16/11/2023
ጤና ይስጥልን::
📩 ለአብርሆተ ሰብእ የትምህርት ሥልጠናና ንግድ አክሲዮን ማኅበር ባለአክሲዮኖች 📩
✍️ጉዳዩ : የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ
👁ቀን: ኅዳር 23/2016 ዓ/ም
👁እለት: እሁድ
👁ሰዓት፡ ከጧቱ 3፡00 ጀምሮ
👁ቦታ፡ ባሕር ዳር ከተማ በሙሉዓለም የባሕል ማዕከል
1. የመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች
1.1. የ2015 በጀት ዓመት ሥራ አፈፃፀም ሪፖርት
1.2. የ2015 በጀት ዓመት ኦዲት ሪፖርት
1.3. የ2016 በጀት ዓመት እቅድ
2. የአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች፡
2.1. የአባላት ጉዳይ
2.2. ደንብ ማሻሻል
2.3. የቦርድ አባላትን ማሟላት
ማሳሰቢያ፡- በስብሰባው መገኘት የማይችሉ ከሆነ የዳይሬክተሮች ቦርድ ባዘጋጀው የመወከያ ቅፅ አልያም በፍትሕ ጽ/ቤት ወክለው ከስብሰባው እለት 3 ቀን ቀድመው በአካል ወይም በኢሜል [email protected] ለአክሲዮን ማኅበሩ እንዲያሳውቁ፡፡
መወከያ ቅፁን በድርጅቱ ቢሮ/ቴሌግራም/ድረ ገፅ ላይ ያገኙታል።
ኑ! ትውልድ እንሥራ!
የዳይሬክተሮች ቦርድ