞኑ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ባስተላለፉት መልእክት ነው።

አቶ ዓይነኩሉ እንደገለጹት፣ ወጣቶች በሰላም ግንባታ፣ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት እንዲሁም በሀገራዊ ውሳኔ ሰጪ ሂደቶች ያላቸውን ሚና ማጠናከር ይገባል።

በክልሉ ያለው የሰላም ችግር በአጭር ጊዜ እንዲፈታ ወጣቶችና ሴቶች የራሳቸውን ድርሻ እንዲወጡ አስገንዝበዋል።

በየአካባቢያቸው ሰላምን ከማስጠበቅ ባለፈ ወጣቶች በሥራ ፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ፣ በዲጂታል ኢኮኖሚና በሙያ ክህሎት ራሳቸውን በማብቃት ለሀገር እድገት አበርክቶ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

በዞኑ በወጣቶችና በሴቶች ተሳትፎ ከጫካ የተመለሱ ወጣቶች መኖራቸውን በመጥቀስ፣ ይህንን የሰላም ጥረት ማጠናከርና ወጣቶችን በልማት ላይ በተግባር ማሳተፍ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ሴቶች፣ ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ የሮምነሺ ጠናጋሻው፣ ወጣቶች ችግሮቻቸውን በውይይትና በድርድር በመፍታት በሰላም ግንባታ፣ በማኅበረሰብ ልማትና በውሳኔ ሰጪ ሂደቶች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

በተጨማሪም ወጣቶች በበጎ ፈቃድ ተሳትፎ የአቅም ደካሞችን በመደገፍ፣ ቤት በመገንባት፣ ማዕድ በማጋራትና በግብርና ሥራዎች በመሳተፍ የመረዳዳትና የመደጋገፍ እሴቶችን እንዲያጎለብቱ ጠይቀዋል።

ወጣቱ በሥራና በተግባር እንዲመራ ከተደረገ ለሰላም ግንባታ፣ ለማኅበራዊ ትስስርና ለአካባቢያዊ ልማት ወሳኝ ሚና ሊወጡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

መድረኩን የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ የሮምነሺ ጠናጋሻው እና የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወይዘሮ ንግሥት ይጥና የመሩት ሲሆን የመምሪያው የወጣቶች አደረጃጀት ስብዕና ግንባታ ቡድን መሪ ደረጀ አድማሱ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል።

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተከናውኑ ተግባራት በፎቶ ተቀናብረው የተጎበኙ ሲሆን የዓለም ወጣቶች ቀን ወጣቶች ከበዓሉ አከባበር ባለፈ በሰላም፣ በልማትና በበጎ ፈቃድ ሥራዎች ተጨባጭ ሚና እንዲወጡ በማስቻል ተከናውኗል።

የውጫዊ ወረራና የውስጣዊ ጽንፈኝነት ስጋቶችን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማት ላይ ትኩረት እንዲደረግ ተጠየቀ።ደብረ ብርሃን፦ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የደብረሲና ከተማ አስተዳደር ከሃይማኖ...
21/08/2026

የውጫዊ ወረራና የውስጣዊ ጽንፈኝነት ስጋቶችን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማት ላይ ትኩረት እንዲደረግ ተጠየቀ።

ደብረ ብርሃን፦ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የደብረሲና ከተማ አስተዳደር ከሃይማኖት አባቶች፣ ከሀገር ሽማግሌዎችና ከተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የከተማዋ ከንቲባ አቶ ላቀው ደበበ፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ሽማግሌዎችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በሰላም ግንባታና በጽንፈኝነት አደጋዎች መከላከል ላይ ያላቸውን ሀላፊነት በተግባር እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የከተማዋ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሳዬ ወ/አማኑኤል በበኩላቸው፣ የሰላምና የልማት ግቦችን ለማሳካት የሁሉም ወገን ትብብርና የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

በመድረኩ ተሳታፊዎችም ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን የተጀመሩ የልማት ሥራዎች በተጠናከረ አመራርና በሕዝብ ተሳትፎ በውጤታማነት እንዲጠናቀቁ አሳስበዋል።

ደብረ ሲና ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት

ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን ተባለ።አጣዬ፣ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን)  በአጣዬ ከተማ አስተዳደር “ው...
21/08/2026

ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን ተባለ።

አጣዬ፣ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን)

በአጣዬ ከተማ አስተዳደር “ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን” በሚል መሪ ሀሳብ ውይይት ተካሄደ።

ውይይቱን የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር እንድሪስ እና የከተማው ም/ከንቲባና የመሬት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላቸው ትዜ መርተዋል።

የመወያያ ሰነዱን ያቀረቡት የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘውዱ ታለፍ ሲሆኑ፣ ሰነዱን መነሻ በማድረግ በሀገራዊ ሰላም፣ በውጫዊ ስጋቶች፣ በውስጣዊ ፅንፈኝነትና በህብረተሰቡ ሚና ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።

በውይይቱ የሀገር ሽማግሌዎች በሰጡት አስተያየት፣ የሰላም ጥበቃና የሀገር አንድነት ለሁሉም የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ጠቁመው፣ ህብረተሰቡ የፅንፈኝነትን አደጋ በመመከት ለሰላም መጠናከር ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ ተሳታፊዎችም የሰላም ሁኔታን ለማስጠበቅ፣ የፅንፈኝነትን አደጋ ለመከላከልና የልማት ሥራዎችን ለማፋጠን በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ሀሳቦችን አንስተዋል።

በመጨረሻም የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር እንድሪስና የከተማው ም/ከንቲባ አቶ በላቸው ትዜ በሰጡት ማጠቃለያ፣ የሰላምና የልማት ሂደትን ለማስቀጠል የህብረተሰቡ አንድነትና ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ በጋራ በመቆም የሰላምና የልማት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

ውይይቱም ዘላቂ ሰላምን በማስፈን የልማት ጥረቶችን ለማጠናከር በጋራ መስራት እንደሚገባ በማሳሰብ ተጠናቋል።

 በሞላሌ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የ112ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ለተቸገሩ ተማሪወች ያሰባሰብትን 35 ደርዘን ደብተር ለሴ/ወ/ህ/ማ/ጉ/ጽ/ቤት አስረከብ፡፡ በሞላሌ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው ...
21/08/2026


በሞላሌ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የ112ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ለተቸገሩ ተማሪወች ያሰባሰብትን 35 ደርዘን ደብተር ለሴ/ወ/ህ/ማ/ጉ/ጽ/ቤት አስረከብ፡፡

በሞላሌ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የ112ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር ለተቸገሩ ተማሪወች ያሰባሰብት 35 ደርዘን ደብተር ለሴ/ወ/ህ/ማ/ጉ/ጽ/ቤት አስረከብ፤እርክክብንም የ112ኮማዶ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ኮለኔል ከተማ መለሰ ለሴ/ወ/ህ/ማ/ጉ/ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሂሩት ፍቃደ እና ለሞላሌ ከተማ አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊዋ ወ/ሮ አለምፀሀይ መኩሪያ አስረክበወል።

በፕሮግራሙም ላይ የ112ኮማዶ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ኮለኔል ከተማ መለሰ አገራችን ሰላም ሆና ተማሪወች ከጦርነት ስሜት ወተው ለትምርታቸው እንዲያተኩሩ ሁላችንም ሰላም ለማምጣት የበኩላችንን እንወጣ ብለዋል።

Address

Debre Birehan
Debre Birhan
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara North Shewa Zone Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Amhara North Shewa Zone Communication:

Shortcuts

Share