Ethiopian Institute of Textile and Fashion Technology

Ethiopian Institute of Textile and Fashion Technology In Ethiopia, EiTEX is a premier higher education institute under Bahir Dar University for more than

In Ethiopia, EiTEX is a premier higher education institute under Bahir Dar University for more than 50 years. It is a pioneer institute in offering programs in Textile, Leather, Apparel and Fashion technology. The institute continues to strive to strengthen research, community service and technology transfer activities in order to contribute to economic development of the country as per Growth and

Transformation Plan (GTP). The EiTEX is one of the limbs of the Bahir Dar University whose objectives perfectly fit the strategy of agriculture-led and export-oriented industrialization and the effort to combat the problem of textile & garment manufacturing and trade of the country. The institute aims to support and develop Ethiopian Textile, Garment, Leather and Fashion industries. Furthermore, the institute regularly organizes international conferences in the cotton, textile, apparel and leather sectors. Generally, the vision of EiTEX has been to support and enhance the capability and the competitiveness to Ethiopian Textile, Garment, Leather and Fashion industries including the small and medium enterprises.

02/09/2026

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቅበላ ማስታወቂያ 🎓

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው የመግቢያ መስፈርት መሰረት በማታ (Extension) እና በርቀት (Distance) መርሃ ግብሮች በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በPGDT ተማሪዎችን ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል።

በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉና መማር የምትፈልጉ አመልካቾች ከነሀሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 30 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እያስታወቅን የምታመለክቱባቸውን የትምህርት መስኮች ዝርዝር ከታች መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን::

🎯 የማመልከቻ መስፈርት (በትምህርት ሚኒስቴር የመግቢያ መስፈርት መሰረት)፡

🔖 የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ወስደው በትምህርት ሚኒስቴር የወጣውን የየዘመኑን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ፤
🔖 ከዲፕሎማ ወይም ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ወደ ከፍተኛ ትምህርት ለመግባት የተቀመጠውን የመግቢያ መስፈርት ያሟሉ፤
🔖 በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአቅም ማሻሻያ (Remedial program) ተከታትለው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ፤
🔖 ለበለጠ መረጃ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ድረ-ገጽ https://bdu.edu.et/registrar/ ይመልከቱ::

📑 ለምዝገባ የሚያስፈልጉ ሰነዶች/ማስረጃዎች፡
📝 የትምህርት ማስረጃ ዋናውና ፎቶ ኮፒ፤
📝የብቃት ማረጋጫ (COC) (ለሚያስፈልጋቸው ብቻ)፤
📝ኦፊሻል ትራንስክርፒት (ለሚያስፈልጋቸው ብቻ)፤
📝ለማመልከቻ (Application fee) 300 ብር የተከፈለበት ኦሪጅናልና አንድ የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል::

📍 የማመልከቻ ቦታ፡
🔖 ለማታ ትምህርት ፕሮግራሞች፡ በባህር ዳር ካምፓስ በየአካዳሚክ ክፍል ሬጅስትራሮች ሲሆን፤
🔖 ለርቀት ትምህርት ፕሮግራሞች፡ በርቀት ትምህርት ማዕከላት ማለትም በባህር ዳር፤ ጎንደር፤ ደሴ፤ ደብረ ብርሃን፤ አዲስ አበባ፤ ደብረ ማርቆስ፤ ፍኖተ ሰላም እና ሞጣ - እነሴ ማዕከላት ምዝገባ ይደረጋል::

⚠️ ተጨማሪ ማሳሰቢያዎች፡
🔖 የቀድሞው ትምህርት ፖሊሲ 12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ ተቀባይነት የለውም፤
🔖 በዲፕሎማ የሚመዘገቡ አመልካቾች በምዝገባ ወቅት ኦፊሻል ትራንስክርፕት በፖስታ ሳጥን ቁጥር 79 ማስላክ አለባቸው፤
🔖 በሀገር አቀፍ ደረጃ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ፈተና ላልተዘጋጀላቸው የትምህርት ዘርፎች ዩኒቨርስቲው የሚያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና መውሰድ አለባቸው:: የፈተናው ቀን እና የቅበላ ውጤት ይፋ የሚደረግበትን ቀን በውስጥ ማስታወቂያ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ድረ-ገጽ https://bdu.edu.et ወይም የፌስቡክ ገጽ ወደ ፊት ይገለፃል፤

🔖በቂ የተማሪ ቁጥር የማያመለክትባቸው የትምህርት መስኮች አይከፈቱም::
🔖ከዚህ በፊት ለመማር ተመዝግበው ባቋረጡት የት/ት መስክ በተመሳሳይ የቅበላ ዓይነት መመዝገብ አይቻልም::

💳 ክፍያ የሚፈጸምባቸው የባንክ አካውንቶች፡

የመመዝገቢያ ክፍያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚከተሉት የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የውስጥ ገቢ የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች መክፈልና ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል::

📌 1000224663378 — ለቢዝነስና ኢኮኖሚክስ፣ ማህበራው ሳይንስ፣ ሂውማኒቲስ፣ ለህግ፤ ትምህርት ኮሌጅ (PGDT)፣ግብርናና አካባቢ ሳይንስ እና ስፖርት አካዳሚ የትምህርት መስክ አመልካቾች ብቻ፤

📌 1000096185007 — ለኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስትቲዩት (EiTEX) የትምህርት መስክ አመልካቾች ብቻ፤

📌 1000013094563 — ለባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስትቲዩት (BiT) የትምህርት መስክ አመልካቾች ብቻ::

📚 የሚሰጡ የትምህርት መስኮች ዝርዝር (Programs Offered)
🔻 1. የርቀት ትምህርት ፕሮግራሞች (Distance Programs)
(የማመልከቻ ማዕከላት፡ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ደብረ ብርሃን፣ አዲስ አበባ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ፍኖተ ሰላም እና ሞጣ-እነሴ)
* College of Business and Economics (BA Degree):
* Accounting and Finance
* Management
* Economics
* Marketing Management
* Logistics & Supply Chain Management
* Faculty of Humanities (BA Degree):
* English Language and Literature
* Ethiopian Language and Literature- Amharic
* Folklore / Culture Studies
* Ge’ez Language & Literature
* Journalism and Communications
* Faculty of Social Science (BA Degree):
* Civics and Ethical Studies
* Geography
* Sociology
* Political Science
* Social Work
* College of Education (PGDT Program):
* PGDT (Amharic; English; Geography; Civics; Mathematics; Chemistry; Biology; Physics; Sport Science; ICT; Economics; Business education)

🔻 2. የማታ ትምህርት ፕሮግራሞች (Extension Programs)
(የማመልከቻ ቦታ፡ በባህር ዳር ካምፓስ)

* College of Business and Economics (BA Degree):
* Accounting and Finance
* Economics
* Management
* Marketing Management
* Logistics & Supply Chain Management
* Tourism and Hotel Management
* School of Law (BA Degree):
* Law
* Governance and Developmental Studies
* Faculty of Social Science (BA Degree):
* Civics and Ethical Studies
* Geography
* Sociology
* Political Science
* Philosophy
* Social Work
* Faculty of Humanities (BA Degree):
* English Language and Literature
* Ethiopian Language and Literature- Amharic
* Folklore / Culture studies
* Ge’ez Language & Literature
* Journalism and Communications
* Cinema and Theatre Arts
* Sport Academy (BSc Degree):
* Physical Education
* Sport Science
* College of Agriculture and Environmental Science (BSc Degree):
* Veterinary Science
* Ethiopian Institute of Textile and Fashion Technology - EiTEX (BSc Degree):
* Fashion Design
* Garment Engineering
* Leather Product Engineering
* Textile and Apparel Merchandising
* Faculty of Computing (BSc Degree):
* Computer Science
* Software Engineering
* Cyber Security
* Information Systems
* School of Material Science and Engineering (BSc Degree):
* Material Science and Engineering
* Faculty of Civil & Water Resource Engineering (BSc Degree):
* Civil Engineering
* Hydraulic & Water Resource Engineering
* Water Resources & Irrigation Engineering
* Faculty of Electrical and Computer Engineering (BSc Degree):
* Electrical Engineering
* Computer Engineering
* Faculty of Chemical & Food Engineering (BSc Degree):
* Human Nutrition
* Faculty of Mechanical & Industrial Engineering (BSc Degree):
* Mechanical Engineering
* Automotive Engineering
* Electromechanical Engineering
* Industrial Engineering

🌐 የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ድረ-ገጽ፡
https://bdu.edu.et/registrar/
ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር በማድረግ መረጃውን ያካፍሉ! 🔄

የkg 1 እጣ የሚወጣበት
30/08/2026

የkg 1 እጣ የሚወጣበት

የ1ኛ ክፍል ምዝገባ
30/08/2026

የ1ኛ ክፍል ምዝገባ

የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) የ2019 ዓ.ም. የበጀት ዓመት ዕቅድ አቀራረብ ተጠናቀቀባሕር ዳር፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ...
28/08/2026

የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) የ2019 ዓ.ም. የበጀት ዓመት ዕቅድ አቀራረብ ተጠናቀቀ

ባሕር ዳር፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) የ2019 ዓ.ም. የበጀት ዓመት ዕቅድ የሁለተኛ ቀን በቀጠለው የእቅድ አቀራረብ ላይ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ታምራት ተስፋዬ፣ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ምስረታ መነሻ በማድረግ EiTEX በራስ ገዝ ተቋምነት የሚኖረውን ሚና እና የሚያገኘውን ቱርፋቶች በመሠረታዊ ሀሳቦችን አቀረበዋል።

እንደ ፕሮፌሰር ታምራት EiTEX በራስ ገዝነት መቀጠሉ የተቋሙን የማስተማር፣ የምርምር፣ የፈጠራ፣ የኢንዱስትሪ ትስስርና የማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎችን ይበልጥ በማጠናከር በሀገራዊና ዓለምአቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ተቋም ለመገንባት ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።

እንዲሁም ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የዕቅድ አቀራረብ መርሃ ግብር በቀጣዩ የበጀት ዓመት ተቋሙ ሊያሳካቸው ያቀዳቸውን ዋና ዋና ግቦች፣ ተግባራትና የአፈጻጸም አቅጣጫዎች በግልጽ ለማስቀመጥ ያለመ ሲሆን፣ የተቋሙን የትምህርትና ምርምር ጥራት ማሻሻል፣ የፈጠራ ሥራዎችን ማጠናከር፣ ከቴክስታይልና ፋሽን ኢንዱስትሪው ጋር ያለውን ትስስር ማሳደግ እና ተቋማዊ አቅምን ማጠናከር ትኩረት ከሚደረግባቸው አቅጣጫዎች መካከል ናቸው።

ከዕቅድ አቀራረቡ በኋላ በቀረቡት ዕቅዶች ዙሪያ ውይይትና ግምገማ ተደርጓል። ተሳታፊ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች እና ሌሎች የተቋሙ ኃላፊዎች በዕቅዶቻቸው አፈጻጸም፣ በተግባራት ቅደም ተከተል፣ በግቦች ላይ በመመርኮዝ የሚለካ ውጤት ማስመዝገብ እና በተቋሙ የተቀመጡ ተቋማዊ አቅጣጫዎችን በተግባር ማሳካት ዙሪያ ሀሳብና አስተያየት አቅርበዋል።

ተሳታፊዎች በቀረበው የራስ ገዝነት ምስረታ መነሻ ሀሳብ ላይ በመወያየት ለዩኒቨርሲቲ ብሎም ለኢንስቲትዩቱ የራስገዝነት ሂደት መሠረት ለመጣል ያስችላል የተባለ ሲሆን በቀረበው የራስ ገዝ መነሻ ፕሮፖዛል ዙሪያ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል።

ፕሮፌሰር ታምራት ተስፋዬ በተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ ዝርዝር ማብራሪያ በመስጠት፣ የራስ ገዝነት ሂደቱ በጥናት፣ በማስረጃ እና በተቋሙ ነባራዊ አቅም ላይ በመመስረት መመራት እንዳለበት ጭምር አስገንዝበዋል

የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) በዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝነት የሚኖረውን ሚና የሚያሳይ የመነሻ ፕሮፖዛል አቀረበ=====≡=========================...
28/08/2026

የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) በዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝነት የሚኖረውን ሚና የሚያሳይ የመነሻ ፕሮፖዛል አቀረበ
=====≡======================================================
ባሕር ዳር፣ ነሐሴ 22፣ 2019 ዓ.ም — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ታምራት ተስፋዬ፣ በዛሬ የሁለተኛ ቀን በቀጠለው እቅድ አቀራረብ ላይ ኢንስቲትዩቱ በራስ ገዝ ተቋምነት እንዲቀጥል የሚያስችሉ መሠረታዊ ሀሳቦችን ያካተተ የመነሻ ፕሮፖዛል አቀረቡ።

ፕሮፌሰር ታምራት የመነሻ ፕሮፖዛሉን ሲያቀርቡ፣ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን የራስ ገዝነት ምስረታ ሂደት እንዲሁም ከዚህ ቀደም በተቋሙ የተከናወኑ ተቋማዊ ሂደቶችን እንደመነሻ በመጠቀም፣ EiTEX በራስ ገዝ ተቋምነት ሊኖረው የሚችለውን ሚናና ሊገኙ የሚችሉ ቱርፋቶችን በሰፊው አብራርተዋል።

እንደ ፕሮፌሰር ታምራት ገለጻ ኢንስቲትዩቱ በራስ ገዝ ተቋምነት ለመቀጠል ከመማርና ማስተማር ሥራው ባሻገር የራሱን የገቢ ማስገኛ አቅም ማሳደግ፣ የምርምርና ኢኖቬሽን ሥራዎችን ማጠናከር እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን ትስስር ማስፋት የሚጠበቅበት ይሆናል።

በዚህ ረገድ የኢንስቲትዩቱ የሰላም ኢንተግሬትድ ቴክስታይል ፋብሪካ፣ የጋርመንት ፋብሪካ፣ አክሪዲቴድ ላቦራቶሪዎች እና ሌሎች ኢንተርፕራይዞችን በመፍጠርና በማጠናከር የገቢ ማስገኛ አቅሙን ማሳደግ እንደሚችል በፕሮፖዛሉ ተመላክቷል።

በተጨማሪም EiTEX በቴክስታይል፣ በፋሽንና በቆዳ ዘርፎች የሚያከናውናቸውን የምርምር፣ የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎች በማጠናከር ለኢንዱስትሪው የቴክኖሎጂና የሙያ ድጋፍ ማድረግ እንደሚችል ተጠቁሟል።

የኢንስቲትዩቱ የምርምርና ኢኖቬሽን አቅም መጎልበት፣ የላቦራቶሪና የምርት አቅሞች መስፋት፣ ከኢንዱስትሪና ከሌሎች ተቋማት ጋር ያለው ትስስር መጠናከር እንዲሁም የራስ ገዝ የገቢ ምንጮች መፈጠር ለኢንስቲትዩቱ ዘላቂነትና ተወዳዳሪነት ወሳኝ መሆናቸውም በመነሻ ፕሮፖዛሉ ተመልክቷል።

ፕሮፌሰር ታምራት እንዳመለከቱት፣ EiTEX በራስ ገዝ ተቋምነት ሲደራጅ ተቋሙ በራሱ የሚወስንበትን የሥራ አቅም ማሳደግ፣ ምርምርና ኢኖቬሽንን ማፋጠን፣ የኢንዱስትሪ ትስስርን ማጠናከር እና ለሀገሪቱ የቴክስታይልና ፋሽን ኢንዱስትሪ የተሻለ የሰው ኃይል፣ ቴክኖሎጂና እውቀት ማቅረብ የሚችል ተቋም ለመሆን ያለውን እድል ያሰፋል።

በመሆኑም የመነሻ ፕሮፖዛሉ የEiTEXን ተቋማዊ አቅም በማጠናከር፣ የገቢ ማስገኛ ምንጮችን በማስፋት፣ ምርምርና ኢኖቬሽንን በማበረታታት እና ከቴክስታይልና ፋሽን ኢንዱስትሪው ጋር ያለውን ትስስር በማጠናከር ኢንስቲትዩቱ በራስ ገዝ ተቋምነት ዘላቂና ውጤታማ ተቋም እንዲሆን የሚያግዙ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

የEiTEX 2019 ዓ.ም. የበጀት ዓመት ዕቅድ እየገመገመ ነውባሕር ዳር፣ ነሐሴ 21/2019 ዓ.ም. — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX...
27/08/2026

የEiTEX 2019 ዓ.ም. የበጀት ዓመት ዕቅድ እየገመገመ ነው

ባሕር ዳር፣ ነሐሴ 21/2019 ዓ.ም. — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) የ2019 ዓ.ም. በጀት ዓመት ዕቅድ አቀራረብ በዲኖች፣ በዳይሬክተሮች እና በማኔጂንግ ዳይሬክተሩ እየተካሄደ ነው።

በዕቅድ አቀራረቡ የኢንስቲትዩቱ የተለያዩ ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች በ2018 ዓ.ም. የተከናወኑ ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን፣ የታዩ ክፍተቶችንና በሁኔታ ትንተና በማቅረብ በ2019 በጀት ዓመት ለማሳካት ያቀዷቸውን ዋና ዋና ተግባራት እያቀረቡ ይገኛል።

ኢንስቲትዩቱ በውጤት ላይ የተመሠረተ የሰባት ትምህርት ፕሮግራሞች የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ አውደ ጥናት አካሄደ::ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም (BDU-EiTEX) — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮ...
25/08/2026

ኢንስቲትዩቱ በውጤት ላይ የተመሠረተ የሰባት ትምህርት ፕሮግራሞች የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ አውደ ጥናት አካሄደ::
ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም (BDU-EiTEX) — በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የኢንስቲትዩቱ አመራሮች፣ መምህራን፣ የኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በውጤት ላይ የተመሰረተ ትምህርት (Outcome-Based Education - OBE) የሰባት ትምህርት ፕሮግራሞች ማሻሻያ (ክለሳ) አውደ ጥናት ተካሄደ።
አውደ ጥናቱን በንግግር የከፈቱት የኢንስቲትዩቱ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ተባባሪ ፕሮፌሰር አዳነ ኃይሌ፣ የዚህ ዝግጅት ዋነኛ ዓላማ የኢንስቲትዩቱ የአካዳሚክ መርሃ ግብሮች ዘመኑን የዋጁ፣ ፈጠራን የሚያበረታቱ እንዲሁም ከተማሪዎች፣ ከኢንዱስትሪዎች፣ ከማህበረሰቡና ከሀገር አጠቃላይ ፍላጎት ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም ተቋሙ በቴክስታይል፣ በልብስ ስፌት፣ በቆዳ፣ በፋሽንና ተያያዥ የቴክኖሎጂ ዘርፎች ባለሙያዎችን በማሰልጠን ረገድ ያከበተውን ልምድ በመጠቀም ለሀገር እድገት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ባለሙያዎችን ለማፍራት እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ከተደረገባቸው ሰባት ፕሮግራሞች መካከል በኢንስቲትዩቱ መምህራን የቀረቡ ሲሆን፣ እነሱም፦
• Textile Engineering በዶ/ር ደሳለኝ በሻው
• Fashion Engineering በወ/ሮ ሳባ መኮነን
• Leather Engineering በአቶ ከተማ አለሙ
• Textile Design በዶ/ር ብሩክ ፈንታሁን
• Fashion Design፦ በአቶ አሸናፊ ተክላይ
• Textile and Apparel Merchandizing በአቶ እዮብ ምንባለ
• Visual Arts፦ በአቶ ሀይማኖት ካሳሁን ቀርበዋል::
በመጨረሻም ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት፣ በበይነመረብ (Online) ከተጋበዙ ምሁራን፣ ከኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም ከተቋሙ ምሁራን ጠቃሚ አስተያየቶችና ግብአቶች ተሰብስበውበት አውደ ጥናቱ በስኬት ተጠናቋል።

25/08/2026
Happening Now ===========Curriculum Validation Workshop is undergoing. Seven programs ( Textile Engineering, Textile Des...
24/08/2026

Happening Now
===========
Curriculum Validation Workshop is undergoing. Seven programs ( Textile Engineering, Textile Design, Leather Engineering, Fashion Engineering, Fashion Design, Textile and Apparel Merchandizing and Visual Arts) are presented to be reviewed and validated. Experts, stakeholders and staff members are attending the workshop.

Three Days to Go: Curriculum Validation Workshop
21/08/2026

Three Days to Go: Curriculum Validation Workshop

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Institute of Textile and Fashion Technology posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Ethiopian Institute of Textile and Fashion Technology:

Shortcuts

Share