02/05/2023
በብቃትና በጥራት የተደራጀ ሥራ ፈጣሪ ወጣቶችን በማፍራት ሥራ አጥነትን መቀነስ ይገባል ተባለ።
ሚያዚያ 23/2015 ዓ.ም
================================
የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን
================================
የቂልጦ ኮንስትራክሽን እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በ2015 በጀት አመት ውስጥ ባለፉት 9 ወራቶች የተከናወኑ ተግባራትንና የቀጣይ የተማሪ ቅበላንና በሌሎች አጀንዳዎኝ ሁሉም የቦርዱ አባላት በተገኙበት ዝርዝር ውይይት ተደርጓል።
በአሁኑ ወቅት የሚስተዋለውን የስራ አጥ ቁጥር ከመቀነስ በዘለለ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂን በመቅዳት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ወጣቶችን ማፍራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በ2015 በጀት አመት በ9 ወሩ ውስጥ የተከናወኑ ተግባራትንና የኮሌጁን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች በዝርዝር ለቦርዱ ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
በቦርድ ስብሰባው ላይ የስልጤ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፈድሉ ከድር እንዲሁም ሁሉም የቦርዱ አባላት ተሳትፈዋል፡፡
በዋናነትም ኮሌጁ በቀጣይ ግዜያት ከሌሎች ባለድርሻ ሴክተር መስሪያቤቶችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የሚያከናውናቸው ተግባራትንና የቅንጅት ስራዎች ላይ አፅንኦት ተሰጥቶበታል፡፡
የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ቡሴር እንደገለፁት የቂልጦ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግር ማዕከልና የምርምር ማዕከል እንዲሆን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ተገቢውን የድጋፍና ክትትል ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
አስተዳዳሪዋ አክለውም በኮሌጁ የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች ብቁና በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ስራ ፈላጊ ሳይሆን ተፈላጊ እንዲሆኑ ቦርዱና የኮሌጁ ማህበረሰብ ሀላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ በትኩረት እየሰሩ እንደሆነ ገልፀዋል።
ወ/ሮ መህዲያ አክለውም የቂልጦ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እያገጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመሻገር ብሎም ኮሌጁ የሚፈለግበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የቦርድ አባላትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ሀላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት አለበቸው ብለዋል፡፡
የስልጤ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፈድሉ ከድር በመድረኩ እንዳሉት የቦርድ አባላቱና ኮሌጁ በተናበበና በተቀናጀ መልኩ በመስራት በመደበኛና በአጫጭር ግዜ ስልጠናዎችን ለመውሰድ ወደ ተቋማት የሚገቡ ሰልጣኞች ቅበላን በተሻለ መልኩ መፈፀም ይገባል ሲሉ አሳስቧ፡፡
አቶ ፈድሉ ከድር አክለው እንዳነሱት ኮሌጁን አሁን ላይ ካለበት አንድ ደረጃ ከፍ ለማድረግ ተማሪዎች ተገኝተው ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲወስዱ እንደሆነም ገልፀዋል፡፡
ተማሪዎችን ወደ ኮሌጁ ገብተው የተለያዩ የትምህርት አይነትና ሙያ እንዲወስዱ እንዲሁም ኮሌጁን
ደረጃውን ከፍ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት በየ ቀበሌው በመግባት ለተማሪዎች ግንዛቤ በመፍጠርና በማስተባበሩ ረገድ ወሰኝ ሚና እንዳላቸውም ጠቁመዋል፡፡
የቂልጦ ኮንስትራክሽንና እንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ከድር ቀጀላ በበኩላቸው የቂልጦ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ ሰልጣኞችን ለማፍራትና ኮሌጁ የሚፈለግበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የቦርድ አባላትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ሀላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው ገልጿል፡፡
አቶ ከድር ቀጀላ አክለውም በበቂ ዕውቀትና ክህሎት የዳበሩ ኢንተርፕራይዞችን በብዛትና በጥራት በማፍራት ረገድ የሚስተዋሉ ጉድለቶችን በማረም የዘርፉን ውጤታማነት በተ