12/08/2026
ማስታወቂያ
የ ኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት በሚሰጥባቸው የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የ9ኛና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። በመሆኑም በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶቹ ተመዝግባችሁ ለመማር ፍላጎቱ ያላችሁና መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች በዚህ ሊንክ https://sbs.moe.gov.et/apply መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
✍️ ነጻ የትምህርት እድሉ የሚሰጣቸው ጥቅሞች
👉 ሙሉ የትምህርት ክፍያ ሽፋን
👉 የመኝታና የምግብ አገልግሎት
👉 የተሟላ እና ልዩ ሥርዓተ ትምህርት የሚከተል ጥራት ያለው ትምህርት
👉 ምቹ የመማሪያ አካባቢ
✍️ትምህርት የሚሰጥባቸው ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች
✍️ 9ኛ እና 10ኛ ክፍል
👉 ቡኢ ልዩ አዳሪ
👉 ጅግጅጋ ልዩ አዳሪ
👉 ጋምቤላ ልዩ አዳሪ
👉 ወሊሶ ልዩ አዳሪ
👉 ቦንጋ ልዩ አዳሪ
✍️ 9ኛ ክፍል ብቻ
👉 አርባ ምንጭ ልዩ አዳሪ
👉 ድሬዳዋ ልዩ አዳሪ
👉 አሶሳ ልዩ አዳሪ
👉 ባህር ዳር ልዩ አዳሪ
የመመዝገቢያ መስፈርቶች
✍️ ለ9ኛ ክፍል ተመዝጋቢዎች
👉 የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና አማካይ ውጤት 85 በመቶ እና በላይ አማካኝ ውጤት ያለው/ያላት እንዲሁም በእንግሊዝኛና በሂሳብ ትምህርቶች 80 እና በላይ ያመጣ/ያመጣች ።
👉 ጥሩ ስነ -ምግባር ያለው/ያላት
✍️ ለ10ኛ ክፍል ተመዝጋቢዎች
👉በ2017 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና 70 እና በላይ አማካኝ ውጤት ያመጣ/ያመጣች
👉በ9ኛ ክፍል ትራንስክሪብት 85 በመቶና በላይ አማካኝ ውጤት ያመጣ/ያመጣች እንዲሁም በእንግሊዝኛ እና ሂሳብ ትምህርት ዓይነት 80 በመቶና በላይ ያመጣ/ያመጣች።
✍️ የምዝገባ ሁኔታ
👉 ባሉበት በበየነ መረብ ( Online) ይመዝገቡ፡_ https://sbs.moe.gov.et/apply
✍️ መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች ምዝገባችሁን ባላችሁበት ቦታ ሆናችሁ ለዚሁ ሲባል በተዘጋጀው የመመዝገቢያ ፖርታል በኦንላይን መመዝገብ እና አስፈላጊ የተባሉ መረጃዎችን ማያያዝ ይጠበቅባችኋል
✍️ ምዝገባው እስከ ነሃሴ 15/2018 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።
✍️ ለፈተና የሚቀርቡ ተማሪዎች ዝርዝር እና የፈተና ጊዜ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል
✍️ የመመልመያ መስፈርቱን አሟልተው ፈተናውን የሚያልፉ ተማሪዎች ባሉን ክፍት ቦታዎች በሚመደቡበት ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ለመማር ፈቃደኛ የሆኑ መሆን አለባቸው።