Bahir Dar Academy

Bahir Dar Academy Bahir Dar Academy is One of the Best school in Bahir Dar which was Established in 2001 G.C (1994 E.C). It is a private School.

The School teaches from nursery to grade 12 encompassing kindergarten, elementary and secondary school.

ማንበብ ሙሉ ሰዉ ያደርጋል፡፡የሰዉ ልጅ ማንበብ ሲያቆም ይሞታል ይላሉ ታላላቅ ፈላስፋዎች፡፡ባህር ዳር አካዳሚ ማንበብን ለልጆች ማስተማር ያለዉን ከፍተኛ ጥቅም ይረዳል፡፡ በዚህም ከልጅነታቸዉ ...
13/03/2022

ማንበብ ሙሉ ሰዉ ያደርጋል፡፡የሰዉ ልጅ ማንበብ ሲያቆም ይሞታል ይላሉ ታላላቅ ፈላስፋዎች፡፡ባህር ዳር አካዳሚ ማንበብን ለልጆች ማስተማር ያለዉን ከፍተኛ ጥቅም ይረዳል፡፡ በዚህም ከልጅነታቸዉ ልጆች አንባቢ ሆነዉ እንዲታነጹ ጥረት ያደርጋል፡፡ ከ1-4ኛ ክፍል ተማሪዎች በት/ቤቱ የሚከበረዉን የንባብ ቀን እንዲህ በደመቀ መልኩ በማንበብ ያከብራሉ፡፡ እናንተ የነገ ተስፋዎቸች ሀገር ተረካቢዎች በማንበብ፣በመመራመር እና በስነ-ምግባር የምትመራ ሀገር ከፊታችሁ አለቻችሁ እና በርትታችሁ አንባቢ ሁኑ፡፡

የባህር ዳር አካዳሚ የዋናው ግቢ የkg-3 ተመራቂ ተማሪዎች የባህር ዳር ኤር ፖርትን ጎብኝተዋል ፡፡ በዚህም እጅግ አስደሳች እና ትምህርታዊ ጊዜ አሳልፈዋል፡፡ ይህንን ላመቻቹ መምህራን እና ...
13/03/2022

የባህር ዳር አካዳሚ የዋናው ግቢ የkg-3 ተመራቂ ተማሪዎች የባህር ዳር ኤር ፖርትን ጎብኝተዋል ፡፡ በዚህም እጅግ አስደሳች እና ትምህርታዊ ጊዜ አሳልፈዋል፡፡ ይህንን ላመቻቹ መምህራን እና አስተዳዳሪዎች እናመሰግናለን፡፡

ባህር ዳር አካዳሚ አባይ ካንፖስ የኬጅ-3 ተመራቂዎች ጉብኝት ባህር ዳር ስታድየም አድርገዋል፡፡ በዚህም እጅግ አስደሳች እና ትምህርታዊ ጊዜ አሳልፈዋል፡፡ ዕጻናት ሲደሰቱ እንደማየት የሚያደስ...
13/03/2022

ባህር ዳር አካዳሚ አባይ ካንፖስ የኬጅ-3 ተመራቂዎች ጉብኝት ባህር ዳር ስታድየም አድርገዋል፡፡ በዚህም እጅግ አስደሳች እና ትምህርታዊ ጊዜ አሳልፈዋል፡፡ ዕጻናት ሲደሰቱ እንደማየት የሚያደስት ነገር የለም፡፡ ይህንን ላመቻቹ መምህራን እና አስተዳዳሪዎች እናመሰግናለን፡፡

የባህር ዳር አካዳሚ በሁሉም ካምፓሶች  የ1-4ኛ ግቢ ፣የ5-8ኛግቢ  እና የ9-12 ኛ ግቢ)በመጀመሪያዉ ሴሚስተር  ከ90 በላይ አማካይ ዉጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን የሰርተፊኬት (Excelle...
03/03/2022

የባህር ዳር አካዳሚ በሁሉም ካምፓሶች የ1-4ኛ ግቢ ፣የ5-8ኛግቢ እና የ9-12 ኛ ግቢ)በመጀመሪያዉ ሴሚስተር ከ90 በላይ አማካይ ዉጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን የሰርተፊኬት (Excellent Award) ሽልማት በመስጠት ዕዉቅና ሰጧል፡፡ ተማሪዎች የልፋታችሁ ዉጤት ነዉና ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ወላጆችም ለነበራችሁ ድጋፍ እናመሰግናለን፡፡

የኢትዮጵያዊያን ኩራት፤ የአፍሪካዉያን የነጻነት ጮራ ፈንጣቂ፤ የጥቁሮች ትግል ፋና ወጊ የሆነዉ የአድዋ በዓል ለልጅ ልጆቻችን የምናስተምረዉ አባቶቻችን የከፈሉት የደም ዋጋ ነዉ፡፡ ልጆች በት/...
03/03/2022

የኢትዮጵያዊያን ኩራት፤ የአፍሪካዉያን የነጻነት ጮራ ፈንጣቂ፤ የጥቁሮች ትግል ፋና ወጊ የሆነዉ የአድዋ በዓል ለልጅ ልጆቻችን የምናስተምረዉ አባቶቻችን የከፈሉት የደም ዋጋ ነዉ፡፡ ልጆች በት/ቤት ደረጃ ሊማሩት እና ሊያከብሩት ይገባል፡፡ አጼ ሚኒሊክ ጦርነቱን ያነሳሱበት እና የመሩበት ብልሃት፣የነበረዉ ህብረት እና መናበብ፣ መተሳሰብ በጋራ መስራ፣ለነጻነት መሞት….ወዘተ የሚሉት ነገሮች ልጆቻችን ከታሪካቸዉ ተምረዉ ለሀገራቸዉ ጠንክረዉ እንዲማሪ እና እንዲሰሩ ያደርጋቸዋል፡፡
የባህር ዳር አካዳሚ ተማሪዎች የ126 ኛዉን የአድዋን በዓል እንዲህ ነበር ያከበሩት፡፡በአሁኑ ሰዓት አድዋ ሲነሳ ስሙዋ አብሮ የሚነሳዉ እንቁዋ አርቲስት እጅጋየሁ ሽባባዉ እንዲህ ስለአድዋ አዚማለች፡፡
የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት
ሰው ተከፍሎበታል ከደም እና ከአጥንት
ስንት ወገን ወደቀ በነፃነት ምድር
ትናገር ዓድዋ ትናገር ትመስክር
ትናገር ዓድዋ ትናገር ሀገሬ
እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ
በኩራት ... በክብር ... በደስታ ... በፍቅር ... በድል

#ኢትዮጵያ
ለተከፈለልን ዋጋ ባለዕዶች ነን ። እናመሠግናለን

ከታች በምስሉ የምትታየዉ ልጅ ሰላማዊት እሸቱ ትባላለች፡፡ባህር ዳር አካዳሚ ካፈራቸዉ ተፅእኖ ፈጣሪ ሴት ተማሪዎች ዉስጥ አንዱዋ ነች፡፡የቀድሞ የባህር ዳር አካዳሚ  ጎበዝ ተማሪ ነች፡፡ህክምና...
04/02/2022

ከታች በምስሉ የምትታየዉ ልጅ ሰላማዊት እሸቱ ትባላለች፡፡ባህር ዳር አካዳሚ ካፈራቸዉ ተፅእኖ ፈጣሪ ሴት ተማሪዎች ዉስጥ አንዱዋ ነች፡፡የቀድሞ የባህር ዳር አካዳሚ ጎበዝ ተማሪ ነች፡፡ህክምና ትምህርቱዋን ተከታትላ አሁን በአፍሪካም ሆነ በኢትዮጵያ በተለያዩ ስብሰባዎች ንግግር በማድረግ ሀገሩዋን እና የተማረችበትንም ሆነ የኖረችበትን ህብረተሰብ ስም በበጎ እያስጠራች ትገኛለች፡፡ከዚህ በታች የምትመለከቱት ምስልም የሀበሻ ቀሚሱዋን ለብሳ ይህች ድንቅ ልጅ በ38ኛ የአፍሪካ አንድነት ስብሰባ ላይ በሚካሄደዉ የከፍተኛ ደረጃ የደረሱ ወጣት ፓናሊስቶች ስብሰባ ላይ ተጋብዛ በመሳተፍ ላይ ትገኛለች፡፡ ይህች ድንቅ የባህር ዳር አካዳሚ ፍሬ ‘’ልጅ ሆኘ በትልቅ መድረክ የሀበሻ ቀሚስ በኩራት ለብሸ ሀገሬን ማሳወቅ እፈልግ ነበር ይህንንም እያሳካሁ ነዉ’’ በማለት በfacebook ገጹዋ ላይ ተናግራለች፡፡ ት/ቤቶች በርትተዉ ሲሰሩ ሁሌም የሚያስተምሩዋቸዉ ተማሪዎች የሀገራቸዉን ምንነት ጠንቅቀዉ የሚረዱ፣በዕዉቀት ተፈላጊ የሆኑ እንዲሁም በባህላቸዉ እና በማንነታቸዉ የሚኮሩ እንደሚሆኑ ማሳያ ይህችዉ ታታሪ ልጅ ነች፡፡በርች ህብረተሰብሽንም ሆነ ሀገርሽን ለማገልገል የምትታትሪ እንደምትሆኝ አንጠራጠርም፡ እንላለን፡፡

26/01/2022
The Benefits of Reading Books.
14/01/2022

The Benefits of Reading Books.

ጥር ወር ለት/ቤቶች እና ለተማሪዎች ጠንካራ ስራዎች የሚሰራበት ወር ነዉ፡፡ በተለይ የመጀመሪያዉ ወሰነ ት/ት የማጠቃለያ ፈተና የሚሰጠዉ በዚህ ወር በመሆኑ ተማሪዎች ጠንክረዉ  እና ከዚህ በፊ...
13/01/2022

ጥር ወር ለት/ቤቶች እና ለተማሪዎች ጠንካራ ስራዎች የሚሰራበት ወር ነዉ፡፡ በተለይ የመጀመሪያዉ ወሰነ ት/ት የማጠቃለያ ፈተና የሚሰጠዉ በዚህ ወር በመሆኑ ተማሪዎች ጠንክረዉ እና ከዚህ በፊት ከለመዱት የጥናት ጊዜ የበለጠዉን መስራት እና እራሳቸዉን ለፈተና ዝግጁ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በመጸሃፍቶች የተደራጀዉ የባህር ዳር አካዳሚ ቤተ-መጸሃፍት ደግሞ እንደወትሮዉ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ በሳምንት 6 ቀን ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ምሽት 12፡00 ድረስ ተማሪዎች ን ያስጠቅማል፡፡የ2014 ዓ.ም ተማሪዎችም ከአለፈዉ አመት በተሻለ መልኩ በማጥናት እንዲህ ቤተ-መጸሃፍቱን አጨናንቀዉታል፡፡ማንበብ ሙሉ ሰዉ ያደርጋል፡፡የማያነብ ሰዉ ደግሞ እንደሞተ ሰዉ ነዉ ይባላል እና ተማሪዎቻችን በርቱ እንላለን፡፡

መልካም የገና በዓል ይሁንልዎ!!!
07/01/2022

መልካም የገና በዓል ይሁንልዎ!!!

ዛሬ በቀን 26/04/2014 ዓ.ም የባህር ዳር አካዳሚ  የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን የሂሳብ ብቃት ለመመዘን ድንገተኛ ፈተና  ተሰጧቸዋል፡፤ ይህ የሂሳብ ት/ት ፈተና የተማሪዎችን የሂሳብ ክህሎት...
05/01/2022

ዛሬ በቀን 26/04/2014 ዓ.ም የባህር ዳር አካዳሚ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን የሂሳብ ብቃት ለመመዘን ድንገተኛ ፈተና ተሰጧቸዋል፡፤ ይህ የሂሳብ ት/ት ፈተና የተማሪዎችን የሂሳብ ክህሎት ለመለካት እንዲሁም ያለባቸዉን ክፍተት ለማወቅ እና ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያግዝ ነዉ፡፡ በተለይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የዚህ አመት የብሄራዊ ፈተና ተፈታኞች እንደመሆናቸዉ የተሰጣቸዉ ፈተና እራሳቸዉን የሚያዩበት እንደሚሆን ጥርጥር የለዉም፡፡በባህርዳር አካዳሚ በሁሉም ክፍሎች በአመት አንዴ የተለያዩ የብቃት ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡ ይህም ት/ቤቱ የተማሪዎችን አቅም የሚለካበት እና ክፍተቶችን በተሎ ለመሙላት የሚዉል ሲሆን ት/ቤቱ ለት/ት ጥራት ያለዉን ትኩረት የሚያሳይ ነዉ፡፡በዚህ ፈተና የተሳተፋችሁ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ስለነበራችሁ ተሳትፎ እና ስላሳያችሁት ስነምግባር እጅግ በጣም እናመሰግናለን፡፡

Address

Bahir Dar

Opening Hours

Monday 01:30 - 16:30
Tuesday 01:30 - 16:30
Wednesday 01:30 - 16:30
Thursday 01:30 - 16:30
Friday 01:30 - 16:30

Telephone

+251582208313

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahir Dar Academy posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Bahir Dar Academy:

Shortcuts

Share

Category