11/05/2026
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለስምንት አንጋፋ ምሁራኑ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ!
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፤ በምርምር፣ በመማር ማስተማር እና በከፍተኛ የማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ላቅ ያለ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 8 (ስምንት) ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት (Full Professorship) ማዕረግ እድገት መፍቀዱን በታላቅ ደስታ ይገልጻል።
እነዚህ ምሁራን ለዓመታት በእውቀት ሽግግር እና በሳይንሳዊ ምርምር ዘርፍ ላሳዩት ትጋትና ለሀገራዊ ዕድገት ላበረከቱት የማይተካ ሚና ይህ ከፍተኛ የአካዳሚክ ማዕረግ የሚገባቸው መሆኑ በቦርዱ ተረጋግጧል።
የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ያገኙ ምሁራን ዝርዝር፡
1. ፕሮፌሰር አባይነህ ሙንሼ አብተው – በባዮሜዲካል ሳይንስ (Biomedical Sciences)
2. ፕሮፌሰር አያሌው ወንዴ መለሰ – በውሃ አካላት ኢኮሎጂ እና አስተዳደር (Wetland (Aquatic) Ecology and Management)
3. ፕሮፌሰር ዳዊት አስራት ጌታሁን – በ Educational Psychology
4. ፕሮፌሰር ደሳለኝ እጅጉ ብርሐኔ – በዱር እንስሳት ኢኮሎጂ እና ጥበቃ (Wildlife Ecology & Conservation)
5. ፕሮፌሰር ፍቅረሰላም ጋረድ መንግሥቱ – በኮሙኒኬሽን ኢንጂነሪንግ (Communication Engineering)
6. ፕሮፌሰር ጌታሁን የማታ ሉሌ – በዕፅዋት ኢኮፊዚዮሎጂ (Plant Ecophysiology)
7. ፕሮፌሰር ጌትነት ታምሩ ጥግነህ– በ Inorganic Chemistry
8. ፕሮፌሰር ማተብ ታፈረ ገድፈው – በትምህርት ፖሊሲ እና አመራር (Education Policy and Leadership)
ዩኒቨርሲቲያችን ለተከበራችሁ ፕሮፌሰሮች፣ ለቤተሰቦቻችሁ እንዲሁም ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ "እንኳን ደስ አላችሁ" እያለ፤ ወደፊትም በምርምርና በፈጠራ ስራዎቻችሁ የዓባይ ጓዳ የሆነችውን እናት ዩኒቨርሲቲያችሁንና ሀገራችሁን በበለጠ እንድታገለግሉ ይመኛል።
ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ!
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
The Bahir Dar University board, in its meeting held on May 11, 2026, has approved the promotion of eight researchers from Associate Professor to Full Professor.
Congratulations to our esteemed academic staff on your well-deserved promotion to Full Professor. This achievement recognizes years of effective teaching, dedicated research, and outstanding contributions to your university and the broader community.
1. Dr. Abaineh Munshea Abitew: Professor of Biomedical Sciences
2. Dr. Ayalew Wondie Melese: Professor of Wetland (Aquatic) Ecology and Management
3. Dr. Dawit Asrat Getahun: Professor of Educational Psychology
4. Dr. Dessalegn Ejigu Berhane: Professor of Wildlife Ecology & Conservation
5. Dr. Fikreselam Gared Mengistu: Professor of Communication Engineering
6. Dr. Getahun Yemata Lule: Professor of Plant Ecophysiology
7. Dr. Getinet Tamiru Tigineh፡ Professor of Inorganic Chemistry
8. Dr. Mateb Tafere Gedifew: Professor of Education Policy and Leadership
Congratulations