Bonga University

Bonga University Bonga University is one of the Public Higher Educational Institution in Ethiopia.
(1)

Bonga University Academic Leaders Attend International Environmental Seminar in China.        ::::::::::::::​August 2026...
07/08/2026

Bonga University Academic Leaders Attend International Environmental Seminar in China.

::::::::::::::​August 2026 :::::::::::::::

Academic leaders from Bonga University recently completed a 21-day international training program, "Seminar on Environmental Pollution Prevention and Control for Developing Countries," hosted by China’s Biogas Institute of the Ministry of Agriculture and Rural Affairs (BIOMA).

​BIOMA, a globally recognized center for technical training and sustainable rural development, hosted the delegation across three major Chinese cities: Chengdu (Sichuan), Kunming (Yunnan), and Guangzhou (Guangdong).

The program provided delegates with direct exposure to China's advanced practices in renewable energy, pollution control, and sustainable development.

​The training opportunity was secured through the diplomatic engagement of Bonga University President, Dr. Degela Ergano, as part of the university's strategy to expand global partnerships and staff capacity.

Dr. Yared Ayalew Zemede, Director for International Relations and Strategic Partnership at Bonga University, was selected to deliver the valedictory closing address on behalf of all international attendees.

In his address, Dr. Yared thanked BIOMA and the Chinese government for their hospitality while affirming the participants' commitment to applying the knowledge gained to environmental initiatives in their home countries.

​Together We Can!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የ2018ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት አደረገ።            ::::::::::::::::ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም::::::...
06/08/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የ2018ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት አደረገ።

::::::::::::::::ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም::::::::::::::::::

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላት በ2018ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ውይይት አድርጎል።

ሪፖርቱን የዩኒቨርሲቲው ስትራተጂክ ጉዳዮች ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አማረ ወ/ገብርኤል ቀርቧል።

ሪፖርቱ በመማር ማስተማር ፣ በምርምር ፣ በማህበረሰብ አገ/ት እና መሠል ሌሎች ተግባራት ላይ የተሰሩ ተግባራት በዝርዝር ቀርቧል።

በተጨማሪም የ2019 ዓ.ም መነሻ ጠቋሚ ዕቅድ የዩኒቨርሲቲውን ግብ እና ቁልፍ ተግባር አመልካች /KPI / መሠረት አድርጎ ቀርቧል።

ሪፖርቱ እና ጠቋሚ ዕቅዱ ከቀረበ በኋላ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) ከምክትል ፕሬዝደንቶች እና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ሀላፊ ጋር በመሆን በቀረበው ሪፖርት እና ዕቅድ ላይ ማብራሪያ በመስጠት ለውውይት መድረኩን ከፍተዋል።

ያሳካናቸውን በማጠናከር የታዩ ክፍተቶችን መሙላት እንደሚያስፈልግ በምክትል ፕሬዝዳንቶቹ እና በፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ተዘርዝሮ ቀርቧል።

የካውንስል አባላትም በርከት ያሉ የተለያዩ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል።

ለተነሱ ጥያቄዎችም የሚመለከታቸው አካላት ተገቢ ምላሽ የሰጡ ሲሆን እንደግብዓት የተወስዱ ሪፖርት እና ዕቅዱን የሚያጎለብቱም ነጥቦችም ነበሩ።

በመጨረሻም ክቡር ፕሬዝዳንቱ በሰጡት ማጠቃለያ ለካውንስሉ አባላት ንቁ ተሳትፎ አመስግነው የተነሱ ነጥቦችን መሠረት አድርገው ሰፊ የሆነ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በተለይ ዕቅዱ ያለቀለት ባለመሆኑ የተነሱ ሀሳቦች እንደሚካተቱ ገልፀው በቀጣይ 2019 ዓ.ም የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ጠንክሮ መስራት ይገባል ብለዋል።

ክቡር ፕሬዝዳንቱ ትኩረት ከሰጧቸው ነጥቦች መካከል KPI ፣ የተቋም ህልውና፣ የራስ - ገዝ ጉዞ፣ የተቋም ማሻሻያ ፣ ዓለም ዓቀፍ ትብብሮች እና የተቀናጁ የምርምር ተግባራት ፣ ሀብት ማመንጨት ፣ በቡና ሳይንስ ልቆ መውጣት ፣የቴክኖሎጂ መሠረተ-ልማት ማስፋፋት እና የህዝብ ግንኙነት ስራዎች ማጠናከር ላይ መሠረት በማድረግ ተግባራቶቻችንን በመፈፀም በመጪው 2019 ዓ.ም የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ የበኩላችንን ማድረግ ይገባናል በማለት ሪፖርት እና ዕቅዱን በማፅደቅ የዕለቱ መርሀ-ግብር ተቋጭቷል።

በጋራ እንችላለን!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለክረምት ተማሪዎች የዲጂታል ክህሎት ስልጠና ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ተከናወነ።         ::::::::::::::ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም::::::::::::::::በመድረኩ ...
04/08/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለክረምት ተማሪዎች የዲጂታል ክህሎት ስልጠና ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ተከናወነ።

::::::::::::::ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም::::::::::::::::

በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ መማ/ማስ/ምር/ቴክ/ስር/ማ/አ/ት ምክትል ፕሬዝዳንት ከለለው አዲሱ(ዶ/ር) ናቸው።

ምክትል ፕሬዝዳንቱ ተማሪዎችን የእንኳን ደህና መጣችሁ ካሉ በኋላ ጊዚያቸውን በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ የት/ት ጊዜ እንዲያሳልፉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ E-Learning ዳይሬክተር በሀይሉ ገማሪያም(ዶ/ር) ስለክረምት ተማሪዎች ዲጂታል ስልጠና አስፈላጊነት እና ስለሚወስዷቸው ኮርስ ዙሪያ ለተማሪዎች አብራርተዋል።

የአካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ፣ ሬጅስትራር እና ትም/ት ጥራት ዳይሬክተር በየተራ ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት በተለይ የት/ት ሰሌዳን /Academic Calendar/፣ ውጤታቸውን በአግባቡ መያዝና ችግር ካለ በጊዜ ማስተካከል እንደሚገባቸው በየተራ በሰጡት ገለፃ አብራርተዋል።

በጋራ እንችላለን!

Bonga University Attends 3rd ACUE General Assembly in Kebridehar.       ::::::::::::::August 2/2026:::::::::::::::::::::...
02/08/2026

Bonga University Attends 3rd ACUE General Assembly in Kebridehar.

::::::::::::::August 2/2026:::::::::::::::::::::::::

​Bonga University, led by President Dr. Degela Ergano, joined leaders from 21 higher education institutions and MOE officials at Kebridehar University for the 3rd General Assembly of Comprehensive Universities (ACUE).

​Under the theme "The Need for Increased Collaboration for Greater Impact," the gathering focused on strengthening institutional partnerships and advancing higher education across the nation.

​Host university President, Eng. Abdulfetah Ahmed Rabi, opened the event with welcoming remarks.

​Dr. Diriba Eticha, current Chairperson of the Comprehensive Universities Forum adressed opening remarks.

Dr. Ebba Minjana , CEO for Higher Education at the Ministry of Educatio (MoE) a key insight on the ongoing higher education reform agenda​ entitled National Reform Agenda.

Field visit and green legacy has been also part of the conference.

Together We Can!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ቡና ላይ ያተኮረ ግዙፍ የምርምር ፕሮጀክት መነሻ ሀሳብ ለውይይት ቀረበ።        ::::::::::::::::::ሀምሌ 23/2018 ዓ.ም::::::::::::::::የቡናን ምር...
30/07/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ቡና ላይ ያተኮረ ግዙፍ የምርምር ፕሮጀክት መነሻ ሀሳብ ለውይይት ቀረበ።

::::::::::::::::::ሀምሌ 23/2018 ዓ.ም::::::::::::::::

የቡናን ምርታማነት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በተቀናጀ ሁሉን ዓቀፍ ምርምር ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከአ/አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር መነሻ ሀሳብ ቀርቧል።

መድረኩን የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የመማ/ ማስ/ ምር/ እና ማህ/ አ/ት ምክትል ፕሬዝዳንት ከለለው አዲሱ (ዶ/ር) ተመራማሪዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ነበር።

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የአስ/ር ቦርድ አባል እና የምርምር ፕሮጀክቱ ከፍተኛ ተመራማሪ እና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ሉሊት ጥላሁን (ዶ/ር) የምርምር ፕሮጀክቱን አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የት/ት ተቋማት ከተለመደው የመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ እንደዚህ አይነት ግዙፍ ምርምርች የአካባቢውን የቡና አቅም ከማሳየቱም በላይ ለሀገርም ለዩኒቨርሲቲውም ትልቅ አቅም እንደሆነ ገልጸዋል።

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የቡናና ቅመማቅመም ዳይሬክተር ክፍሌ በላቸው(ዶ/ር) የምርምር ፕሮጀክቱን ቁልፍ ነጥቦች አስቀድመው አቅርበዋል።

ፀጋዬ ጌታሁን (ዶ/ር)፣ ደምሳቸው ጓዴ (ዶ/ር) እና ትዕግስት ወንድሙ(ዶ/ር) ከአ/አበባ ዩኒቨርሲቲ ከባዮቴክኖንሎጂ ተቋም የመጡ ከፍተኛ ተመራማሪዎች ሲሆኑ በየተራ ዋናውን የምርምር ፕሮጀክት መሠረት ያደረጉ የተለያዩ ርዕስ ላይ የመነሻ ሀሳብ አቅርበዋል።

የምርምር ፕርጀክቶቹ ከቀረቡ በኋላ የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ተነስተዋል።

በጋራ እንችላለን!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ም/ኢ/ሕ/ክ/መ/ሴቶች እና ማህ/ጉ/ቢሮ የወጣቶች ዘርፍ ጋር በመተባበር ለወጣቶች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።       :::::::::::::::::: ሀምሌ 22/2018 ...
29/07/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ም/ኢ/ሕ/ክ/መ/ሴቶች እና ማህ/ጉ/ቢሮ የወጣቶች ዘርፍ ጋር በመተባበር ለወጣቶች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

:::::::::::::::::: ሀምሌ 22/2018 ዓ.ም::::::::::::::::::::

የወጣቶችን ሁለንተናዊ የአቅም ግንባታ መስጠት መሠረት ያደረገው መድረኩ ለ260 ወጣቶች የክረምት አቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

በመድረኩ ተገኝተው ‎የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ(ዶ/ር) ናቸው።

ክቡር ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው ክልሉ በተፈጥሮ ፀጋ የታደለ መሆኑን አውስተዋል።

አክለውም ‎ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የአከባቢውን ፀጋዎች በማልማት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማቶች ማዋል ስለሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በርካታ ጥናት እና ምርምሮችን እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል።

በተጨማሪም ሰርቶ ማሳያዎችን በማዘጋጀት ለአከባቢው ማህበረሰብ የማስተዋወቅ ስራን በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

ክቡር ፕሬዝዳንቱ መልዕክታቸውን ቀጥለው ‎ወጣቱ ትውልድ በዙሪያው ያለውን ፀጋዎች በማልማት ራሱንና ሀገሩን ለመለወጥ ተግቶ መስራት እንደሚገባው አሳስበዋል።

ለአምስት ተከታታይ ቀን የሚቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና የወጣቶችን አመለካከት በመቅረጽ የውስጥ አቅምን እንዲጠቀሙ ለማስቻል ያለመ እንደመሆኑ ተሳታፊ ወጣቶች በንቃት በመሳተፍ ሀላፊነታችሁን ልትወጡ ይገባል በማለት ስልጠናውን በይፋ አስጀምረዋል።

‎የደ/ም/ኢ/ሕ/ክ/መ/ሴቶች እና ማህ/ጉ/ቢሮ የወጣቶች ዘርፍ አማካሪ አቶ ሰይድ ኢብራሂም በበኩላቸው ወጣቶች በውስጣቸው ያለውን አቅም አውጥተው ለመጠቀም ዝግጁ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።

‎ክልላችን ለግብርና ፣ ለማዕድንና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ሊሆን የሚችል ግዙፍ ፀጋዎችን የታደለ እንደመሆኑ ወጣቱ ከዘርፉ የሚገኘውን ፀጋ ለመቋደስ ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

‎ በጋራ እንችላለን!

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የዩኒቨርሲቲውን የግንባታ ፕሮርጀክቶች ጎበኙ።          ::::::::::::::::ሀምሌ 20/2018 ዓ.ም:::::::::::::::::የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝ...
27/07/2026

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የዩኒቨርሲቲውን የግንባታ ፕሮርጀክቶች ጎበኙ።

::::::::::::::::ሀምሌ 20/2018 ዓ.ም:::::::::::::::::

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር)በጊቢው ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ የግንባታ ፕሮጀኬቶችን ጎብኝተዋል።

በዩኒቨርሲቲው ፕርጀክት ጽ/ቤት የሚመራው ግንባታው በተለይ የመምህራን መኖሪያ ህንፃ እና የማስተማሪያ ሆቴል ግንባታዎውች ያሉበት ደረጃ ተገምግሟል።

በጉብኝቱ የፕሮጀክት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ክንዴ ተሾመ እንደገለፁት ተቋርጠው የነበሩ የግንባታ ፕሮጀክቶች መቀጠላቸውን እና በተለይ የመምህራን መኖሪያ ቤት በቅርቡ ተጠናቅቆ ወደ አገልግሎት እንደሚገቡ ጠቅሰዋል።

የግንባታ ፕሮጀክቶቹ አሁን ላይ ጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኙ የተጠቀሰ ሲሆን እጅግ ባጠረ ጊዜ ተጠናቅቀው ወደ አገልግሎት የሚገቡ የመምህራን መኖሪያን ጨምሮ ሌሎች ግንባታዎችም እንዳሉ ተጠቅሶል።

ክቡር ፕሬዝዳንቱም በጉብኝታቸው መደሰታቸውን ጠቅሰው በተለይ የመምህራን መኖሪያ ቤት ቀሪ ጥቂት ስራዎች ተጠናቅቀው ለመምህራን እንዲውሉ አሳስበዋል።

በጋራ እንችላለን!

ለቦንጋ ዩኒቨርሲቲ መምህራን የGIS ቴክኖሎጂ  አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።       :::::::::::::::ሐምሌ18/2018 ዓ.ም::::::::::::::::ለዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ስታፍ ...
25/07/2026

ለቦንጋ ዩኒቨርሲቲ መምህራን የGIS ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።

:::::::::::::::ሐምሌ18/2018 ዓ.ም::::::::::::::::

ለዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ስታፍ የተሠጠው የGIS ስልጠና በዋናነት ለምርምር ተግባር መጠቀም በሚቻልበት አግባብ ላይ ትኩረት በማድረግ ነበር።

በስልጠና መድረኩ ላይ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲያችን ተልዕኮዎቹን የበለጠ ለማሳካት እንደነዚህ ዓይነት የቴክኖሎጂ ስልጠናዎች የተሻለ አቅም ይፈጥራሉ ብለዋል።

አክለውም ስልጠናውን ለመስጠት የመጡትን ከፍተኛ ምሁራን እና የቦብንጋ ዩኒቨርሲቲ አስ/ር ቦርድ አባልን ከልብ የመነጨ ምስጋናቸውን ችረዋቸዋል።

በመልዕክታቸው የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ሰልጣኝ ምሁራንና ተመራማሪዎችንም ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለተሻለ የምርምር ተግባር እንድታውሉት ብለዋል።

ስልጠናውን የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ አባል የሆኑት አማረ ባንቲደር (ዶ/ር) በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ መስክ ያካበቱትን ዕውቀት እና ሰፊ ልምድ ተሳታፊዎች በማካፈል ነበር የጀመሩት . . .

በስልጠናው ለምርምር ተግባር አጋዥ የሆነ አዲስ የተንቀሳቃሽ /Mobile/ GIS ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዙሪያ ለዘርፉ ምሁራን ሰፊ የሆነ ሙያዊ ስልጠና ሰጥተዋል።

ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎችንና አሰራሮችን ለመማር-ማስተማር፣ ለምርምር እንዲሁም ለዕለት-ተዕለት አስተዳደራዊ ስራዎችም እንዴት መጠቀም እንደሚቻልም ገለጻና ተግባራዊ የሆነ የልምድ ልውውጥ ተደርጓል።

በጋራ እንችላለን!

የ2018 ዓ.ም ሀገር ዓቀፉ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን አስመልክቶ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መልዕክት አስተላለፉ። ::::::::::::::ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም:::...
23/07/2026

የ2018 ዓ.ም ሀገር ዓቀፉ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን አስመልክቶ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መልዕክት አስተላለፉ።

::::::::::::::ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም:::::::::::::

በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በስድስት ዙሮች በበይነ-መረብ /Online/ እና በወረቀት ሲሰጥ የነበረው ሀገር - ዓቀፉ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሰላም ተጠናቋል።

ፈተናው በሰላም መጠናቀቁን አስመልክቶ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) ለመርሀ-ግብሩ ስኬት የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል።

ከት/ት ሚ/ር የመጡ ፈተና አስፈፃሚዎች ፣ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ባደረገው የተደራጀ የፈተና ቅድሜ ዝግጅት በሁሉም ዙሮች የተሰጠውን ፈተና ያለምንም ችግር ማስፈፀም ያስቻላቸው መሆኑን የገለፁ ሲሆን ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ መምህራን የአስ/ር ሰራተኞች ፣ የፀጥታ አካላት እና ሌሎችንም ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል።

በመጨረሻም ክቡር ፕሬዝዳንቱ ለተፈታኞች መልካም ምኞታቸውን በማስተላለፍ መልዕክታቸውን ቋጭተዋል።

በጋራ እንችላለን!

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በሀገረ አሜሪካ ከሚገኘው ከቨርሰንድ ዩኒቨርሲቲ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት/ MOU / ተፈራረመ።             ::::::::::ሐምሌ 15/2...
22/07/2026

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በሀገረ አሜሪካ ከሚገኘው ከቨርሰንድ ዩኒቨርሲቲ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት/ MOU / ተፈራረመ።

::::::::::ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም::::::::::::::

በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) እና በቨርሰንድ ዩኒቨርሲቲ በኩል ከፍተኛ የስራ ሀላፊ ስምምነቱን ተፈራርመዋል ።

ቨርሰንድ ዩኒቨርሲቲ በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት የሚገኝ ሲሆን ከቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመማር ማስተማር ፣ በምረርምር እንዲሁም በቴክኖሎጂ ዘርፍ እና ባህል ልውውጥ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ የስምምነት ሰነዱ ያመለክታል።

°ለመምህራን የሚሰጡ የተለያየ ይዘት እና መጠን ያላቸው ስልጠናዎች

° በጋራ ኮርሶችን መስጠት/ Joint Academic Program/ ፣ የምህራንና የተማሪ ልውውጥ እና መሠል ተግባራት

ስምምነቱ ከዩኒቨርሲቲው በተጨማሪ የአካባቢውን የተፈጥሮ ፀጋ በእውቀት አጎልብቶ ከመጠቀም አንፃር ከምርምር ባለፈ የህብረተሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረቱን ያደርጋል።

ቡና ላይ የሚሰሩ የምርምር ስራዎች ደግሞ ሌላው የአካባቢውን ተጠቃሚነት ከግምት ያስገባ ነው።

በምርምሩ ዘርፍ ታዋቂ በሆኑ የምርምር ህትመቶች ላይ የቦንጋም የቨርሰንድ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን በጋራ የምርምሮችን በመስራት ከፍተኛ አቅም መፍጠር እንደሚቻልም ተጠቅሷል።

በአጠቃላይ ክቡር ፕረሬዝዳንቱ ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) እንደገለፁት እንደነዚህ አይነት የመግባቢያ ስምምነቶች ለዩኒቨርሲቲያችን በርካታ ዕድሎችን ይዘው እንደመምጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ጠቅሰው ከመፈራረም ባለፈ ለተግባራዊነቱም በጋራ እንደሚሠሩ ገልፀዋል።

በጋራ እንችላለን!

Address

Bonga
334

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bonga University posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share