Lalibela Study Design & Supervision Works PLC

Lalibela Study Design & Supervision Works PLC Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Lalibela Study Design & Supervision Works PLC, Bahir Dar.

የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የዳይሬክተሮች ቦርድ የመጀመሪያ ጉባኤ በስኬት ተጠናቀቀ!የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የዳይሬክተሮች ቦርድ የመጀመሪያ ጉ...
20/08/2026

የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የዳይሬክተሮች ቦርድ የመጀመሪያ ጉባኤ በስኬት ተጠናቀቀ!

የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የዳይሬክተሮች ቦርድ የመጀመሪያ ጉባኤውን የቦርዱ ሰብሳቢና አባላት፣ እንዲሁም የኩባንያው ከፍተኛ ኃላፊዎች በተገኙበት በስኬት አካሂዶ አጠናቋል።

የጉባኤው ዋና ዋና ውሳኔዎች
✔️ የቦርድ አባላት ትውውቅ ተከናውኗል፣ የቦርዱ መደበኛ የመሰብሰቢያ ጊዜ ተወስኖ የቦርዱ የሥራ ሂደት ግልጽ እንዲሆን ተደርጓል።
✔️በጉባኤው የኩባንያውን የ2018 ዓ.ም. ግማሽ በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀምና የፋይናስ ሪፖርት በጥልቀት ገምግሞ አጽድቋል።
🎤 በግምገማውም የተመዘገቡ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተነስተው ተመክሮባቸዋል።
✔️የ2019 ዓ.ም. የተዘጋጁት የበጀት፣ የፕሮጀክትና የካፒታል ማሳደጊያ ዕቅዶች በጥልቀት ተገምግመው የፀደቁ ሲሆን፣ የኩባንያውን የወደፊት ዕድገት፣ተወዳዳሪነትና ውጤታማነት ለማሳደግ በሚያስችሉ ስትራቴጅ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።
✔️የቦርድ–ማኔጅመንት ትብብርን፣ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን በማጠናከር የኩባንያውን ተቋማዊ አቅም የበለጠ ለማሳደግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ የቦርድ አባላትና የኩባንያው ኃላፊዎች የኩባንያውን ዕድገት፣ ውጤታማነትና ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት፣ በተቀናጀ አመራርና በትብብር ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በተለይም የኩባንያውን የገበያ ድርሻ ማሳደግ፣ ሙያዊ የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻል፣ የደንበኞችን እምነት ማጠናከር እና የኩባንያውን ተወዳዳሪነት በቀጣይነት ማሳደግ የቀጣይ የስራ ዘመን ትኩረት እንዲሆኑ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ይህ የመጀመሪያው የዳይሬክተሮች ቦርድ ጉባኤ ኩባንያው ባለፉት ዓመታት ያስመዘገባቸውን መልካም ውጤቶች በማጠናከር፣ ያሉትን ዕድሎች በመጠቀም እና ለቀጣይ የስራ ዘመን የተሻለ ዕድገት የሚያስገኝ ጠንካራ የሥራ መሠረት በማስቀመጥ ረገድ ታሪካዊና ወሳኝ መድረክ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል።

የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የዳይሬክተሮች ቦርድ የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነው! ባህር ዳር — ነሀሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም.የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥ...
19/08/2026

የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የዳይሬክተሮች ቦርድ የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነው!

ባህር ዳር — ነሀሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም.
የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የዳይሬክተሮች ቦርድ የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤውን በባህር ዳር በድምቀት እያካሄደ ይገኛል።

በጉባኤው
1ኛ.የተከበሩ ዶ/ር አማኑኤል ፈረደ የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ፣
2ኛ. አቶ ጥላሁን ወርቅነህ የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል፣
3ኛ. አቶ ብርሃኑ ጣማለሁ የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል፣
4ኛ. አቶ ገሰጥ ጥላሁን የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል፣
5ኛ. ኢ/ር ፍስሃ ወንድይፍራው የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ ፀሐፊ፣ ተገኝተው በጉባኤው እየተሳተፉ ይገኛሉ። እንዲሁም ከፍተኛ የኩባንያው ኃላፊዎችም በጉባኤው በመገኘት የኩባንያውን የሥራ አፈጻጸምና የወደፊት ዕቅድ በተመለከተ ገለጻና ውይይት እያደረጉ ነው።

ጉባኤው የኩባንያውን የሥራ አቅጣጫ፣ የአፈጻጸም ሁኔታ እና የቀጣይ አመት የሥራ ዕቅድ በጋራ ለመገምገምና የኩባንያውን ቀጣይ የዕድገት አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚያስችል ወሳኝ መድረክ ነው።

የጉባኤው ዋና ዋና አጀንዳዎች ፦
👉 የቦርድ አባላት መተዋወቅ እና የቦርዱ መደበኛ የመሰብሰቢያ ጊዜ መወሰን፤
👉 ስለኩባንያው አመሠራረት፣ የሥራ አፈጻጸምና ያለበትን አሁናዊ ቁመና በተመለከተ መረጃ መለዋወጥ፤
👉 የ2018 ግማሽ በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም መገምገም፤
👉 የ2019 ዓ.ም. የኩባንያውን ዓመታዊ ዕቅድ መገምገምና ማጽደቅ፤
👉 የኩባንያውን የወደፊት ዕድገት፣ የተሻለ አመራር፣ ተጠያቂነትና የቦርድ–ማኔጅመንት ትብብርን ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።

የመጀመሪያው የዳይሬክተሮች ቦርድ ጉባኤ የኩባንያውን የተቀናጀ አመራር በማጠናከር፣ የሥራ አፈጻጸምን በመገምገምና ለቀጣይ ዘመን ግልጽና ተግባራዊ አቅጣጫ በማስቀመጥ ረገድ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሚሆን ይጠበቃል።

የፓክት አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን ድራፍት ሪፖርቶች የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።በአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ባለቤትነት እና በላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባ...
01/08/2026

የፓክት አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን ድራፍት ሪፖርቶች የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ባለቤትነት እና በላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ ጥናትና ዲዛይን ስራቸው እየተከናወኑ ያሉ የፓክት (PACT) አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክቶች ድራፍት ሪፖርቶች የግምገማ መድረክ ዛሬ ሀምሌ 25/2018 ዓ.ም. በባህርዳር ከተማ ተጀምሯል።

በመድረኩ ላይ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የመስኖ ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች፣ የፌደራል የፓክት ፕሮግራም አስተባባሪ፣ የክልል የፓክት (PACT) ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ እንዲሁም የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።

በዚህ የግምገማ መድረክ ላይ ኩባንያችን የጥናትና ዲዛይን ሥራ ውል ከወሰደባቸው 14 የፓክት አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክቶች መካከል የድራፍት ሪፖርታቸው የተጠናቀቁት አዊ ዞን ፋግታ ለኮማ ወረዳ (አፍፂሚ፣ ለብሲ 2፣ ዙማ) ሰሃላ ወረዳ (መሸሃ) እና ደላንታ ወረዳ (ተሬ) ፕሮጀክቶች ለውይይት የሚቀርቡ ይሆናል።

በግምገማው ሂደት የፕሮጀክቶቹ ሁሉም ሪፖርቶች ማለትም የውሃ ተፋሰስ (Watershed) ማኔጅመንት፣ የአፈር (Soil) ጥናት፣ የአግሮኖሚ ጥናት፣ የጂኦሎጂ ጥናት፣ የሃይድሮሎጂ ጥናት፣ የኢንጂነሪንግ ዲዛይን፣ የሶሺዮ–ኢኮኖሚና ፋይናንሺያል ትንተና፣ የአግሪ ቢዝነስና ማርኬቲንግ ጥናት፣ እንዲሁም የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ (Environmental Impact Assessment) በዝርዝር ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል።

የግምገማ መድረኩ ዓላማ የቀረቡትን የድራፍት ሪፖርቶች በገንቢ አስተያየቶችና በሙያዊ ምክረ ሀሳቦች በማዳበር፣ ጥራታቸውን የጠበቁ፣ በተፈለገው ደረጃ የተሟሉ እና ለትግበራ ዝግጁ የሆኑ የመጨረሻ (Final) ሪፖርቶች እንዲዘጋጁ ማስቻል ሲሆን፣ በመድረኩም ለሪፖርቶቹ ጥራት ማሻሻያ እና ለፕሮጀክቶቹ ስኬታማ አፈጻጸም ጉልህ አስተዋጽኦ የሚኖራቸው ገንቢ አስተያየቶችና ሙያዊ ምክረ ሀሳቦች ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል።

29/07/2026
7 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን ድራፍት ሪፖርት ግምገማ በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ፡፡ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባለቤትነት የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይን እና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የጥናትና...
23/07/2026

7 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን ድራፍት ሪፖርት ግምገማ በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባለቤትነት የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይን እና ቁጥጥር ሥራዎች ኩባንያ የጥናትና ዲዛይን ስራቸው በመከናወን ላይ ያሉ 7 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የድራፍት ሪፖርቶች የግምገማ መድረክ በአዲስ አበባ በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።

በግምገማው ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚመለከታቸው ከፍተኛ ባለሙያዎች እና የኩባንያችን የጥናትና ዲዛይን ባለሙያዎች ተሳትፈው የድራፍት ሪፖርቶቹን በዝርዝር ገምግመዋል።

በግምገማው ሂደት የጥናቱን ጥራትና ተግባራዊነት የሚያጎለብቱ ገንቢ አስተያየቶችና ሙያዊ ምክረ ሃሳቦች የቀረቡ ሲሆን እነዚህን በማካተት የመጨረሻ (Final) ሪፖርቶቹ ተሻሽለው እንዲቀርቡ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

እነዚህ ፕሮጀክቶች በአማራ ክልል በታች አርማጭሆ ወረዳ (ዶጋው እና ሙሴ ባምብ የገጠር ከተማ) ፣ በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ (ማህረሽ የገጠር ከተማ) ፣ በጭልጋ ወረዳ (ጫንድባ እና ጮንጮቅ የገጠር ከተማ) እና በመተማ ወረዳ (ሽንፋ እና ዳስ ጉንዶ የገጠር ከተማ) የሚገኙ ሲሆን፣ ወጪያቸው ሙሉ በሙሉ በዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እተከናወነ ይገኛል።

ከታች ያሉትን የማህበራዊ ኦፊሻል ድህረ-ገፆቻችንን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ!
🔹 Official Website: https://www.lalibeladesign.net
🔹 Facebook: https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
🔹 Telegram: https://t.me/lalibelaSDSWPLC
# መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ Like & share ያድርጉ!

የባህር ዳር ከተማ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክትን የጥናትና ዲዛይን ሥራ የውስጥ ሪቪው እየተካሄደ ነው::ልህቀት የዲዛይንና ቁጥጥር ኮርፖሬሽን እና ላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይና ቁጥጥር ስራወች ኩባንያ በጋራ...
18/07/2026

የባህር ዳር ከተማ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክትን የጥናትና ዲዛይን ሥራ የውስጥ ሪቪው እየተካሄደ ነው::

ልህቀት የዲዛይንና ቁጥጥር ኮርፖሬሽን እና ላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይና ቁጥጥር ስራወች ኩባንያ በጋራ እየሰሩት የሚገኘው የባህር ዳር ከተማ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክትን የጥናትና ዲዛይን ሥራ የሃይድሮጅኦሎጅካል ኢንቨስቲጌሽን (Hydrogeological investigation) ሥራው በልህቀት የዲዛይንና ቁጥጥር ኮርፖሬሽን አዳራሽ የውስጥ ሪቪዉ ዛሬ 11.11.2018 ዓ.ም እየተካሄደ ይገኛል::
በሪቪው የሁለቱም አማካሪዎች የሚመለከታቸው አመራሮችና ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።

🦺 የግንባታ የስራ ላይ ደህንነት የሁላችንም ኃላፊነት ነው!"Safety First – Every Life Matters!"በግንባታ ፕሮጀክቶች የሚደርሱ አደጋዎች ሊከላከሉ ይችላሉ። አንድ የተወሰደ ...
16/07/2026

🦺 የግንባታ የስራ ላይ ደህንነት የሁላችንም ኃላፊነት ነው!
"Safety First – Every Life Matters!"
በግንባታ ፕሮጀክቶች የሚደርሱ አደጋዎች ሊከላከሉ ይችላሉ። አንድ የተወሰደ የደህንነት እርምጃ የሰውን ሕይወት ሊያድን ይችላል።

⚠️ በግንባታ ቦታ የሚከሰቱ ዋና ዋና አደጋዎች
🔸 ከከፍታ ላይ መውደቅ
🔸 በሚወድቁ ወይም በሚንቀሳቀሱ እቃዎች መመታት
🔸 በማሽኖች ወይም በቁፋሮ ውስጥ መጭመቅ
🔸 የኤሌክትሪክ አደጋ
🔸 ለአቧራ፣ ለኬሚካሎች፣ ለጫጫታና ለንዝረት በተደጋጋሚ መጋለጥ

🛡️ አደጋን እንዴት እንቀንስ?
✅ ሁልጊዜ የግል መከላከያ ቁሳቁሶች (PPE) ይጠቀሙ።
⛑️ የደህንነት ኮፍያ • 👷 የደህንነት ጫማ • 🥽 መነጽር • 🧤 ጓንት • 🪢 የደህንነት ማሰሪያ (Harness)
✅ ከስራ በፊት የደህንነት ስልጠና እና Toolbox Talk ማካሄድ
✅ አደገኛ ቦታዎችን በግልጽ ምልክቶች ማሳወቅ
✅ የመጀመሪያ እርዳታ እና የድንገተኛ አደጋ እቅድ ዝግጁ ማድረግ

🤝 የማን ኃላፊነት ነው?

🏢 የፕሮጀክት ባለቤት (Client)
✔️ ለደህንነት በቂ በጀት መመደብ
✔️ ብቁ ተቋራጮችን መምረጥ
✔️ የደህንነት አፈጻጸምን መከታተል

👷 ተቋራጭ (Contractor)
✔️ Personal Protective Equipment ( PPE) ማቅረብና መጠቀሙን ማረጋገጥ
✔️ ለሰራተኞች የደህንነት ስልጠና መስጠት
✔️ አደጋን በቅድሚያ መከላከል

📐 አማካሪ (Consultant)
✔️ ደህንነትን ያማከለ ዲዛይን (Design for Safety) ማዘጋጀት
✔️ የደህንነት እቅዶችን ማጽደቅና መከታተል
✔️ የግንባታ ስራዎች የደህንነት መመሪያዎችን እየተከተሉ መሆኑን በጥብቅ መቆጣጠር

📜 ሕግ ምን ይላል?
የሰራተኛ ደህንነት የሕግ ግዴታ ነው።
✔️ የILO ኮንቬንሽን 167(Safety and Health in Construction Convention) በግንባታ ስራ ላይ መተግበር ያለባቸውን የደህንነት መስፈርቶች በዝርዝር ያስቀምጣል።
✔️ የአሜሪካ የስራ ደህንነትና ጤና አስተዳደር (OSHA) እና የ ISO 45001 በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባታ ቦታዎች ላይ አደጋን ለመቀነስ የሚያስችሉ የስራ ደህንነት አስተዳደር ስርዓቶችን (OHS Management Systems) ለመዘርጋት እንደ መመሪያ ያገለግላሉ።
✔️ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ህገ-መንግስት (አንቀጽ 42) ሰራተኞች ጤንነታቸውና ደህንነታቸው የተጠበቀ የስራ አካባቢ የማግኘት መብት እንዳላቸው ይደነግጋል።
✔️ የሠራተኛና አሰሪ ግንኙነት አዋጅ 1156/2011በአዋጁ ምዕራፍ ሰባት ላይ ስለ ስራ ላይ ደህንነት፣ ጤንነትና የስራ አካባቢ ጥበቃ፤ አሰሪው ለሰራተኛው ተገቢውን የደህንነት መጠበቂያ እቃዎች የማቅረብ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የስራ ቦታ የመፍጠር ግዴታ እንዳለበት ያስገነዝባል።
✔️ የህንጻ አዋጅ እና መመሪያዎች: የግንባታ ስራዎች ከመጀመራቸው በፊት የደህንነት እቅድ መኖር እንዳለበትና አተገባበሩም ክትትል እንደሚደረግበት ይደነግጋሉ።

💡 መልዕክታችን
"የስራ ደህንነት ተጨማሪ ወጪ ሳይሆን የሰው ሕይወትን፣ የፕሮጀክት ጥራትን እና የሥራ ውጤታማነትን የሚጠብቅ ዋና መሠረት ነው።"
የLalibela Study, Design & Supervision Works PLC የፕሮጀክቶች ጥራት፣ ደህንነት እና ዘላቂነት የሙያችን መሠረታዊ እሴቶች ናቸው። ከጥናት እስከ ዲዛይን፣ ከግንባታ ቁጥጥር እስከ ፕሮጀክት ርክክብ ድረስ የሰው ሕይወትን እና የሥራ ደህንነትን በቅድሚያ እናስቀምጣለን።

ከታች ያሉትን የማህበራዊ ኦፊሻል ድህረ-ገፆቻችንን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ!
🔹 Official Website: https://www.lalibeladesign.net
🔹 Facebook: https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
🔹 Telegram: https://t.me/lalibelaSDSWPLC
# መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ Like & share ያድርጉ!

በኩባንያችን እየተሰሩ ሚገኙ 14 የፓክት አነስተኛ መስኖ ጥናትና ዲዛይን ፕሮጀክቶች ፕሮግረስ ሪፖርት ተገመገመ፡፡(ሰኔ 10/2018 ዓ.ም) በኩባንያችን በሂደት ላይ የሚገኙ የፓክት አነስተኛ ...
17/06/2026

በኩባንያችን እየተሰሩ ሚገኙ 14 የፓክት አነስተኛ መስኖ ጥናትና ዲዛይን ፕሮጀክቶች ፕሮግረስ ሪፖርት ተገመገመ፡፡

(ሰኔ 10/2018 ዓ.ም) በኩባንያችን በሂደት ላይ የሚገኙ የፓክት አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክቶች የመስክ ስራ እና የድራፍት ሪፖርት አፈጻጸምን በተመለከተ ከባለሙያዎች ጋር ዝርዝር የውይይትና የግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

ውይይቱን የኩባንያው ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢ/ር ፍስሃ ወንድይፍራው እና የኩባንያው የመጠጥ ውሃና መስኖ ስራዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ መዝገቡ ዮሃንስ የመሩት ሲሆን የመስክ ስራዎች አፈፃፀም እና ድራፍት ሪፖርት ያለበት ደረጃ በባለሙያች ቀርቦ ዝርዝር ውይይት ተደርጎበታል ።

የመጠጥ ውሃና መስኖ ሥራዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ መዝገቡ ዮሃንስ በሰጡት ማብራሪያ ኩባንያችን በአጠቃላይ 14 የፓክት አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክቶችን ለመስራት ውል ወስዶ ወደ ሥራ መግባቱን ገልጸው የሥራዎቹን ወቅታዊ ደረጃ፣ በሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችንና መወሰድ የሚገባቸውን የመፍትሄ እርምጃዎች አስመልክቶ በዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።።

የኩባንያው ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢ/ር ፍስሃ ወንድይፍራው በበኩላቸው ባለሙያዎቹ ያሉትን ወቅታዊ ችግሮች በፅናት ተቋቁመው የመስክ ሥራውን በማጠናቀቃቸው ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ ባለሙያዎች ይህንን ቁርጠኝነት በማስቀጠል የድራፍት ሪፖርቶቹን እስከ ተቀመጠው ቀነ-ገደብ እንዲያጠናቅቁ አስገንዝበዋል።

ውይይቱም በስራ ሂደት ላይ በየደረጃው ለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች አፋጣኝ መፍትሄዎችን በመስጠት እያንዳንዱ ባለሙያና የስራ ኃላፊ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣትና ስራዎቹን በላቀ ውጤታማነት ለማጠናቀቅ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ተጠናቋል።

12/06/2026
የስራ ቅጥር ማስታወቂያ !(ቀን ሰኔ/03/2018  ዓ.ም) የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይን እና ቁጥጥር ስራዎች ኃ.የተ.የግ.ማ  ለኩባንያው በተገለፀው የስራ መደብ  አመልካቾችን አወዳደሮ መቅጠር ይ...
10/06/2026

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ !

(ቀን ሰኔ/03/2018 ዓ.ም) የላሊበላ ጥናት፣ ዲዛይን እና ቁጥጥር ስራዎች ኃ.የተ.የግ.ማ ለኩባንያው በተገለፀው የስራ መደብ አመልካቾችን አወዳደሮ መቅጠር ይፈልጋል።

ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን!

Address

Bahir Dar
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lalibela Study Design & Supervision Works PLC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Lalibela Study Design & Supervision Works PLC:

Shortcuts

Share