BahirDar Health Science College-ባህር ዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ

BahirDar Health Science College-ባህር ዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ Welcome to Bahirdar Health Science College, this is one of the three oldest mid-level health care Ins

for more information Ping us on +251582222099

የባህርዳር  ጤና  ሳይንስ  ኮሌጅ  ሰራተኞች  ለተማሪዎች  የትምህርት  ቁሳቁስ  ድጋፍ  አደረጉ=========መስከረም 06/2019 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) — የባህርዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ...
16/09/2026

የባህርዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሰራተኞች ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
=========
መስከረም 06/2019 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) — የባህርዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሰራተኞች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ እንዳይርቁ በማሰብ 1,800 ደብተሮችና 500 እስክርቢቶዎችን ድጋፍ አደረጉ።

ድጋፉ የተደረገው ከኮሌጁ ሰራተኞች በተሰበሰበ ገንዘብ ሲሆን፣ የትምህርት ቁሳቁሶቹም ለአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስረክበዋል።

ድጋፉን የተቀበሉት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ መኳንት አደመ፣ የኮሌጁ ሰራተኞች በራሳቸው ተነሳሽነት ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ሳቢያ ከትምህርት ገበታ እንዳይርቁ የሚደረጉ ተግባራት ትልቅ ማህበራዊ አስተዋፅኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል።

ድጋፉን ያስረከቡት የባህርዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን አቶ ሙሉቀን አሰፋ በበኩላቸው፣ የኮሌጁ ሰራተኞች በየዓመቱ ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ተግባራትን ማከናወናቸውን ገልጸዋል።
በዚህ ዓመትም አንድም ተማሪ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት እንዳይርቅ በማሰብ ሰራተኞቹ በጋራ ድጋፍ ማድረጋቸውን የገለጹት ዲኑ ለሰራተኞች የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።

በቀጣይም ተመሳሳይ የበጎ አድራጎትና የትምህርት ድጋፍ ተግባራትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ ሙሉቀን ገልጸዋል።
በአማራ ክልል አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ መርሃ ግብር በርካታ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ድርጅቶች፣ግለሰቦችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በስፋት እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ
1. በዌብ ሳይት ገጻችን http://www.anrseb.gov.et/
2. በዩቱብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCARNQWN5bm5z2JmKsC_Cn8w
3. በፌስ ቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Amhara-Education-Bureau
4. በቴሌግራም ቻናላችን t.me/anrse
ያግኙን
5. በቲክቶክ ገፃችን bureau

KEMBANGTOTO memelopori enterprise situs toto 4D tertata rapi poling togel mudah akses melalui penyusun antarmuka terstruktur yang mempermudah pemantauan pilihan angka secara intuitif.

16/09/2026
16/09/2026
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ
16/09/2026

ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት አደረሳችሁ!2019 ዓ.ም. ለሁላችንም የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የደስታ ዓመት ይሁን!መልካም አዲስ ዓመት!፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥...
10/09/2026

እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት አደረሳችሁ!
2019 ዓ.ም. ለሁላችንም የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የደስታ ዓመት ይሁን!
መልካም አዲስ ዓመት!
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
Happy Ethiopian New Year 2019 E.C. !
May 2019 E.C. bring us all a year of peace, good health, love, and happiness.
Happy Ethiopian New Year!

BahirDar Health Science College-ባህር ዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የባህር ዳር ከፍተኛ ትምህርት ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጤናው የትምህርት ዘርፍ  በዲፕሎማ ፕሮግራም ያሰለጥናቸው 5...
18/07/2026

BahirDar Health Science College-ባህር ዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
የባህር ዳር ከፍተኛ ትምህርት ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጤናው የትምህርት ዘርፍ በዲፕሎማ ፕሮግራም ያሰለጥናቸው 5 መቶ 56 ተማሪዎችን አስመረቀ

‎በመርሀግብሩ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አበበ ተምትሜ በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ በመገኘት እንደተናገሩት መንግስት በአካል የጠነከረ በአእምሮ የበለጸገ ብቁና ክህሎት ያለው የሰው ሃይል በማፍራት እየሰራ ነው ብለዋል።

‎በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሚዛናዊ አስተሳሰብ ለሀገርና ለዜጎች ሁለንተናዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታልም ብለዋል።

‎ጤና ሳይንስ ኮሌጁ በክልሉ በጤናው ዘርፍ ብቁ የሆኑ የጤና ባለሞያዎችን እያፈራ ይገኛል ያሉት አቶ አበበ ተምትሜ ናቸው።

‎የባህርዳር ከፍተኛ ትምህርት ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን የሆኑት አቶ ሙሉቀን አሰፋ በበኩላቸው ኮሌጁ ለ49 አመታት የጀመረውን የጤና ባለሞያዎች ስልጠና በተለያዩ ደረጃዎች በማሳደግ በ2018 ዓ.ም ሙሉ እውቅና በማግኘት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጸዋል።

‎አቶ ሙሉቀን አክለውም በእለቱ በነርሲግ፣ ፓርማሲ ፣ ድገተኛ ህክምና እና በጤና ኤክስቴንሽን ማሻሻያ ከ5መቶ 56 ተማሪዎች መካከል 4መቶ 93 ሴቶች መሆናቸውን ጠቅሰው ተመራቂ ተማሪዎች የሚጠበቅባቸውን የሞያ ግዴታ በስነ-ምግባርና በሃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

‎በዕለቱም በቆይታቸው የላቀና የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ልዩ የዋንጫና የሜዳሊያ ሽልማት ተበርክቶ

‎ተመራቂ ተማሪዎች እንደተናገሩት በቀጣይም በተማሩበት የትምህርት መስክ በራሳቸው አቅም ስራ በመፍጠር ራሳቸውን እና ማህበረሰቡን ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

‎በምረቃ መርሃግብሩ ላይም የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የኮሌጁ አመራሮች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች፣ ተመራቂ ተማሪዎችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል::

‎ #አብክመጤናቢሮ


Amhara Health Bureau - አብክመ ጤና ቢሮ
Medical Information
Amhara Public Health Institute/APHI/
Ministry of Health,Ethiopia
Ministry of Education Ethiopia
‎ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም

18/07/2026
18/07/2026

Address

Bahirdar
Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when BahirDar Health Science College-ባህር ዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to BahirDar Health Science College-ባህር ዳር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ:

Shortcuts

Share