ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች

ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች

Share

ተዋሕዶ

Photos from ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች's post 08/10/2022

በሰው ቂም አትያዝ
በሰው ቂም አትያዝ በሰው ላይ ያለውን ቂም በልቡናው የሚያሳድር ሰው ጸሎቱ ቅድመእግዚአብሔር አትደርስምና ከመናፍቃን ጋር አትጸልይ ከአሕዛብ ጋርም ቢሆን ሃይ አበ 20፥17
ተቆጡ ነገር አትበድሉ በመኝታችሁ ሳላችሁ በልባችሁ የምታስቡት ይታወቃችሁ መዝ 4፥4
የዋሀን ብፁአን ናቸው እነርሱ ምድንን ይወርሳሉና...በሚሰድቧችሁና በሚያሳድዷችሁ ጊዜ ስለእኔም እየዋሹ ክፉውን ሁሉ በሚናገሩባችሁ ጊዜ ብፁዓን ናችሁ ማቴ5፥5-12
ወንድሞቻችን ራሳችሁ አትበቀሉ ቁጣን አሳልፏት እኔ እበቀላለሁ...ጠላትህ ቢራብ አብላው ቢጠማም አጠጣው ይህንን ብታደርግ የእሳት ፍህም በራሱ ላይ ትክምራለህ ሮሜ 12፥19-21
ተቆጡ አትበድሉም ፀሐይ ሳይጠልቅም ቁጣችሁን አብርዱ ለሰይጣንም መንገድ አትስጡ ኤፌ4፥26-27
ሕፀፅ እንደሚያመጣብህ የምታውቀውን አትሥራ ሰውን ሁሉ ውደድ ሰዎች ሁሉ በአንተ ዘንድ ከራስህ ይልቅ የከበሩ ይሁኑ ከሰው ሁሉ ጋር ሰላማዊ ሁን ሃይ አበ 21፥5
አሁንም በክርስቶስ ደስታ ወይም በፍቅር የልብ መጽናናት ወይም የመንፈስ አንድነት ወይም ማዘንና መራራትም በእናንተ ዘንድ ካለ እርሱን ብቻ ታስቡ ዘንድ አንድ ልብና አንድ ምክርም ሆናችሁ ትህትናን በያዘ ልቡና ከራሳችሁ ይልቅ ባልንጀራችሁን አክብሩ እንጂ አትታበዩ ፊልጵ 2፥1-5

Photos from ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች's post 07/10/2022

ክብርህ ሰማያዊ ነው
ሰው በጥንተተፈጥሮው ምድራዊ ነው በዳግማዊ ተፈጥሮው ደግሞ ሰማያዊ ነው ከምድ አፈር ተፈጥር በማየገቦ ከብሮ ሰማያዊ የክርስቶስ አካል ሕብረት ቤተሰብ ማሕበር ይሆናል ረቂቁ ቃል በግዘፈሥጋ እንደተወለደ ግዘፈሥጋ ያለው ሰው ደግሞ በረቂቅ ይወለዳል
የኔን ወሰደና የሱን ሰጠኝ እንደለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከክርስቶስ ጋር ይሞታል ከክርስቶስ ጋር ይቀበራል ከክርስቶስ ጋር ይነሳል ሮሜ6:3
ስለምድራዊ ክብር ፈንታ ሰማያዊዉን ክብር ሻ ፈልግ አብዝቶ ከመብላት ሰውነቱን የከለከለ ሰው እርሱ ሰውነቱን ከኃጢአት ወስኖ ገትቶ መያዝ ይቻለዋልና ሃይ አበ 21፥16
ከክርስቶስ ጋር ከተነሳችሁ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ በአለበት በላይ ያለውን ሹ ቈላ 3፥1-3
ወይን አትጠጣ ቀምሰህ ፈጣሪውን ለማመስገን ብቻ ይሁን እንጂ፡
እንደጢሞቲዎስም ብትታመም ከገድል ጽናት የተነሳ በጽኑ ደዌ ብትያዝ ግን ከወይን ጥቂት ጠጣ እርሱ ለሥጋ ሕይወት ይሆንልሀልና ወይን አብዝቶ መጠጣት ደዌሥጋ ደዌነፍስ ያገኘዋል ቢቻል አንድ ጽዋ ቢበዛ ሁለት ቢጠጣ ለነፍሱም ለሥጋውም ረብህ ጥቅም ይሆነዋል
ስለሆድህ በሽታና ስለዘወትር ደዌህ ጥቂት ወይን ጨምር እንጂ ውኃ ብቻ አትጠጣ 1ጢሞ 5፥23
ራሳችሁን ጠብቁ በመብልና በመጠጥ በመቀማጠልና የዓለምን ኑሮ በማሰብ ልባችሁን አታደንድኑ ያቺ ቀንም በድንገት ትደርስባችኋለች በምድር በሚደርሱ ሁሉ ላይ እንደተዘረጋች ወጥመድ ትደርሳለችና እንግዲህ ከዚህ ከሚመጣው ሁሉ በጸሎታችሁ ማምለጥ እንድችሉ በሰው ልጅ ፊትም መቆምም እንድትችሉ ሁልጊዜ ትጉ። ሉቃ 21፥34-36

Photos from ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች's post 05/10/2022
Photos from ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች's post 05/10/2022

ናሁ ይመጽእ በደመናሰማይ ራዕ1፥7
በሰማይ ደመና ተጭኖ ይመጣል
ደመና በነፋስ ጋዝነት ከውቅያኖስ ዝናም ተሸክሞ መልኩን ጥቁር አድርጎ እግዚአብሔር በአዘዘው ቦታ ላይ የሚያፈስ ነው
በተለይም በረድ በረዱን ሰው በማይኖርበት ጥሩ ጥሩውን ሰው በሚኖርበት ያወርዳል ለሰዎች ረብህ ጥቅም ይሆናል ምድርም ጌጥ የሚሰጡአትን ዕጽዋት እንድታበቅል ያደርጋታል
ደመና የተባሉ መምህራን ናቸው፦
ደመና ዝናምን ከዑቅያኖስ ተሸክሞ ለሚፈልጉት ሰዎች እንደሚሰጥ መምህራንም ለሰዎች ሕይወተሥጋ ሕይወተነፍስ የሚሆነውን የእግዚአብሔር ቃል ያስተምራሉ እነሱንም እንዲመስሉ ያደርጓቸዋል
የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ በጎ አኖኗራቸውንም እያያችሁ ምሰሏቸው ዕብ 13፥7
ክፉዎችን ሰዎች ደግሞ ወደበጎነት እንዲመለሱ ይገስጾቸዋል ካልተመለሱም ወደእግዚአብሔር ይጸልዩባቸዋል
ኤልያስ አክአብን እንደገሰጸው 1ነገ 17፥1
ዮሐንስ መጥምቅ ሄሮድስን የወንድምህ የፊልጶስን ሚስት ልታገባ አይገባህም ብሎ እንደገሰጸው ማቴ 14፥1
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አውዶክስያን እንደገሰጸ ሳይፈሩ ያስተምራሉ ይገስጻሉ
ደመና ውኃ ቋጥሮ ወጥቶ እየዞረ እያዘነመ ብዙ አትክልት እና አዝርዕት እንዲበቅሉ ያደርጋል መምህራንም እየዞሩ እያስተማሩ ያልተመለሰውን ጥያቄ መልሰው የተመለሰው ተርጉመው አስተምረው ብዙ ሰዎችን ከአምልኮጣዖት ወደአምልኮተእግዚአብሔር ይመልሷቸዋል
አንመለስም ያሉትንም እግዚአብሔር በእሊህ መምህራን አድሮ በመአት ይመጣባቸዋል
በቅዱስ ጴጥሮስ አድሮ ሐናንያን እንደቀሰፈ የሐ ሥራ 5፥1-6
በቅዱስ ጳውሎስ አድሮ በርያሱስን እንደቀሰፈ ይቀስፋቸዋል የሐ ሥራ 13፥6
መምህራን ለነፍስ የሚያስፈልጋትን የሚመግቡ የእግዚአብሔር ማደሪያ ዳመናወች ናቸው።

Photos from ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች's post 03/10/2022

ገንዘብ ይኑርህ ገንዘብ ግን አትውደድ
ገንዘብ ብር የምትወድ አትሁን ወርቅ ብር ልታደልብ አትውደድ ለኑሮህ ለልብስህ ለምግብህ የሚበቃ ያህል በመጠን ይሁን እንጂ ገንዘብ የሚወዱ እግዚአብሔር ማስደሰት አይቻላቸውምና
እግዚአብሔር ከኔ ጋር ቢሆን በምሄድባት በዚች መንገድ ቢጠብቀኝ የምበላውን እንጀራ የምለብሰውንም ልብስ ቢሰጠኝ ወደአባቴም ቤት በጤና ቢመልሰኝ እግዚአብሔር አምላኬ ይሆንልኛል ከሰጠኸኝም ሁሉ ለአንተ ከአሥር አንድ እሰጣለሁ ዘፍ 28፥20-22
የእለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን በደላችንን ይቅር በለን...ሌባ በሚሰረቀው በምድራዊ ቦታ ገንዘባችሁን አታስቀምጡ ሌቦች ቆፍረው በማይሰርቁት በሰማይ ለእናንተ መዝገብን ሰብስቡ ማቴ 6፥11-19
ምግባችንንና ልብሳችንን ካገኘን ይበቃናል ጠንዘብን መውደድ የኃጢአት ሁሉ ሥር ነውና ይህንንም በመመኘት ተሳስተው ሃይማኖታቸውን የለወጠው ብዙዎች ናቸውና 1ጢሞ 6፥8-21

ማንም ሰው ድሀ እንዲሆን አይፈለግም።
ግን በማጭበርበርና ከድሀ በመቀማት የሱ ያልሆነውን በመውሰድ አይደለም። ግረህ ጥረህ ብላ ተብሎ በተሰጠው በጉልበቱ በወዙ አፍርቶ ራሱንና ቤተሰቡን እና በአጠቃላይ በሃይማኖት የሚመስሉትንና የማይመስሉትንም እየረዳ መኖር አለበትደ

Photos from ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች's post 03/10/2022

ከወንድሞቻችሁ ጋር በፍቅር ኑሩ እንግዳ መቀበልንም አትርሱ ዕብ 13፥1
ወንድሞች ወደአንተ በመጡ ጊዜ እግራቸውን ማጠብ ቸል አትበል ይህቺን ስራ ቸል የሚሏትን ሥላሴ በፋዳ ይመረምሯቸዋልና ምንም ኤጲስቆጶሳትም ስንኳ ቢሆኑ እግዚአብሔር አስቀድሞ የደቀመዛሙርቱን እግር አጥቦ እንዲሁ ያደርጉ ዘንድ ከዝዟቸዋልና ሃይ አበ ዘ፫፻ 20፥29
በኵስኵስትም ውኃ ቀድቶ የደቀመዛሙርቱን እግር ያጥብ ጀመር...እንዲህም አላቸው አደረግሁላችሁን አወቃችሁን? እናንተ መምህራችን ጌታችንም ትሉኛላችሁ መልካም ትላላችሁ።፤እኔ እንዲሁ ነኝና እንግዲህ እኔ መምህራችሁና ጌታችሁ ስሆን እግራችሁን ካጠብኋችሁ እናንተም እንዲሁ የባለእንጀሮቻችሁን እግር ልታጥቡ ይገባችኋል። ዮሐ 13፥1-17
ባልቴትን ልትሾም ብትመርጥ እድሜዋ ስድሳ (60) የሆናትን አንድ ባል ያገባችውን ምረጥ እንግዳን ከተቀበለች የጻድቃንን እግር ካጠበች የተራበውን ካበላች በጎ ምግባርንም ሁሉ ከተከተለች ትመርጥ 1ጢሞ5፥9-10

Photos from ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች's post 01/10/2022

ማሕሌት፡
ስንኳን ለእመቤታችን ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
የማሕሌት ክብሯ ቀላል አይምሰላችሁ ተአ ማርያም 202:6
የአገልጋዮች ድምፅ ከፍ ከፍ ብሎ በተሰማና ማሕሌቱ በደመቀ ጊዜ እንደወይን ዘለላ ያለ የውሀ ነጠብጣብ በቤተክርስቲያን ውስጥ ይታያል ወደመሬትም ይወርዳል ማሕሌት ከመቆማቸው በፊት ግን በቤተክርስቲያን ውስጥ ውሀው አይንጠበጠብም እናንተ የክርስቲያን ወገኖች በቤተክርስቲያን ድምፅን ከፍ እያደረጉ በመጮህ በእጅ በማጨብጨብ በእግር እያሸበሸቡ በማሕሌታዊ ምስጋና እግዚአብሔርን ማመስገንና እመቤታችንን ማወደስ ከሁሉም ይበልጣል።
በእግዚአብሔር በዓላት እና በእመቤታችን በዓል የሚያመሰግኑትን የሚንቁና የሚያሽሟጥጡ ቢኖሩ ንጉሥ ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት ሲያመሰግን ሜልኮል ስቃበት የደረሰባት እዳ በደል ይደረግበታል
ዳዊት ለእግዚአብሔር ሲዘም ስለሳቀችበት እግዚአብሔር ለሜልኮል ልጅ አልሰጣትም 2ሳሙ6፥20-23
እግዚአብሔርን በፍጹም ልቡ የሚያመሰግን ሰው ከሱራፌል ጋር አንድ ሆኖ ያመሰግናል
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ሲያመሰግኑ ሰማ አየም ኢሳ6፥3
እንደአቡነ ተክለሃይማኖት
እንደቅዱስ ያሬድ
እንደቅዱስ ጳውሎስ
እስከሦስተኛው ሰማይ ነጠቁት በሥጋው ይሁን በነፍሱ እንጃ እንዳለ 2ቆሮ12፥2
የዳዊትን መዝሙር የሚጸልይ አንድ ሰው ነበር በበአቱ ሆኖ ሲጸልይ ካሕናት በማሕሌት ሲያገለግሉ ግሩም ራዕይ አየ
አምላክን የወለደች እመቤታችን መጥታ በመካከላቸው ተገኘች የጣፈጠ ምግብም አጠጣቻቸው እኔም ከነሱ ጋር ልጠጣ ወደድኩ ከእርሷ ጋር ቆሞ የነበረው መልአክ ግን አንተስ አትሂድ አይገባህም ሰነፍ ነህ አለኝ ተአ ማርያም 204፥2
እናንተ የክርስቲያን ወገኖች በቤተክርስቲያን ውስጥ የማሕሌት ምስጋና አገልግሎት በእግዚአብሔርና አምላክን በወለደች በክብርት እመቤታችን ዘንድ ምን ያህል ተወዳጅ እንዳለው አስተውሉ።
እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት እንዲል መዝ 150፥1
ኵሉ ነፍስ ይሴብሖ ለእግዚአብሔር
እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን መዝ 150፥6
በእውነት ዓለምን ሁሉ በአንድ ቃሕ የፈጠረ ፈጽሞ የመሰገነ ነው በሁለት ወገን ድንግል የምትሆን እመቤታችንም በሰውና በመላእክት አንደበት የተመሰገነች ናት ሉቃ 1፥28 ሉቃ1:48
ለምስጋንዋ ታነቃንና ታተጋን ዘንድ ኑ እመቤታችን እንለምናት፡

Photos from ለቤተክርስቲያን ደራሾች የቤተክርስቲያን ልጆች's post 30/09/2022

አንትሙሰ ፍጥረት ኅሩያን ፩ጴጥ፪:፱
እናንተስ ደጋግ ፍጥረታት ናችሁ 1ጴጥ2:9
ፍጥረት በተፈጥሮው ለሰው ልጅ እንዲገዛ የታዘዘ ነው
ፍጥረታትን ፈጥሮ ከፈጸመ በኋላ አክብሮ እና አልቆ የሰራው የሰውን ልጅ ነው።
እግዚአብሔር አምላክ ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጠረው፡
እግዚአብሔር በባሕርይ በሕልውና በአገዛዝ...አንድ ነው።
በአካል በግብር በስም ሦስት ነው፡
በስም አብ ወልድ መንፈስቅዱስ ናቸው።
በኵነት ልብ ቃል እስትንፋስ ናቸው።
ለሰው ይህ ሁሉ የተሰጠው ታላቅ ፍጡር ነው።
በአብ አበው በወልድ ውሉድ በመንፈስቅዱስ መንፈሳዊያን ብሎ ስሙን ሰጠን
በኵነት ልብነቱ ልብን በቃልነቱ ቃልን በእስትንፋስነቱ (በሕይወትነቱ) እስትንፋስን (ሕይወት) ሰጠን
በባሕርይ አንድ እንደመሆኑ የሰው ባሕርይም ከአራቱ ባሕርያት የተፈጠረ ነው ከአራቱ ባሕርያት ውጪ የተፈጠ ሰው የለም።
እግዚአብሔር በነሲዕ ተገናዝቦ አሀቲ ባሕርይ ነውደ
ሰው ግን ነሲዕ ተገናዝቦ የለውም።
ነገር ግን ይህ ደግ ፍጥረት ነው፡
በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል የተፈጠረ ነው ዘፍ1:26
በእግዚአብሔር እጅ የተፈጠረ ክቡር ፍጥረት ነው መዝ 118፡73
ደግ ፍጥረት ነው የንጉሥ መንፈስቅዱስ ማደሪያም ነው 1ጴጥ 2:9
እናንተ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ እንደሆናችሁ የእግዚአብሔር መንፈስም በእናንተ ላይ አድሮ እንደሚኖር አታውቁምን 1ቆሮ 3:16
ቅዱስ ወገን ትሆኑልኛላችሁ ዘጸ 22:31
እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ ዘሌ11:45 ዘሌ19:2 1ጴጥ 1:15
እኔ እግዚአብሔር ቅዱስ ነኝና ለኔም ትሆኑ ዘንድ ከአሕዛብ ለይቻችኋለሁና ቅዱሳን ትሆኑልኛላችሁ ዘሌ20:26

መምህር ሰሎሞን ንብረት

30/09/2022

እንደስማቸው የትህትና አባት ናቸው።

የአራቱ ጉባዔያት፣ የቅኔና የአቡሻኽር ሊቅ ናቸው። የኔታ ትሕትና ይባላሉ ።

የዘመናችን ቅዱስ ያሬድ ወተዋነይ ወዮሐንስ ገብላዊ መምህራችንን በዕድሜ በጸጋ ያኑርልን።ብዙ ልንጠቀምባቸው ይገባናል። ሊቀ ሊቃውንት የኔታ ትሕትና በወሎ ክፍለ ሃገር ኃይቅ እስጢፋኖስ ገዳም የአራቱ ጉባኤያት መምህር ናቸው።

ሁላችንም እንጠይቃቸው ጉባኤ ቤታቸውንም እንጎብኝ።
አምላከ ቅዱሳን ጉባኤ ቤታቸውን ያስፋልን።

28/09/2022

ገብርኤል ሲመጣ ከሰማይ ተልኮ፡
ሰይጣን ይሸነፋል ይወድቃል ተማርኮ፡

ገብርኤል ጠላታችንን ሰይጣንን ይጣልልን

03/09/2022

ወልደእግዚአብሔር ሆይ ልደትህ ድንቅ ነው ሃይ አበ ዘያዕቆብ ዘሥሩግ 88:2

30/08/2022

ስንኳን ለአቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አረሳችሁ
ሁለት እግር ኖሮህ ወደገሀነም ከምትጣል አንድ እግር ኖሮህ ወደመንግስተሰማያት ብትገባ ይሻልሀል
ስንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ለአቡነ ተክለሃይማኖት አደረሳችሁ!!!

Want your school to be the top-listed School/college in Bedele?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address


ጠባብ በር
Bedele