26/04/2026
Shalom Business and Technology College organized a workshop training for technical and vocational graduating students under the title: “Skills for a Successful Entrepreneurship.”
The training was delivered by Mr. Leul Endale, who is the Director of Institutional Capacity Building and Quality Assurance at the Sidama Regional State Bureau of Labor, Skills, and Enterprise Development.
During the training, technical and vocational trainees and prospective graduates were given broad awareness on the importance of technical and vocational education. They were also advised that after graduation, they should focus on creating their own jobs (entrepreneurship) rather than relying solely on employment opportunities.
At the end of the training, the college dean, Dr. Tsegaye Mathewos, explained that the training was important and timely. He stated that the trainees gained valuable understanding. Certificates of participation were then awarded to the trainer, Mr. Leul Endale, and the student trainees, marking the conclusion of the day’s workshop.
25/04/2026
ሻሎም ዜና
ሻሎም ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ለቴክኒክ እና ሙያ ተመራቂ ተማሪዎች "Skills for a successful Entrepreneurship" (ለስኬታማ ወደፊት የክህሎቶች አስፈላጊነት) በሚል ርዕስ "Work shop" ስልጠና ተሰጠ።
ለተመራቂ ተማሪዎች ስልጠና የሰጡት አቶ ልዑል እንዳለ የሲዳማ ብሄራዊ ክልል ሥራ ክህሎት እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የተቋማት አቅም ግንባታና ጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ናቸው።
በስልጠናውም የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኝ እና እጩ ምሩቃን ተማሪዎች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አስፈላጊነት እና ከምረቃ በኋላ ሰልጣኞች ሥራ ፈጠራ ላይ እንጂ ተቀጣሪነት ላይ ብቻ መደገፍ እንደሌለባቸው ሰፋ ባለ ጭብጥ ለተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰቷቸዋል።
በስልጠናው ማጠናቀቂያ የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ፀጋዬ ማቴዎስ፥ የተሰጠው ስልጠና አስፈላጊና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን አብራርተው ሰልጣኝ ተማሪዎች ከፍተኛ ግንዛቤ እንዳገኙ ከገለፁ በኋላ፣ ለአሰልጣኙ አቶ ልዑል እንዳለ እና ለሰልጣኝ ተማሪዎች የስልጠና ተሳትፎ የምስክር ወረቀት (Certificate) ተሰጥቶ፥ የእለቱ ስልጠና አብቅቷል።
14/03/2026
ዜና ሻሎም
=======
ሻሎም ቢዝነስና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ ፊቼ ጨምበላላ በአል ዋዜማን በእስፖርታዊ ክንዋኔዎች በደማቅ :ሁኔታ አከበረ።
ፊቼ ጨምበላላ ፥የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ በዓል ይሁን እንጂ ፥በአለም የትምህርት ፣የሳይንስ እና ባህል ቅርስ ምዝገባ ድርጅት( UNESCO ) የተመዘገበ የኢትዮጵያ እና የአለም በዓል፥ከመሆኑም አንጻር በኮሌጃችን ማህበረሰብ በደማቅ ሁኔታ እንዲከበር በተያዘው ዓመታዊ ዕቅድ መሰረት በደማቅ ተከብሯል።
በበአሉ አከባበርም ላበረከትነው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የበዓሉ የሩጫ ስፖርት ውድድሮች አዘጋጅ ከሆነው ከብራይት አፍሪካ ራን (BRIGHT AFRICAN RUN) በከፍተኛ ተሳትፎ የምስጋና የምስክር ወረቀት (ሰርተፍኬት) ለሻሎም ኮሌጅ ተበርክቷል ።
በዕለቱም የኮሌጃችን የቦርድ ሰብሳቢ፣ የኢትዮጲያ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት ዶ/ር ፍትህ ወልደሰንበት ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈው ከኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር አብረው ሮጠው በዓሉን አክብረዋል።
እንኳን ለፊቼ ጨምበላላ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
AYIDDE CAMBALAALLA!!
09/03/2026
ሻሎም ኮሌጅ ሀዋሳ
እንኳን ለሴቶች ቀን ማርች 8 በሰላም አደረሳችሁ ።
07/01/2026
ዜና ሻሎም ❗️
ሻሎም ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት መታሰቢያ "የገና በዓል" ከኮሌጁ መምህራን፣ ሠራተኞች እና ተማሪዎች ጋር ዛሬ ታህሳስ 28/ 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ በጋራ አከበረ።
በዕለቱም ኮሌጁ የልደት መታሰቢያ በዓልን ባከበረበት ወቅት የገና በዓል በኢትዮጵያና በሌላው የአለም ክፍል ምን ይመስላል? በሚል ጥናታዊ ፅሁፍ በኮሌጁ አካዳሚክ ፕሮግራም ኮርድኔተር አቶ አለማየሁ ዮናስ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም ተማሪዎች እና መምህራኖችን ያሳተፉ በዓሉ ላይ ትኩረት ያደረጉ የተለያዩ ጥያቄና መልሶች እንዲሁም አዝናኝ ጨዋታዎች ተደርገዋል።
በመጨረሻም የኮሌጁ የሬጅስትራር ሀላፊ የሆኑት አቶ ቶንጃ ቶማ ለበዓሉ ታዳሚያን የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ የዛሬው በዓል መልካም እንደሆነ ተናግረው በቀጣይም እንዲህ አይነት በዓሎች በኮሌጁ ውስጥ እንደሚቀጥሉ በመግለፅ የዕለቱን የመዝጊያ ንግግር አድርገው የዕለቱ ፕርግራም ባማረና በደመቀ መልኩ ፍፃሜውን አግኝቷል።
👉 ሻሎም ኮሌጅ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል በሠላም አደረሳቹ ለማለት ይወዳል።
መልካም በዓል!! 🎄 !
07/11/2025
ዜና ሻሎም
በሻሎም ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ለመምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች ሥልጠና ተሰጠ።
ሻሎም ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በዓመታዊ ዕቅድ: በያዘው መሰረት ለመምህራን እና ሠራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና በ"Igniting The Intrapreneurial Spirit"
በሚል ርዕስ በአሰልጣኝና ተመራማሪው ዶ/ር ይልማ ገለቱ አንድ ቀን የፈጀ ስልጠና መምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞችን በተቋሙ ውስጥ እንዴት የለውጥ ሐዋርያ መሆን እንደሚቻል እና ማሕበረሰባዊ እና አገራዊ ችግር ፈቺነት መላበስ እንደሚቻል፥ ሰፊ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ስልጠና ተሰጥቷል።
በስልጠናው ተሳታፊ የነበሩ ሰልጣኞች እንደገለፁት፥ስልጠናው ችግር ፈቺነት እና አስተሳሰብን በሰፊው የሚያዳብር እንደሆነ ገልፀው፥እንዲህ አይነት ስልጠና ስለተዘጋጀ ተቋሙን አመስግነዋል።
28/10/2025
ሻሎም ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ለአዲሱ የትምህርት ዘመን ምዝገባ ላይ ነን።
ይምጡ ይመዝገቡ: እጅግ አስፈላጊ በሆኑ በተመረጡ የትምህርት ዘርፎች ብቁ በሆኑ መምህራን እና በተደራጀ የመማሪያ ክፍሎች እናንተን ለማስተማር ተዘጋጅቶ ይጠብቃችሁዋል።
ለበለጠ መረጃ
0904 70 70 70 ደውለው ያነጋግሩን።